August 2, 2021
7 mins read

ጠላት ሲሸነፍ እርግማን ያበዛል – አበበ ገላው

“እኛ ወርቅ ነን! ኢትዮጵያዊነት ወድቆ ይቀበራል! ትግራይ በአለም ፊት ታላቅ ትሆናለች!” የዚህ አይነት አሳፋሪ ፉከራና ድንፋታ የሚያሰሙት በውጭ የሚኖሩ የአሸባሪው ህወሃት ጭፍን ደጋፊዎች ናቸው። አዲስ ነገር አልተናገሩም። ጸረ ኢትዮጵያ አጀንዳቸው በሰነድ ተደግፎ ታሪክ የመዘገበው ሃቅ ነው። የህወሃት ዘረኝነት ትርፉ የለየለት ፋሺስታዊነትን መፍጠሩንም በተግባር እያየን ነው።

በአሁኑ ጊዜ የህወሃታዊያን ትግራይን እንገነጥላለን የሚል ማስፈራሪያ የቁራ ጩኸት ነው። ምን ተይዞ ጉዞ? የህወሃት መሪዎች እንኳን አገር ገንጥሎ ማስተዳደር ህጻን ልጅ ለመጠበቅ አምኖ የሚሰጣቸው ወላጅ እንደ ሌለ ይታወቃል። ህዝብን መምራት መሰረቱ ቅንነት እንጂ መግደል፣ መዝረፍ፣ ሰቆቃና ግፍ መፈጸም አይደለም። በርግጥ ከአውሬ ጋር እየተጋደለና እየተቋሰለ ለዘላለም መኖር የሚፈልግ ማንም የለም። መንገዱን ጨርቅ ያድርግላችሁ ቢባሉ ግን መልሶ ማጠፊያው ያጥራቸዋል። እውነተኛው ምኞታቸው የኢትዮጵያውን ህዝብ በበላይነት ይዘው በድጋሚ ደሙን መምጠጥ፣ መግደል፣ መዝረፍና ማሰቃየት ነው። መቼም ምኞትም ቅዠትም ፈጽሞ አይከለከልም።

መሬት ላይ ካለው እውነታ ጋር መታረቅ ተስኗቸዋል። ህወሃት ጥቂቶችን በዝርፊያና የደም ንግድ ቱጃር አድርጎ ትግራይን ግን ከስንዴ ልመና ማውጣት ባለመቻሉ ከሁሉም በከፋ ሁኔታ ህዝቡ በረሃብ ያልቃል። አሁንም የተራበው ህዝብ በርሃብና በቸነፈር ከማለቁ በፊት በቅንጦት የለኮሰውን ጦርነት አቁሞ ምግብ ለተራበው እንዲደርስ ከማድረግ ይልቅ ህጻናትን የጦርነት እሳት ውስጥ ይማግዳል። ከዚህ በሁዋላ የህወሃት ጉዳይ አክትሟል። ዳግም እራሱን የኢትዮጵያ ህዝብ አናት ላይ ሊጭን አጽሞ አይቻለውም።
በእርግጥ ህወሃት በፈጠረው መጠነ ሰፊ ሽብርና የጥፋት አደጋ ምክንያት በአሁኑ ጊዜ የኢትዮጵያውያን ዋነኛው ጭንቀት የአገራቸው የወደፊት እጣ ፈንታ ነው። በህወሃት መሪዎች እብሪትና ሴራ ምክንያት የደረሰው አላስፈላጊ የሰብዓዊና ቁሳዊ ውድመት ታሪክ ይቅር አይለውም። ህወሃቶች እኛ የበላይ ሆነን የአፓርታይድ ስርአታችንን ካላስቀጠልን ኢትዮጵያ ትበታተን በሚል አደገኛና የተሳሳተ የቁማር እሳቤ ታውረው የጫሩት ጦርነት ያስከተለው ጥፋትና እልቂት ተዘርዝሮ አያልቅም።
የጥቃቱ የመጀመሪያው ሰለባ የሆነው የአገር ዋልታና መከታው የመከላከያ ሰራዊት ነው። የእነሱን ሰላምና ድንበር ለማስጠበቅ፣ ህይወቱን በገፍ የሰዋ ሰራዊት በተኛበት ተረሸነ፣

በህይወት የተረፈውም ምርኮኛና ቁስለኛ ሆነ። እንዲህ አይነት ውለታ ቢስነትና ክህደት በታሪክ ተሰምቶ አይታወቅም።
ህወሃቶች በስሙ ዘውትር የሚነግዱበት ምስኪኑ የትግራይ ህዝብም ያተረፈው ልጆቹን በድጋሚ ለጦርነት መገበር፣ ሞት፣ ስደትና ረሃብ ነው። ለትግራይ ህዝብም ይሁን ለኢትዮጵያ ህወሃት ከተፈጠረ ጀምሮ ትሩፋቱ ነጻነት ሳይሆን ማለቂያ የሌለው ሞትና ውድመት ነው።

አንድ መዘንጋት የሌለበት ሃቅ ግን ታላቁ የህወሃት ሴራ መክሸፉን ነው። ከንቱ እቅዳቸው ቢሳካ ኖሮ ዛሬ በድጋሚ ወይ የአፓርታይድ ስርአታቸውን መልሰው የኢትዮጵያ ህዝብ ጫንቃ ላይ ይጭኑ ነበር፣ ካልሆነም ህዝቡን በዘር ከፋፍለው እርስ በርሱ በማጫረስ ኢትዪጵያን የማፍረስ ህልማቸውን ያሳኩ ነበር።
በእርግጥ ዛሬም ህወሃት እንደገና በማንሰራራት የፈጠረው ችግርና ስጋት ቀላል የሚባል አይደለም። የጦርነቱን ቀጠና ወደ አፋርና አማራ ክልሎች በማስፋት ዘረፋ፣ ግድያና ሁከት

በመፍጠር ላይ ይገኛል። መጠነ ሰፊ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ በማድረግም ህዝብን ከማሸበር፣ ከመከፋፈልና ውዥንብር ከመፍጠር አልፎ የአለም አቀፉን ህብረተሰብ በማደናገርና የኢትዮጵያን ገጽታ በማጠልሸት ላይ ትኩረት አድርገው በስፋት እየተንቀሳቀሱ ነው።

ይህ አሸባሪና ጸረ ኢትዮጵያ ድርጅት እስካልጠፋ ድረስ አስተማማኝ ሰላም በቀላሉ ሊገኝ አይችልም። ዛሬም ከኢትዮጵያ ጠላቶች ጋር እያሰሬ የአገርና የህዝብን ደህንነት አደጋ ላይ ጥላሏል። የሆነ ሆኖ ዛሬ የኢትዮጵያ ህዝብ ህወሃት የደቀነበትን የህልውና አደጋ ለመመከት ከዳር እስከ ዳር ሆ ብሎ ተነስቷል። የኢትዮጵያ ህዝብ እረጅም ታሪክ የሚያረጋግጠው ይሄንኑ ሃቅ ነው። ህዝቡ የአገሩን ህልውናና ሉአላዊነት ለድርድር አያቀርብም።

ስለዚህም ህወሃት ሲኦልም ቢሆን ግብተን ኢትዮጵያን እናፈርሳለን ብሎ መደንፋቱ ከንቱ ቅዥት ነው። ኢትዮጵያ አትፈርስም! ህወሃትም በራሱ እኩይነት ከገባበት ሲኦል ተምልሶ ኢትዮጵያ ላይ የአፓርታይድ ስርአቱን መልሶ መጫን ፋጽሞ አይቻለውም።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ “ ሰው የሰነፎችን ዜማ ከሚሰማ ይልቅ የጠቢባንን ተግሣጽ መስማት ይሻለዋል። ”   — መክብብ 7፥5 እስቲ ቆም ብለን በማሰብ  ራሳችንን እንፈትሽ ።  እንደ ሰው ፣ የምንጓዝበት መንገድ ትክክል ነውን ? ከቶስ ሰው መሆናችንን እናምናለንን ? እያንዳንዳችን ሰው መሆናችንን እስካላመንን ጊዜ ድረስ ጥላቻችን እየገዘፈ

 ለሀገር ክብርና ብልፅግና ብለን ፤ ቆም ብለን በማሰብ ፤ ህሊናችንን ከጥላቻ እናፅዳ

                                                         ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)                                                       ጥር 12፣ 2017(January 20, 2025) ጆ ባይደን ስልጣናቸውን ለማስረከብ ጥቂት ቀናት ሲቀራቸው በአሜሪካን ምድር በጣም አደገኛ የሆነ የኦሊጋርኪ መደብ እንደተፈጠረና፣ የአሜሪካንንም ዲሞክራሲ አደጋ ውስጥ ሊጥለው እንደሚችል ተናግረዋል።  ጆ ባይደን እንዳሉት በተለይም በሃይ ቴክ

አሜሪካ ወደ ኦሊጋርኪ አገዛዝ እያመራ ነው! ጆ ባይደን ስልጣን ለመልቀቅ ጥቂታ ቀናት ሲቀራቸው የተናዘዙት!!

ከነፃነት ዘገዬ የአራት ኪሎው ኦነግ ሸኔ ከቁጥር ጋር እንደተጣላ ዕድሜውን አገባደደ፡፡ ኦነግ/ኦህዲድ ዛሬም ሆነ ዱሮ፣ በቤተ መንግሥትም ይሁን በጫካ ቁጥር ላይ ያለው አቋም ምን ጊዜም ያስደንቀኛል፡፡ ደግሞም እየባሰባቸው እንጂ ሲቀንሱ አይታዩም፡፡ ጥቂት

80 ቢሊዮን ብር ስንት ብር ነው?

በላይነህ አባተ ([email protected]) መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ ምዕራባውያን የኢትዮጵያን ልጆች እያታለሉና እየደለሉ ከእምነታቸው ለመንጠቅ ሲቃጡ በ1951 ዓ ም ባሳተሙት ‘መድሎተ አሚን ወይም የሃማኖት ሚዛን ጥልቅ መጽሐፍ ሽፋን ላይ ሕዝብ ልቡናውን፣ ዓይኑን፣ ጀሮውንና

ሰው ሆይ!

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
Go toTop