ፖሊስ ከማህበረሰቡ የተሰጠውን ጥቆማ መሰረት በማድረግ መርካቶ ውስጥ ጣና የገበያ ማእከል ጎን አድማስ ህንፃ ውስጥ አዲሱን የጦር መሳሪያ ቁጥጥር አዋጅ በሚፃረር መልኩ ተከማችቶ የተገኘው ከ20ሺ በላይ ጋጀራ በቁጥጥር ስር በማዋል ጠቅላላ ምርመራ እያካሄደበት እንደሆነ የመርካቶ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ወንጀል ምርመራ ዘርፍ ሃላፊ ምክትል ኢኒስፔክተር ብርሃኑ አለሙ ተናግረዋል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ ለሽብር ተግባር ሊውል የነበረ ከ20ሺ በላይ ጋጀራ በቁጥጥር ስር ዋለ
በአዲስ አበባ ከተማ ለሽብር ተግባር ሊውል የነበረ ከ20ሺ በላይ ጋጀራ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያካሄደ እንደሆነ የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የመርካቶ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ አስታወቀ፡፡
የጦር መሳሪያውን ክምችት በመጠቆም ረገድ የህብረተሰቡ ትብብር ከፍተኛ ነበር ያሉት ምክትል ኢኒስፔክተር ብርሃኑ የብሄራዊ ደህንነት ባለሙያዎችና የፖሊስ አባሎችም ድርሻ የጎላ እንደነበር ጠቁመዋል፡፡
አሁን ካለው ወቅታዊ ሁኔታ አንፃር በተለያዩ የሃገራችን አካባቢዎች በማሰራጨት ለሽብር አላማ ለማዋል ታሳቢ ያደረገ የጦር መሳሪያ ሊሆን እንደሚችል ተገምቷል ያሉት ሃላፊው ከዚሁ ጋር ተያይዞ ወንጀለኛው በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተካሄደበት ነው ማለታቸውን የአዲስ ከተማ ክፍለ ኮሙዩኒኬሽን የተገኘው መረጃያሳያል።
የሽብርተኛ ቡድኖችን ተልዕኮ ለመፈፀም በተለያዩ አካባቢዎች የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦችን ህዝቡ ከፀጥታ ሃይሉ ጋር በመቀናጀት እያደረገ ያለውን ስራ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተመላክቷል፡፡
(ኢ ፕ ድ)
የእንግዳ ልኡክ ጽሁፎችን የአርትዖት አምዶችን ወይም አስተያየቶችን እና ትንታኔዎች መጣጥፎችን እንቀበላለን:: ሀሳበወትን እና እውቀትዎን ለአንባቢዎቻችን እንዲያካፍሉ እንጋብዛችኋለን። ጽሑፋችሁ በዓለም ዙሪያ በሚሊዮን የሚቆጠሩ አንባቢዎችን ይደርሳል፣ ያለቀ ጽሁፍ በ admin@zehabesha.com በኩል ያቅርቡ! የሚሰነዘሩ አስተያየቶች ደራሲውን ብቻ የሚያንፀባርቁ እንጂ የዘ-ሐበሻ ዶት ኮም ኦፊሴላዊ ፖሊሲ ወይም አቋም የሚያንፀባርቁ አይሆኑም!!