የዐቢይ አህመድ መንግስት ከትግራይ አሽባሪ ኃይሎች ጋር እንደሚደራደር መናገራቸው ተረጋገጠ

 አንድ የዳያስፖራ ቡድን ሊቀ መንበር፣ የቡድኑ አባላት ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ጋር ባካሄዱት የግል ውይይት ከትግራይ ኃይሎች ጋር ተኩስ አቁምን የተመለከተ ድርድር ይካሄዳል ሲሉ ዐቢይ እንደነገሯቸው ለአሶስየትድ ፕሬስ ገልጸዋል። የቡድኑ አባላት ከዐቢይ ጋራ ቅዳሜ ለ5 ሰዓታት መነጋገራቸውን የገለጹት የአሜሪካን ኢትዮጵያውያን ህዝባዊ ጉዳዮች ኮሚቴ ሊቀመንበር መስፍን ተገኑ ፣ዐቢይ የሀገሪቱን ጥቅም የሚያስቀድም ምክንያታዊ ድርድር ይካሄዳል ማለታቸውን ጠቅሰዋል። ባለፈው ሳምንት ኢትዮጵያን የጎበኙት የአሜሪካን ልዩ ልዑክ ስለሂደቱ ሃሳብ ሳይኖራቸው እንደማይቀርም ገልጸዋል።
ሁለቱ ወገኖች እንዲደራደሩ ዓለም አቀፍ ጥረቶች እየተደረጉ ቢሆንም ዐቢይ ግን ድርድር እንደሚካሄድ በይፋ ተናግረው አያውቁም። ጦርነቱ ከተጀመረ በኋላ የኢትዮጵያ መንግሥት ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት)ን አሸባሪ ሲል መፈረጁ የኢትዮጵያን መንግስትና ህወሓትን ወደ ድርድር ማምጣትን ፈታኝ አድርጎት ቆይቷል።የህወሓት ኃይሎች ወደ ትግራይ ካፈገፈጉ በኋላ መንግስት ትግራይ ላለመግባት መወሰኑ አቶ መስፍን ፣ የበርካታ ኢትዮጵያውያንን ፍላጎት የሚጻረር ነበር ሲሉ ተናግረዋል።በዚህ ምክንያት ኮሚቴያቸው በጉዳዩ ላይ ከመንግስት ጋር ለመነጋገር ጠይቆ የዐቢይ ምክትል ወይም የጽህፈት ቤታቸው ሃላፊ ያነጋግሩናል ብለው ሲጠብቁ ዐቢያ ራሳቸው መጥተው እንዳነጋገሯቸው ተናግረዋል።
በዚሁ ወቅትም ዐቢይ «ወደ ትግራይ ክልል አለመግባት የትግራይ ህዝብ ለተዋጊዎቹ ስለሚሰጠው ድጋፍ ቆም ብሎ እንዲያስብ የሚያስገድድ እንደሚሆንና ለመንግሥትም ጊዜ እንደሚሰጥ» ነግረውናል ብለዋል።አሶስየትድ ፕሬስ በጉዳዩ ላይ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ቃል አቀባይ ብሌነ ስዩምም ሆነ ከህወሓት ቃል አቀባይ ጌታቸው ረዳ አስተያየት ለማግኘት ቢሞክርም እንዳልተሳካላት ዘግቧል።
DW
ተጨማሪ ያንብቡ:  ፋኖ ዘመነ ካሴ ያስተላለፈው መመሪያ | ፋኖ በልዩ ኦፕሬሽን ወደ ከተማው ገብቷል ! | መንግስት በክልሉ ግማሹን ፋኖ እንደሚያስተዳድር አመነ !

1 Comment

  1. The prime minister Abiy Ahmed should be transparent enough on this issue (negotiation with the TPLF) because a lot is at stake. Historically, the TPLF takes advantage of negotiations to prepare itself for more aggression and conflict. It has never been a credible partner. But the front line regions ( Afar and Amhara) which have been bearing the burden of the TPLG invasions and destruction should be consulted.

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share