አፍሪካ ህብረት ልዩ ልዑክ ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ፤ ዛሬ የአማራ እና የአፋር ክልሎችን ይጎበኛሉ

የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ የአማራ እና አፋር ክልሎችን ዛሬ እንደሚጎበኙ አስታወቁ። ከትላንት በስቲያ እሁድ መቐለ ደርሰው የተመለሱት ኦባሳንጆ፤ ትላንት ምሽት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታ ጥበቃው ምክር ቤት ባደረገው ስብሰባ ላይ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ማብራሪያ አቅርበዋል።
ባለፈው ሐሙስ አዲስ አበባ የደረሱት ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ፤ ወደ መቐለ ከመጓዛቸው በፊት ከፕሬዝደንት ሳህለ-ወርቅ ዘውዴ፣ ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እንዲሁም ከኦሮሚያ ክልል ፕሬዝደንት ሽመልስ አብዲሳ ጋር ተገናኝተው መወያየታቸውን ትናንት ምሽት በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ጥበቃ ምክር ቤት ውይይት ላይ አስረድተዋል።
ከአዲስ አበባ በቪዲዮ ኮንፈረንስ ውይይቱን የተቀላቀሉት ልዩ ልዑኩ “እየተባባሰ በመጣው ውጊያ፣ ውጥረቱን ማርገብ በሚቻልበት መንገድ እና ለውይይት መንገድ በሚመቻችበት አካሔድ” ላይ ከኢትዮጵያ ፌደራል መንግሥት ባለስልጣናት እና ከኦሮሚያ ክልል ፕሬዝደንት ጋር ያደረጓቸው ውይይቶች “ፍሬያማ” እንደነበሩ አብራርተዋል። በትግራይ የተቀሰቀሰው ውጊያ የተስፋፋባቸውን የአማራ እና የአፋር ክልሎችን ዛሬ ማክሰኞ የመጎብኘት ዕቅድ እንዳላቸውም አስታውቀዋል።

Ethiopia Insider

ተጨማሪ ያንብቡ:  ከኢትዮጵያ ወደ ኬንያ የተላከ ስኳር ድንበር ላይ እየተበላሸ እንደሚገኝ ተጠቆመ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share