blinken
ጦርነት እንኳን ለሰው ለአጠቃለይ ለምድር እንሥሣት ና እፅዋት የማይበጅ ነው ።ጦርነት ህይወት ላላቸው ፍጡራን ይቅርና ለአጠቃላይ ለምድሪቷም አንዳች ጥቅም አይሰጥም ።ለምድርም ሆነ ለነዋሪዎቿ አጥፊያቸው እንጂ አልሚያቸው ከቶም አይሆንም ። ይህንን እርባና ቢሥነቱን እያወቁ ግን በጦርነት ውሥጥና ከውጤቱ በኋላ “እናተርፋለን ” ባዮች በረቀቀ ሴራ ጦርነትን ደጋግመው ሲጭሩ ህዝብን ከህዝብ ሲያጫርሱ እናስተውላለን ። በገድሎባላይዜሽን መረህ ።
በገድሎባላይዜሽን መርህ የሚመራ ፤ በጦር ኃይል ደካማ የሆነውን አገር ሀብት መቆጣጠር በጉልበት ና በቴክኖሎጂ ተተግኖ መዝረፍ ፣ ግቡ ነውና ይህ በቀማኞች የሚመራ ጦርነት ሰብዓዊ ፍጡርን በሙሉ ለጥቅሙ ሲል እንደሚጨርስ ትላንት በሄሮሺማና ናጋሳኪ እንዲሁም በማጨው ፣ ዛሬ ደግሞ በአፍጋኒስታን ፣ በሊቢያ በየመን ፣ በሶሪያ ፣ በፍሊስጤም ና በኢትዮጵያ በትግራይ ክልል ተረጋግጧል ።
የገሎባላይዜሽኑ ፊትአውራሪ የአንድ አገር ዜጋ እርስ በእርሱ ቢጫረስ ፣ ህዝብ ቢፈናቀል ከቶም ደንታ የለውም ።ግቡ እርስ በእርስ አጫርሶ ዳርክ ኮንትኔት የሚላትን አፍሪካ መዝረፍ ነው ። ዓላማው የተፈጥሮ ሀብት እና መአድናትን ማጋበስ ነው ። …
የለምለም ና በበርካታ ማዕድን የተሞለች አገር ባለቤት ለሆነው ባለ አገሩ ፣ አፍሪካዊ ደንታ የለውም ። በዛ ማዕደን በበለፀገ አገር ለሚኖሩ ባለአገሮች ህይወት አይገደውም ። ህሊና ቢሱ በዝባዡ ኃይል እውቀት ያልዘለቀው ፣ ተርታው ህዝብ በሙሉ አልቆ ፣ ጥቂት ሆዳም እርሱን አገልጋይ የሆኑ ዜጎች በምድሪቱ ቢተርፉለት ሥለሚመርጥ ” በመተላለቃችሁ ግፉበት ፤ በርቱ! ” እያለ የትጥቅና ሥንቅ አቅርቦት በገፍ ያቀርባል ። የራሱን ብዝበዛ ለማፋጠን የሚረዳውን የጦር መሣሪያ ማምረቻ በሰፊው ሥለገነባም ፣ የተለያዩ እጅግ የዘመኑ የጦር መሣሪያዎችን በማምረት እነዚህንም መሳሪያዎች በድብቅና በግልፅ ከሆድ የዘለለ ህልም ለሌላቸው ፣ አገር አፍራሽ ልሂቃን በመስጠት የአንድ አገር ዜጎች እርስ በእርሳቸው እንዲጨራረሱም ያደርጋል ።
የሰለጠነው በገሎባላይዜሽን መርህ ተቀሳቃሹ እና መሣሪያ አምራቹ አገር ፣ ለጥቅም ሲል መፋጨት ፣ መጋደል የጀመረው በራሱ እና በወረራ የራሱ ባደረገው አገር ነው ። የሮማ ፣ የኦቶማን ኢምፓየርን ና እና የአሜሪካንን አፈናቃይነትና የግዛት ወረራ ከታሪክ አንብቦ መረዳት ይህንን እውነት ለመመሥከር ያስችላል ። እያንዳንዱ አውሮፓዊ ትላንት ምን እንደነበር በመንገር የዛሬው የብዝበዛ ወረራ ከዛ ተመክሮ የመጣ መሆኑንን በተጨባጭ ያስረዳል ።
ፈረንሳይ ና እንግሊዝ በአዲሲቱ አሜሪካ ውሥጥ ለዓመታትት ተዋግተዋል ።ሌላ አገርን በጦርነት የመያዝ ሃሳብ ለመጀመሪያ ጊዜ የተወሰደው ከዛ ይመሥለኛል ።ከአፍሪካ ሠራተኛ እጆችን በኃይልና በጭካኔ ጭምር በማጋዝ ። ጦርነትን በሴራ መልክ በትብብር በማከናወን የተጀመረው በአንደኛው ዓለም ጦርነት መሆኑንንም አትርሱ ።የአውሮፓውያኑ የእርስ በእርስ ጦርነት በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ደግሞ እጅግ የባሰ ሆነ ። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የጦር መሣሪያ አምራች ና ባለቤት የሆኑ አገሮች ፊታቸውን ወደአፍሪካ አዞሩ።
የ19ኛው ክ/ዘ የለየለት የቅኝ ግዛት አገር የመያዝ እሽቅድድም አውሮፓውያን በአፍሪካ አካሂደዋል ። ቤልጄም እንግሊዝ ፣ ፈረንሣይ ፣ጀርመን ኢጣሊያን አፍሪካን ለመቀራመት በአፍሪካ ምድር ተርመሥምሰዋል ። የአፍሪካን ህዝቦችም በጎሣ እየከፋፈሉ አጫርሰዋል ። ለአንዱ መሣሪያና ጥይት በመሥጠት ለአንዱ በመንፈግ የአንድ አገር ህዝብን አፋጅተዋል ። ቂም እንዲያያዝም አድርገዋል ። እነሱ በአንደኛውና ሁለተኛው ዓለም ጦርነት የተጨራረሱትን ያህል አፍሪካዊያንን በወረርሺኝ ፣ በኤችአይቪ ፣ በችጋር ፣ በቸነፈር ወወተ ጭምር እንደቅጠል እንዲረግፍ አድርገዋል ።
በአንደኛውና በሁለተኛው ዓለም ጦርነት 65 ሚሊዮን የሚጠጋ ሰው እንደሞተ ይገመታል ። ከፍተኛው ሞት የተመዘገበው ማለትም 56.4 ሚ ( ከ1939_1945 እኤአ ) በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ሲሆን በአንደኛው የዓለም ጦርነት ( 1914_1918 ዓ/ም ) 8.5 ሚ ህዝብ ነው ያለቀው ።
ዛሬ ደግሞ በገድሎባልአይዜሽን ( ግሎባላይዜሽን ) ዘመን ፣ የአፍሪካን ህዝብ እርስ በእርሱ በማጫረስ ፣ ሁለንተናዊ ድህነት እንዲወራው በማድረግ ፣ ለእለት ጉርሱ ብቻ በማሰብ ኗሪ እንዲሆን በኬሚካል የታሸ ሥንዴና ዱቄት በማቅረብ ፣ ጥቂት የማይባሉ የአፍሪካ ዜጎች ለአገረቸው ደንታ እንዳይኖራቸው በማድረግ የ19 ክ/ዘ ቅኝ ገዢዎቻችን በእጅ አዙር ዛሬም ጀግኖቻችንን በመግደል በጉልበታቸው የእጀራ አባት ሆነውብናል ። ( ወዳጄ ግድሎባላይዜሽን ማለት ትርጉሙ ይኸው ነው ።)
በጦር መሣሪያቸውና በሀብታቸው በመመካት ዛሬም ብዝበዛቸው እንዳይቋረጥ በብርቱ በመፈለግ፣ አውሮፓ ና አሜሪካ አፍሪካን ሠላም አልባ ና የአምባገነኖችና የሽብርተኞች መፈንጫ እያደረጓት ነው ። ይህም ብቻ አይደለም ሞት ምን መሆኑንን ከቶም የማይገነዘበውን ፣ የእለት ምግቡን ካገኘ ያለአቅሙ መሣሪያ ተሸክሞ ለጦርነት ለመማገድ ወደኋላ የማይለውን ፣ በድህነት ሰበብ የሆዱ እሥረኛ የሆነውን ለአቅመ አዳም ያልደረሰውን ዕድሜው በ12 እና በ15 ዓመት መካከል የሚገኘውን ፣ በሃሺሽ በማጦዝ ዛሬ ና አሁን የአፍሪካ ወጣቶች በከንቱ እንዲያልቁ እያደረጉ ነው ።
ዛሬ በአገሬ በኢትዮጵያ ይህ ግፍ በአውሮፓ ና በአሜሪካ ተባባሪነት ፤ በአሸባሪው ህወሃት ፊት አውራሪነት በገሃድ እየተፈፀመ ነው ። ይህ ግፍ ደግሞ ቢዘገይም ዋጋ ያሥከፍላቸዋል ። የአውሮፓና የአሜሪካ መንግሥታት ለብዝበዛ ሲሉ የሰሩት ግፍ እንሆ ዛሬ ዋጋ እንደሚያሥከፍላቸው እያየን ነው ። የሰሞኑ ጎርፍ ና ውድመትም የእግዚአብሔር ልምጪን ኃይለኝነት እያሳየን ነው ። እኛ ኢትዮጵያዊያን ከጥንት እስከዛሬ የምንመካው በፈጣሪያችን በእግዚአብሔር ነውና ጠላቶቻችን በፈጣሪ ልምጪ እንደሚሸነቆጡ እናምናለን ።
እኛ ኢትዮጵያዊያን የምንመካው በፈጣሪያችን ነውና ፈጣሪያችን እግዚአብሔር ከቶም አያሳፍረንም ። እናም ገድለውን በአገራችን ላይ አዛዥ ናዛዥ እንሁን የሚሉትን የምእራቡን ዓለም ና የአሜሪካ ቱጃሮችን የድፍረትና የጭካኔ ተግባር እጃችንን አጣምረን አንቀበለም ። ተላንትም አልተቀበልንም ። ዛሬም አንቀበልም ። አዎ ገድሎባላይዜሽንን አንቀበልም ።