“ሕወሃትን ለመዋጋት የኢትዮጵያ ሕዝብ ቀስቃሽ አያስፈልገውም!” ከአገር አድን ግብረኃይል የተሰጠ ወቅታዊ መግለጫ

/

የኢትዮጵያ አገር አድን ግብረኃይል

SAVE ETHIOPIA TASKFORCE

ዋሽንግተን ዲሲ

ሰሜን አሜሪካ       

(August 19, 2021

ለሃያሰባት ዓመታት በሕወሃት የጭቆና ቀንበር ሲማቅቅ የነበረው የኢትዮጵያ ሕዝብ ሕወሃትን እንዲታገል ቅስቀሳ ያስፈልገዋልን? ሕዝቡ በተለይም በአማራ ክልል አስታጥቁን እያለ ለመንግሥት ውትወታውን አቋርጦ በማያውቅበት ሁኔታ ተመችቶት እንደተኛ ሁሉ ለመቀስቀስ መሞከር ስሜት ይሰጣልን? በእውነት እንነጋገር ከተባለ መቀስቀስ ያለበት የተናጠል ተኩስ አቁም ያወጀውና የአማራ ልዩ ሃይልና መከላከያ ከቁልፍ ቦታዎች እንዲያፈገፍጉ ትእዛዝ የሰጠው መንግሥት ነው ወይስ ከፍተኛ መስዋዕትነት በመክፈል ሕወሃትን ከኮረም ባሻገር ያሳደደው ሕዝቡ?

ለረዥም ጊዜ በመታሠር፣ በመገደል፣ ለከፍተኛ ስቃይ ተዳርጎ አካለ ጎደሎ በመሆን፣ በማንነቱ በመዋረድ፣ በመዘረፍና ከሃገር በመሰደድ ከፍተኛ መስዋዕትነት ከፍሎ ሕወሃትን ከሦስት ዓመት በፊት ከስልጣን ያባረረው ሕዝብ በተለያየ መንግሥታዊና ግለሰባዊ አሻጥርና ሴራ እንደገና እንዲያንሰራራ የተደረገውን ሕወሃትን እንዲዋጋ ቅስቀሳ ሊደረግለት ይገባልን? ከአማራው ጋር የማወራርደው ሂሳብ አለኝ ያለውን ሕወሃት ከተከዜና ከኮረም ወዲያ ለማሻገር በተለይ አማራው መቀስቀስ ያስፈልገዋልን? ሕዝቡ ለሃገሩ፣ ለወገኑና ለክብሩ ቅስቀሳ ያስፈልገዋል ብሎ ማሰብ አንድም ሕዝቡን በደንብ አለማወቅ ነው፤ ሌላም በመንግሥት በኩል በየጊዜው የተሠሩ ሴራና ስህተቶችን ለመሸፈን መሞከርና እንዲሁም የግል ዝና ለማትረፍ መባከን ነው ብለን እናምናለን።

ሕዝቡ በጋራ ሁኖ አባቶቹ በጋራ ያቆዩለትን ሃገር ዳር ድንበሯን ከጠላቶቿ በመጠበቅ ለሚቀጥለው ትውልድ ማስተላለፍ እንዳለበት ማንም ሊነግረውና ሊያስተምረው አይገባም። ቢሆንም በተለይም ፊት ለፊት ከጠላት ጋር ሲፋለም ከጀርባው ሴራ የሚጎነጎንበት ከሆነ፣ ያስለቀቀውን መሬት ለቀህ ውጣ የሚባል ከሆነ፣ ከጠላት የማረከው መሣሪያ ተሰብስቦ የሚወሰድበት ከሆነ፣ ሲደራጅ አትደራጅም የሚባል ከሆነ፣ አንተ ያልመከርክበት ሕገመንግሥት ለአንድ ክልል ብቻ ተብሎ አይለወጥም የሚባል ከሆነ፣ በስተሰሜን አማራው ከሕወሃት ጋር ሲፋለም ኗሪነታቸው በኦረምያ ክልል የሆኑ የአማራ ሚልሽያዎች ትጥቃቸውን በግድ እንዲፈቱ እየተደረገ የሆነኝ ተብሎ ለኦነግ ሸኔ እርድ የሚጋለጡ ከሆነ እንዴት ነው ሕዝቡ በተለይም አማራው በሕወሃት ላይ ያልተከፋፈለ ትኩረት ሊኖረው የሚችለው? ለመሆኑ በአፋር ክልል ለማንም የማፈግፈግ ትእዛዝ ሳይሰጥ በአማራ ክልል ግን ከኮረም፣ ከአለማጣና ከቆቦ የአማራ ልዩ ሃይልና ሚሊሽያ እንዲያፈገፍጉ ለተደረገበት ክስተት መልስና ማብራሪያ የሚሰጥ አካል አለን?

ተጨማሪ ያንብቡ:  አንድነት እና መኢአድ በመጪው እሁድ በባህርዳር በተጠሩት ሰልፍ የተነሳ ከወዲሁ ወጣቶች እየታፈሱ ነው

ለምንድን ነው ወገናችንን በተለይም በሃገሩ ዳር ድንበርና በወገኑ ህልውና የማይደራደረውን አማራውን በተደጋጋሚ በተወሳሰበ ሴራ ልቡን የምናደማውና ምሬት የምንፈጥርበት? በውጭ ሃገር በሰላማዊ ሰልፍ ላይ የአማራን መጨፍጨፍ ዓለም እንዳያውቀው የከለከለ ስብስብና በግለሰብ ደረጃ ብዙ ነገር የምንጠብቅባቸው የተወሰኑ ግለሰቦች ባዘጋጁት “ሕዝባዊ የትብብር ጥሪ” የውይይት ፕሮግራም ላይ በአማራው ላይ የተፈፀመውን የዘር ማጥፋት ወንጀል ላለመጥቀስ የዙሪያ ጥምጥም ሲሄድና በሃገር አንድነት ስም አማራው ለደረሰበትና እየደረሰበት ላለው ስቆቃ በከፊልም ሆነ በሙሉ መጠየቅ የሚገባውን አካል ላለማስቀየም ጥንቃቄ ሲደረግ ማየት እንዴት ልብ ይሰብራል!!!

ውድ ወገናችን ሆይ! በተለይም ብዙ ስቃይ ያስተናገድከውና በማስተናገድ ላይ ያለኸው አማራ ወገናችን ሆይ! ፈተናዎችህ ከዕለት ወደዕለት እየከፉና እየጨመሩ ሲሄዱ እንጂ ሲቀንሱ እየታዩ አይደለም። ማንኛውንም ዓይነት ፈተና ለዘመናት ተወጥተሃል። ያለጥርጥር አሁን የገጠመህንም ትወጠዋለህ። ቢሆንም ጠንቅቀህ ማወቅ ያለብህ የስነልቦና ሰለባ ሊያደርጉህ የሚፈልጉት “ነፍጠኛ፣ ጨቋኝ፣ ሠፋሪና መጤ” እያሉ የሚከሱህና የሚያንገላቱህ ብቻ አይደሉም። ከአብራክህ የወጡ አማሮችም ከሌሎች ያለበቂ ምክንያት ከሚጠሉህ ጋር እየተናበቡ እያስጠቁህ መሆኑን ላፍታም መዘንጋት የለብህም። በማንነትህ ግድያ የሚፈጽሙብህ ሕወሃትና ኦነግ ሸኔ ቢሆኑም ካንተው አብራክ የወጡም ልጆችህ ባልተናነሰ ሁኔታ ጉዳት እያደረሱብህ እንደሆነ ማመንም ቢያቅትህ አምነህ ልትቀበል ይገባል እንላለን። ትናንት እያንዳንዱን ካፋቸው ጠብ የሚለውን ቃል ታከብርላቸው የነበሩ ግለሰቦች ዛሬ ላንተ ሳይሆን መጨፍጨፍህን ለማያምን መሪ የካድሬነት ሥራ እየሠሩብህ ነው። ጠላቶችህ ከውስጥም ከውጭም ስለሆኑ ከእስከዛሬ በተለየ መንገድ ልትደራጅ ይገባል እንላለን። ከፊትለፊትህ ረዥም ጉዞ ይጠብቅሃል። በጊዜያዊ ድል ሳትሳከር በምታምናቸው መሪዎች ዙሪያ እየተሰባሰብክ ለራስህና ለሃገርህ ህልውና የጀመርከውን ተጋድሎ ከግቡ እንድታደርስ ጥሪያችንን እናቀርብልሃለን!!!

ተጨማሪ ያንብቡ:  በወለጋ ጉዳይ:-ከአማራ ፋኖ ከቤተ-አምኀራ ፋኖ የተሰጠ መግለጫ/በሞታችን ላይ እየተሳለቁብን ነው !

ጀግናው ወገናችን ሆይ! ስለኢትዮጵያ አንድነት አስፈላጊነትና ስለሕወሃት ምድራዊ ገሃነምነት ማንም ሊደሰኩርልህ አይገባም። ከሌሎች አገር ወዳድ ወገኖችህ ጋር በመሆን የኢትዮጵያን ዳር ድንበር ለማስከበር ስትታገል ለህልውናህም ጭምር እየታገልክ መሆን እንዳለበት ላንተ አንነግርህም። የአገርህ ህልውና ከአንተ ህልውና ጋር የተያያዘ ስለሆነ ዛሬ ከምንም የበለጠ ለራስህ ህልውና ቅድሚያ መስጠት እንዳለብህ እንደተገነዘብክ የሚያጠራጥር አይደልም።  ለራስህና ለሃገርህ ህልውና የሞት የሽረት ተጋድሎ እያደርግክ ባለህበት ሰዓት “በሃገር ጉዳይ ዳር መቆም የለም” የሚል ጥሪ የሚያቀርቡልህን ለመሆኑ ዳር የቆመውን ለይታችሁ አውቃችኋልን ብለህ ልትጠይቃቸው ይገባል እንላለን።

ጀግናው የአማራ ሕዝብ ሆይ! ባንተ ላይ ባለፉት ሰላሳ ዓመታት በተለይም በላፈው ሦስት ዓመት የደረሰውን ሥቃይና ግፍ “ጥቃቅን የፖለቲካ ልዩነት” ተብሎ መጠቀስ ነበረበትን? ስቆቃህ የራስህ ጥፋት በሚመስል መልክ መቅረብ ነበረበትን? የራስህን ግብዝነት (Ego) ወደጎን ጥለህ እኛን ምሰል መባል ነበረብህን? ዲያስፖራ የምትገኝ ወገናችን ሆይ! በገንዘብህም፣ በዲፕሎማሲም፣ በእምባህም መቼ ነው ለወገንህ ያልደረስከው? ስቆቃውን ስቆቃህ ያላደረግከው? “በሃገር ጉዳይ ዳር መቆም የለም” ከመባልህ በፊት እንደወትሮህ የተቻለህን እያደረግክ አልነበረምን? ነው ወይስ ለወገንህ የምትዘረጋለት ሁሉ በተወሰኑ አካሎች እጅ ብቻ መድረስ አለበት?

አገር ወዳድ ወገናችን ሆይ! ለዘመናት አባቶችህ እንዳደረጉት ለውድ ሃገርህ ምንጊዜም በጋራ መቆም አለብህ። የአማራና የአፋር ክልል በከፊል በወያኔ ወረራ አኬልዳማ ከመሆናቸው በፊት የድረሱልኝ ጥሪ አቅርበህ ነበር። ግን ሰሚ አላገኘህም። ስለሆነም በጥብቅ የምናሳስብህ በመንግሥት መዋቅር ውስጥ በተሰገሰጉ ሴረኞችና ሆድ አደር ካድሬዎች በተደጋጋሚ በስልታዊ ማፈግፈግ ስም የሆነኝ ተብሎ ለአደጋ ስለተጋለጥክ ራስህን ከኋላህም ከፊትህም እንድትጠብቅ ነው። የአንተ ህልውና ለአገርህ ህልውና ዋስትና ነውና!

ተጨማሪ ያንብቡ:  ወደ ሃዋሳ ለድጋፍ ሲሄዱ በመኪና አደጋ የሞቱት ወጣቶች ፎቶ ግራፍ ይመልከቱ

 

“ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!”

“አንድነት ሃይል ነው!”

የኢትዮጵያ አገር አድን ግብረኃይል

 

የኢትዮጵያ አገር አድን ግብረኃይል በሰሜን አሜሪካ

——————————————————————————————————–

Email- ethiopiahageraden@gmail.com

Phone – 8477224193

2 Comments

  1. I do not know why and how your statement can make a real sense when it comes to the very hard reality happening right on the ground!
    Can you please not just tell but answer the very challenging question why and how TPLF guys could march from up there Raya/Wollo all the way down to Debre Tabor and who know next all the way down to Bahir Dar?
    Do you think that it was and is because of lack of meglecha and propaganda that made TPLF” s fast moving possible?
    Don’t you know this dirty war is the war of not only TPLF but also Oromuma politicians including those who are advisors of the very politically infantile and cynical and morally bankrupt prime minister?
    Do you really understand what kind of evil-driven sabotage or conspiracy is going on within both those politicians in Arat Kilo palace and those military officials of the so-called Prosperity Party who are dominantly with the very mentality of Oromuma?
    Do you really believe that the people of Ethiopia have a governemt in a real sense of the term?
    Is it not shameful if not painfully stupid political mentality on the one hand to cry hard about the criminal act of TPLF but on the other hand to praise those guys of palace politics?
    Slow down, take deep breath, think deep and big and help the very confused and horrified innocent people of Ethiopia instead of issuing and dispatching the very monotowns and good for nothing rhetoric and statement (meglecha) that we have come through so many years!

  2. ወገኔ ችግራችን በጣም ውስብስብ ነው። ከ 30 ዓመት በላይ የአማራ ህዝብ መከራ ሰማይ ላይ መድረሱ ዓሊ የማይባል ጉዳይ ሆኖ እያለ ዛሬም የውጭና የውስጥ ጠላቶቻችን የሚነግሩን ስለ ወያኔ ጉዳት ብቻ ሆኗል። ለምሳሌ የእንግሊዙን ወሬ አፈንፋኝ ቢቢሲን ብንወስድ 100% የወያኔ የፕሮፓጋንዳ መሳሪያ ነው ለማለት ይቻላል። በቅርቡ በአፍሪቃ ገጽ ላይ እንዲህ ብሎናል። “Ethiopian teenagers become pawns in propaganda war” የሚገርመው እነዚህ የሃሳብ ስንኩላን በቦታው ተገኝተው እውነትና ውሸቱን አንጓለው ዘግበው ቢሆን ኑሮ መልካም ነበር። ግን ድርጊታቸው ሁሉ በስማ በለው ነው። በእውነት የምናያቸው ያለ እድሜአቸው መሳሪያ ያነገቡ የወያኔ ታጣቂዎች የፈጠራ ወጣቶች ናቸውን? አዎን እኔ በየመድረኩ ምርኮኛን በማናዘዝ አላምንም። ምርኮኛ የመረጃ ምንጭ እንጂ የዲስኩር ማሳኪያ ሊሆን አይገባም። ግን ሰርዓትና ደንብ በሌለው ምድር ላይ ሁሉም ጋዜጠኛና ሳንቲም ፈላጊ በመሆኑ ለሃገር የቱ ይጠቅማል፤ ጉዳዪስ ማንን ይጎዳል የሚል ማንም የለም። ሁሌ ቀረርቶና ሽለላ ብቻ። ያም ገደለ፤ ይኸም ሞተ በሆድ ሁሉን ይዞ ራስን ለቀጣይ ፊልሚያ እንደማዘጋጀት እንደ ሃምሌ ዝናብ በማያቋርጥ መግለጫ ልባችን ውልቅ ልትል ነው። በኢትዮጵያ ላይ በተለይም በአማራ ህዝብ ላይ የተቋጠረው ሴራ ጠሊቅ ነው። በሳውዲ አረቢያ ዘር እየጠየቁ አማራ ነኝ ባለው ላይ የሚያደርሱት ማዋከብና ዝርፊያ ይህ ነው አይባልም። ይህ ደግሞ ለዘመናት ወያኔና ሻቢያ የዘሩት አማራ ጠል የሆነው የጥላቻ ፓለቲካ ውጤት ነው። በአፋር ብዙ ሰው ሲያልቅ፤ በአማራ ክልል ወያኔ ከድንበሩ ዘልቆ ወረራ በመፈጸም ሰው ሲያፈናቅል፤ ሲዘርፍና ሲገድል አንድም የውጭ ሃገር ጋዜጣ ለምን ብሎ የጠየቀ የለም። ጉዳዪ ከአሜሪካው ደንባራ የውጭ ፓሊሲ ጋር የተያያዘ ነው። በቀጥታም ሆነ በእጅ አዙር ለወያኔ ድጋፍ የምታደርገው አሜሪካ በሳማንታ ፓውል በኩልና በሌሎችም ባለስልጣኖቿ በየቀኑ የሚያላዝኑት ስለ ትግራይ ችግር ነው። ሌላው ለእነርሱ ሰው አይደለም። ይህ ግን የከፋፍለህ ግዛው የሩቅና የቅርብ እይታቸው እንጂ ለትግራይ ህዝብ ገዷቸው አያውቅም። አንድም ቀን ለጥቁር ህዝብ ገዷቸው አያውቅም።
    20 ዓመት ሙሉ ከአፍጋንስታን ተፋላሚዎች ጋር ሲላተሙ የኖሩት አሜሪካኖችና ተከታይ ሳተላይቶቻቸው አሁን በሚዲያ ስለ አፍጋኒስታን የሚያናፉት በአፍጋኒስታን ላሉ ነጮች ገዷቸው እንጂ ስለ አፍጋኒስታን ህዝብ ደንታ የላቸውም። አሁን 24 ሰአት ስለ አፍጋኒስታን የሚዘግቡት 20 ዓመት ሙሉ በዚህም በዚያም በአፍጋኒስታን ላይ የመከራ ዶፍ ሲወርድ የት ነበሩ? እንጠይቅስ ከተባለ አሁን በየመን ከሚደርሰው ሰቆቃ የአፍጋኒስታኑ ይበልጣል? ግን ለሰው ልጅ ስብ ዕና አንድም ቀን ገዷቸው አያውቅም። አሁን ደግሞ ኢትዮጵያን ለማፈራረስ አንዴ ኦሮሞችን ሌላ ጊዜ በሃሳብ የዘገዪ ሌሎች ሃይሎችን ከወያኔ ሃይሎች ጋር በሰውርና በቀጥታ መንገድ እየሰበሰቡ የሚያማክሩት ተላላኪ መንግስት ለመመስረት ባላቸው ናፍቆት ነው።
    አሜሪካ ለኢትዮጵያ ጠላት እንጂ ወዳጅ ሆና አታውቅም። በሱማሊያ ስንወረር የገዛነውን መሳሪያ እንኳን መስጠት አልፈለገችም። ያ በፈጠረው ችግር የወታደሩ መንግስት ከራሽያና ከተከታዪቿ ጋር ሽርክና ገጥሞ በዚህም በዚያም እንድንላተም ሆነናል። አሜሪካ አፍሪቃዊ እድገትን አትፈልግም። ጎላና ወጣ ያሉ መሪዎችንም እንዲኖሩ አትፈቅድም። ታሪክን ተመልሶ ማገላበጥ ተገቢ ነው። የአውሮፓና የአሜሪካ የሚዲያ ሽፋን በ “Corporatocracy” የሚመራ በነጻነትና በራሱ አስቦ እውነትን የማይተነፍስ የአስመሳዪች ጥርቅም ነው። መንግስት አለ ይባል እንጂ መሪነቱን የያዙት እነዚሁ ባለጠጎችና ስብስቦች ናቸው። ለዚህም ነው በሺህ የሚቆጠሩ ላቢይስቶች ህግና ደንብ ያወጣሉ የተባሉትን የመንግስት አካላት በቀጥታና በተዘዋዋሪ የእጅ መንሻ በመስጠት ድምጽን የሚያገኙት ትክክለኛውን ሃሳብ በተሳሳተ ለውጠው ድምጽ የሚሰጡት።
    እርግጥ ነው ወያኔን ለመዋጋት የኢትዮጵያ ህዝብ ቀስቃሽ አያስፈልገውም። ወያኔ ያልፈነከተው ማን አለና። የዚህ ሁሉ የጭቆናና የመከራ ዶፍ የወረደበት የሃገራችን ህዝብ እነዚህን ሃይሎች ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ተፋልሞ የሃገሪቱን ሰላም ሊያስከብር ይገባል። ያው በድምጽ በለቀቃችሁት መረጃ ላይ እንዳላችሁት ግን እንዴት ተብሎ ነው የተበተነ፤ የተደቆሰ፤ የተደመሰሰ፤ ተቆርጦ የቀረ፤ ዋሻ ውስጥ የገባ፤ መሳሪያውን የተቀማ ወያኔ አፋር ዘልቆ፤ እስከ ደብረ ታቦር መዝለቅ የቻለው? ለምንስ የአፋርና የአማራ ህዝብ መሬት ላይ ውጊያው እንዲሆን ተፈቀደ? የውስጥም የውጭም ሴራ እንዳለ በዚህ ይህ ጉዳይ አመላካች ነው። ስለሆነም የአማራው ህዝብ ይህ ወገን ለእኔ ይደርሳል፤ ያ እጎኔ ይቆማል ከማለት ይልቅ ራስን አስታጥቆና ሰልጥኖ እሳትን በእሳት በመፋለም የራስንና የሃገርን ክበር ማስጠበቅ አማራጭ የማይገኝለት ጉዳይ ነው። ወያኔ በህይወት እያለ ለአማራ ህዝብ አይተኛም። በማይካድራ ያለ ርህራሄ ሲገሏቸው እየተሳደቡ ነው አንተ አህያ አንተ ንፍጣም አማራ እያሉ። ሰውን አህያ ብሎ የሚጠራ ራሱ አጋስስ መሆኑን ረስቷል። ያ ትራፊ ገዳይ ነው ግማሹ ዳግሞ ከሱዳን በኩል ሲገባ የተደመሰሰው። መቼ የሰው ደም አፍሶ ሰው ደም ሳይፈስ ይቀርና። እንጠንቀቅ። በቃኝ!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share