ፍፁም ነው ዕምነቴ፣ ናዚስት ወያኔ ነው ጠላቴ!!! – መስፍን ማሞ ተሰማ

tplf nazi

ትግራይ ውስጥ በዕብሪት ተወጥሮ የነበረው ናዚስት የትግራይ ነፃ አውጪ ወንበዴ በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በሁለት ሳምንት ተወቅጦ እንደ ዱቄት ቢበተንም በዓለም ዐቀፍ የኢትዮጵያ ጠላቶችና በሀገር በቀለ ባንዳዎች ርብርብ እነሆ ጣዕረ ሞቶቹን ትራፊ መሪዎቹን ይዞና ትግራይ ወለድ ጋሻጃግሬዎቹን አደራጅቶ የሰዖል ላንቃውን ከፍቶ ተነስቷል።

የኢትዮጵያ መዥገርና ታሪካዊ ደመኛ ጠላት የርኩሰት ሁሉ ማህፀን ወያኔ በተረፈ ጣዕረ ሞት መሪዎቹ ያሰባሰባቸው የሽፍቶች ጭፍራ ለመጨረሻው ግብዐተ መሬቱ – ዳግም ለማያንሰራራበት ሞቱ፤ በዲያቢሎስ አውሎ ነፋስ እየከነፈ በአማራና በአፋር የኢትዮጵያ ግዛቶች ሣጥናኤላዊ ጥፋቱን ተያይዞታል።
ላታመልጪኝ፥ አታሯሩጪኝ – እንዲል ብሂሉ – ከመቃብር ወጥቶ ድንጋይ ለድንጋይ የሚዘለው ወራሪው ናዚስት ወያኔ ከመላው ኢትዮጵያ በተመመው የኢትዮጵያውያን የተባበረ ክንድ ዳግም እንዳይነሳ ሆኖ ወደ ትቢያነት ይቀየራል።
ዕርግጥ ነው ከሲዖል የወጣው ናዚስት ወያኔ ኢትዮጵያን ለመበተን በተረፈ ጣዕረ ሞት መሪዎቹ ምሎ ቢገዘትም ፤ ይህ ቅዠቱ እንኳንና አንድ መቶ ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን በህይወት እያሉ ቀርቶ አንድ ኢትዮጵያዊም እንኳን ቢቀር ቅዠቱ የቀን ብርሃን አያይም። ይሁንና ከተበተነበት ተሰባስቦ በአማራና በአፋር ግዛቶቻችን ወረራ ለማካሄዱና ሳጥናኤላዊ ጥፋት ለማድረሱ – በግልፅ የሚታዩና የምናውቃቸው፣ ደግሞም በግልፅ የማይታዩና የማናውቃቸው ምክንያቶች ቢኖሩም – በናዚስቱ ወያኔ የመጨረሻ ግብዐተ መሬትና በኢትዮጵያ ትንሳኤ ላይ ያለን ዕምነት ግን ፀሀይ በምሥራቅ እንደመውጣቷ ያለ ዕውነት ነው!!
ይሁንና የጣዕረ ሞት ወያኔ አፅም ማንሰራራቱ ለጊዜውም ቢሆን ውስጣችንን መናጡ ቆሽታችንን ማድበኑ ፅናታችንንም ባይሆን ተስፋችንን ማንገራገጩ አልቀረም። በዚህ የጦርነት ሂደት ስሜታችን ለመቀያየሩ ሁለት ጉልህ ምክንያቶች አስተዋፅዖ አድርገዋል። አንዱ መረን የለቀቀው የfb አክቲቪስት ተብዪዎችና ዩቱዩበሮች ‘ከውስጥ አዋቂ ምንጮችና ከወታደራዊ ቀጠና የደረሰን መረጃ’ እያሉ የሚለቁት “ሰበር ዜና” ውሎ ሳያድር ‘ዱቄት ዜና’ እየሆነ የሕዝብ ስነ ልቦና መስለቡና ዕምነት መሸርሸሩ ነው።
በእኒህ የfb የጦር አበጋዝ አክቲቪስቶችና ዩቲዩበሮች ‘ያልተደመሰሰ፣ አንገቱ ያልተቀላ፣ መሞቱ በይፋ ያልተነገረ’ ተረፈ ጁንታ የለም። ያልተዘከዘከ ወታደራዊ መረጃ የለም። በኤር ኮንዲሽንድ ቤቱ ሆኖ ‘ስለ ውጊያው መረጃ ሳሰባስብ እንቅልፍ አጥቼ አደርኩ’ ያላለን አክቲቪስትና ዩቲዩበር የለም። አሉታዊ ተፅዕኗቸውን ሳይሆን በየገፃቸው የሚንጋጋውን የአውራ ጣት ብዛት ብቻ ግባቸው ያደረጉ ናቸውና ጉዳታቸው ብዙ ነው።
ሁለተኛውና ዋናው ደግሞ የፌዴራል መንግሥቱ በዚህ ከናዚስት ወያኔ ጋር በሚደረገው የሞት ሽረት ጦርነት (የመንግሥት አካላት በሚያሳዝን መልኩ ግጭት ይሉታል) ለሕዝብ የሚያቀርበው ወቅታዊና ተዓማኒ መረጃና ሀገራዊ ማረጋጊያ አለመኖሩ ነው። ከዓለም ዐቀፍ ዲፕሎማሲ እስከ ሀገር ዐቀፍ የሕዝብ ዲፕሎማሲ ‘ባወጣ ያውጣ’ የመሰለው የመንግሥት ድርጊት በብዙ አጠያያቂ ኩነቶች የተሞላ ቢሆንም ‘መጀመሪያ ሀገሬን’ ያለው ሕዝብ ግን ሁሉን ችሎ በመንግሥት የተጠየቀውን ብቻ ሳይሆን ያልተጠየቀውንም ከማድረግና ከመንግሥት ጎን ከመሆን አልታቀበም፤ ከኢትዮጵያ ህልውና የሚያስቀድመው አንዳች ስንኳ የለውምና።
በሰሜን ወሎና በአፋር ክልል በኩል ‘የሰሚ ሰሚ’ ለሕዝብ ጆሮ የሚደርሰው “ውሀ ቅዳ፥ ውሀ መልስ” አይነት የጦርነት ቀጠና ውሎ ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከተው መንግሥት ‘የመረጃ መዕቀቡን’ አቁሞ ለሕዝብ ዕውነታውን ማሳወቅና መፍትሄውንም ማመላከት ይኖርበታል።
ከወራሪው ናዚስት ወያኔ ጋር የሚካሄደው የፍፃሜው ጦርነት ብሄራዊ እንጂ ከአማራና ከአፋር ጋር ባለመሆኑ የጦርነቱን ልጓም መንግሥት ለመጨበጡና ለመምራቱ በሙሉ ሀይሉና አቅሙ ለሚደግፈው ሕዝብ የማሳወቅና የማረጋጋት ሀላፊነትም አለበት።
የሚሥጢርም ዓይነት አለውና ፌዴራል መንግሥቱ ዙሪያ ጥምጥሙ ሁሉ ለሕዝብ ምሥጢር መሆን የለበትምና በብርቱ ሊታረም ይገባል። ለሞቱ የሚንፈራገጠው ጣዕረ ሞት ወያኔን ፌዴራል መንግሥቱ በዓለም መድረክ በዲፕሎማሲው አፈር ድቤ ማብላት የሚያስችል ሀቅ ተሸክሞ በጁንታው እብለት ለመሸነፉ መንግሥት ራሱን መፈተሽና ማረም የሚጠበቅበት አንዱና ዋናው አብይ ተግባር ነው።
ይህም ሁሉ ሆኖ ግን እንደ ሀገር – ኢትዮጵያ – እና እንደ ሕዝብ – ኢትዮጵያውያን – ምርጫችን አንድና አንድ ብቻ ነው። ኢትዮጵያን ወደ ወጣበት ሲዖል ይዟት ለመግባት በትራፊ ሳጥናኤላዊ መሪዎቹ ፊታውራሪነት የሲዖልን ሠራዊት አሰልፎ በውስጥ ባንዳዎችና በዓለም ዐቀፍ አፍቃሪ ናዚስት ወያኔ ሀይላት ብርቱ ድጋፍ የዘመተብንን ወራሪ ናዚስት ወያኔ ከአኩሪው የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊትና ከመላው ኢትዮጵያ ከተመመው ሕዝባዊ ሠራዊት ጎን በፅናት በመቆም የዘመናት የኢትዮጵያን ጠላት ወደ ዘለዓለማዊ መቃብሩ ሸኝተን ሀገራችንን እና ህይወታችንን መታደግ!!! ኢትዮጵያ በተባበረው የልጆቿ ክንድ በግርማ ሞገስ ከፍ ትላለች!!!!
ተጨማሪ ያንብቡ:  ሁሉ ሠው ያንብበው  እንዲነበብ ያድርግሐ

1 Comment

  1. ትላንትም ስንፎክር ዛሬም ስናፏክር ጀንበር እየወጣች ጠልቃለች ጊዜውም ሳናስበው ነጉዷል። በሃገራችን ረጅም ታሪክ ውስጥ እንደ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ያለ መሰሪ ሃይል በምድሪቱ ኖሮ አያውቅም። ከጅምሩ ውሸትን ተላብሰው ጫካ የገቡት እነዚህ የብሄር ጠባቦች ሃገርን የሸጡ፤ ያሸጡ፤ እልፍ ሰዎችን በመግደልና በመሰወር የሚታወቁ የሌቦች ስብስብ ነበሩ አሁንም ናቸው። በቅርቡ ህገ ወጥ በሆነ መንገድ ዶላር ለዋጭና አስተላላፊ ሆነው እንደሚሰሩ መንግስት መግለጫ ሲሰጥ አንድ ነገር ትዝ አለኝ። ለእኔ ቅርብ የሆነ ባለጠጋ ከውጭ ወደ ሃገር ሊገባ እያሰበ ባለበት ጊዜ አንድ የጋራ ጓደኛችን (በአሁኑ አጠራር የትግራይ ልጅ) ገንዘብ መለወጥ ካለብህ መንገድ አውቃለሁ ይለዋል። ከዚያ በሃገር ቤት የምትኖር በአንድ የትራቭል ኤጄንሲ ውስጥ ተቀጥራ የምትሰራ ሴት ስምና ስልክ ይሰጠዋል። እሄዳለሁ ባይ ጓደኛዬ ብልህ ነውና ከልጅቷ ጋር ተደጋጋሚ ጫወታ በማድረግ ይቀርባታል። እሷም ገንዘቡን በዶላር እዚያው ተሰጣቸዋለህ። እኔ እዚህ ብሩን እሰጥሃለሁ ካለችው በህዋላ እኔም ኮሚሽን ይከፈለኛል በማለት ለማን ዶላሩን እንደሚያስረክብ ስትነግረው ጉዳዪ የወያኔ የአሰራር ሰንሰለት መሆኑ ፍንትው ብሎ ስለታየው በሌላ መንገድ ቀይሮ መሄድንም ሳያሳውቅ ሃገር እንደገባ ትውስ ይለኛል። በካናዳ፤ በአውስትራሊያ፤ በአውሮፓ፤ በአረብ ሃገሮች፤ በአሜሪካ፤ በአፍሪቃ ሃገሮች በተለይም በደቡብ ሱዳን በኩል ወደ ባህረ ሰላጤው ሃገሮች ገንዘብን ለማዘዋወር ያዋቀሩት ጥልቀት ያለው የአሰራር ስልት ገና በበረሃ እያሉ ይጠቀሙበት የነበረውን የስርቆት ብልሃት የሚያስንቅ ነው። አዲስ አበባ ውስጥና ሌሎች ከተሞች በጥቁር ገንዘብ ለዋጭ የነበሩት ብዙዎቹ የራሳቸው ሰዎች ናቸው። ለዚህ ነው መንግስት ሆነውም ሌቦች ነበሩ የምንለው።
    ግን የሃበሻው ፓለቲካ በዘር የሰከረ በመሆኑ የባህር ውስጥ ዓሳን ከመስመጥ አድናለሁ ብሎ የሚሸልል የሙታን ክምር ነው። ረጋ ብሎ ዙሪያውን ለተመለከተ አብደናል እንጂ ጤነኞች እንዳልሆን ያሳያል። እየገደሉ ሞተብን፤ እየሞቱ ገደልናቸው፤ እየሸሹ እያባረርናቸው ነው። ብቻ ወሬው ሁሉ የፈጠራ ቅንጣት እውነት የሌለበት ባለፈ የቪዲዪ ክሊፕና ድምጽ የታገዘ የውሸት ክምር ነው። የዪቱቭ ተመልካችን ለማባዛትና ፍርፋሪ ሳንቲም ለመልቀም እርቃናቸውን የሚሄድ፤ የሌለ ነገር የሚለጥፉ፤ የሰውን ሥራ የራሳቸው አድርገው የሚያቀርቡ፤ ሰው ከሰው እንዲተራመስ ሆን ብለው የውሸት ፕሮፓጋንዳ የሚነዙ እልፍ ናቸው። ሌላው ቀርቶ ስነጽሁፍ፤ ግጥምን፤ ዘፈንና ሌሎችንም ከዘር ፓለቲካ የራቁ የሳይንስና የህብረተሰብ የሥራ ስብስቦችን ሳይቀር ዘርና ቋንቋን እየጠሩ አጸያፊ ስድብ የሚሳደቡ አመድ ተሸካሚዎች ብዙ ናቸው።
    በቅርቡ እኛ ትግራዋያን እንጂ ኢትዮጵያዊያን አይደለንም እያሉ ሲፋከሩ ስሰማ አንድ ነገር ወደ ልቤ መጣ። እንዲህ እያሉ የሚፋከሩት መቀሌ ላይ ሆነው ቢሆን መልካም ነበር። ግን በየአለማቱ ስርቻ ተወሽቀውና ዜግነታችውን ለውጠው ኢትዮጵያዊ አይደለንም ቢሉን የሚያስደንቅ አይሆንም። እነርሱ በስልጣን ሲሆኑ ኢትዮጵያዊ ከስልጣን ሲወርዱ ትግራዊያን አይ ጭንቅላት የበሽተኛ ጥርቅም። ቢበዛ የእነርሱ ልጆች ትግራዊም ኢትዮጵያዊም አይሆኑም። ተወልደው ያደጉበት ሃገር ዜጎች እንጂ። ስለሆነም ይህ ሁሉ ኡኡታና ጫጫታ ጊዜ የሚሽረው የአሻሮ ሃሳብ ክምር ነው። ልብ ያለውና የትግራይን ህዝብ የሚወድ በአውሮፓና በአሜሪካ ጎዳናዎች በስማ በለው በተነገረው ወሬ ዳንኪራ ከመምታት ወይም እንባ ከማፍሰስ በሱዳን፤ በትግራይ፤ እንዲሁም በሌሎቹ የኢትዮጵያ ስፍራዎች በመዘዋወር እውነቱን ፈልቅቆ ለማውጣት ሙከራ ማድረግ በተገባ ነበር። ያ ግን አልሆነም። ያም ክተት ይላል፤ ይህም መጣሁብህ ይላል ተያይዞ ማለቅ ነው። በማህሉ የሚጎድት ትላንት ልጆቻቸውን ለወያኔና ለደርግ የገበሩ የእናቶች እናትና የእነርሱ ልጆች ናቸው። ልብ ላለው ወያኔ ለትግራይ ህዝብ አይጠቅምም። ወያኔ ከትግራይ ህዝብ ውጭ ከባህር የወጣ ዓሳ በመሆኑ ለዚያ ነው የአዲስ አበባው አገዛዙ ሲያከትም መቀሌ ሂዶ በመወሸቅ መብረቃዊ ጥቃት አድርሶ እሱም በዚያው መብረቅ በመገሽለጥ ላይ ያለው። የወያኔ ደጋፊዎች እብዶች ናቸው፡፤ ጆ ባይደን እርዳን ይላሉ። እስቲ አሜሪካ ረድታ ያቆመችው ሃገር የቱ ነው? አሜሪካ ለጥቁር ህዝብ ይገደዋል? ጭራሽ! ግን ከወያኔ ጽዋ አንዴ የተጎነጨ እድሜ ልኩን እንደ አበደ ስለሚኖር ያው ዘፋኟ አስቴር አወቀ እንደምትለን ” ራሱ በድሎ ራሱ አለቀሰ ነው”። ያው ስንላቀስ እንኖራለን እንጂ አንድ ጫፍ ላይ ቆሞ ሌላው ስርቻ ውስጥ የሚደበቅበት ጊዜ አብቅቷል። ተጋጥመን ስንተላለቅ ደስታ የሚሰማው የሰማይ አሞራ ብቻ ነው። ሰው የሆነ በሰው አስከሬን ላይ አይፎክርም፤ አይጨፍርም። ግን የዘር ፓለቲካ አይነ ስውርና ልበ ክፉ ያደርጋልና ይኽው የምናየው ይህኑ ነው። አታድርስ። በቃኝ!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share