በአዲስ አበባ ከተማ ለሽብር ተግባር ሊውል የነበረ ከ20ሺ በላይ ጋጀራ በቁጥጥር ስር ዋለ

በአዲስ አበባ ከተማ ለሽብር ተግባር ሊውል የነበረ ከ20ሺ በላይ ጋጀራ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያካሄደ እንደሆነ የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የመርካቶ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ አስታወቀ፡፡
455
455

ፖሊስ ከማህበረሰቡ የተሰጠውን ጥቆማ መሰረት በማድረግ መርካቶ ውስጥ ጣና የገበያ ማእከል ጎን አድማስ ህንፃ ውስጥ አዲሱን የጦር መሳሪያ ቁጥጥር አዋጅ በሚፃረር መልኩ ተከማችቶ የተገኘው ከ20ሺ በላይ ጋጀራ በቁጥጥር ስር በማዋል ጠቅላላ ምርመራ እያካሄደበት እንደሆነ የመርካቶ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ወንጀል ምርመራ ዘርፍ ሃላፊ ምክትል ኢኒስፔክተር ብርሃኑ አለሙ ተናግረዋል፡፡

የጦር መሳሪያውን ክምችት በመጠቆም ረገድ የህብረተሰቡ ትብብር ከፍተኛ ነበር ያሉት ምክትል ኢኒስፔክተር ብርሃኑ የብሄራዊ ደህንነት ባለሙያዎችና የፖሊስ አባሎችም ድርሻ የጎላ እንደነበር ጠቁመዋል፡፡
አሁን ካለው ወቅታዊ ሁኔታ አንፃር በተለያዩ የሃገራችን አካባቢዎች በማሰራጨት ለሽብር አላማ ለማዋል ታሳቢ ያደረገ የጦር መሳሪያ ሊሆን እንደሚችል ተገምቷል ያሉት ሃላፊው ከዚሁ ጋር ተያይዞ ወንጀለኛው በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተካሄደበት ነው ማለታቸውን የአዲስ ከተማ ክፍለ ኮሙዩኒኬሽን የተገኘው መረጃያሳያል።
የሽብርተኛ ቡድኖችን ተልዕኮ ለመፈፀም በተለያዩ አካባቢዎች የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦችን ህዝቡ ከፀጥታ ሃይሉ ጋር በመቀናጀት እያደረገ ያለውን ስራ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተመላክቷል፡፡
(ኢ ፕ ድ)
ተጨማሪ ያንብቡ:  ከባልደራስ-መኢአድ ሰለኮረና፣ ሰለ ጦርነት እንቅስቃሴና ሰለኃይማኖት አባቶች የተሰጠ ወቅታዊ መግለጫ 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share