ገልጽ ጦርነቱ አሁን ነው የጀመረው!  – አምባቸው ደጀኔ

“በኢትዮጵያ ውስጥ በቅርቡ ለሚከሰተው የሰው ዘር ዕልቂት ተጠያቂው የግራኝ አህመድ አቢይ መንግሥት ነው” ለማለት ቃጥቶኝ ነበር፡፡ ግን ግን ይህ ለላንቲካውና በልማድ የሚነገረው ለአንድ ጥፋት ወይም ውድመት ኃላፊነትንና ተጠያቂነትን የሚወስድ አካል ወይም ግለሰብ የማፈላለግ ጉዳይ አሁን አሁን ጠቀሜታው እስከዚህም ነው፡፡ ጉዳትን ቀድሞ መከላከል እንጂ አንድ ኪሣራ ከደረሰ በኋላ ኃላፊነት የሚወስድን መፈለግ ከጉንጫልፋነት አይዘልም፡፡ የሩዋንዳን ዕልቂት ያስከተሉት አካላት ምን ሆኑ? ምንስ ቢሆኑ የተገደሉትን ዜጎችና የወደመውን ሀብት ንብረት መመለስ ቻሉ ወይ? ሂትለርና ሙሶሊኒ፣ ኢዲያሚንና ቦካሣ፣ አልቃኢዳና አልሻባብ… ያንን ሁሉ የሰውና የንብረት ውድመት አስከትለው ምናልባት ከተራ ሞት ወዲያ ምን ከባድ ቅጣት ደረሰባቸው? … ኃላፊነት የሚወስድ ወገን ቢመጣ በመተከልና በወለጋ፣ በሐረርና በአርሲ፣ በሻሸመኔና በጋምቤላ፣ በባሌና በሌሎች ብዙ ቦታዎች ላለፉት 30 እና 40 ዓመታት በማንነታቸው ምክንያት በአክራሪዎች የታረዱ ዜጎችን ሕይወት ይመልሳል ወይ? ስለዚህ ዋናው ቀድሞ መጠንቀቅ ነው፡፡ ጥንቃቄ ባለማድረግ እጅን አጣጥፎ መቀመጥ ለሰይጣኖች ምቹ ያደርጋል፡፡ በኦህዲድ/ኦነግ እየተደገሰልን ያለው ድግስ እጅግ ከባድ ነው!!

የትናንትናው የብልግና ፓርቲ ሰልፍ በተለይ በአማሮች ላይ የዘር ማጥፋት ወንጀል የታወጀበት ሰልፍ ለመሆኑ እማኝ መቁጠር አያሻም፡፡ እንደዚያ ያለ ሰልፍ በዓለም የመጀመሪያው ነው፤ ለሞኝ ግን ምንም ላይመስል ይችላል፡፡ በነግራኝ አቢይ ወሽመልስ አህመድ አብዲሣ የሚመሩት አክራሪ ኦሮሞዎች እውነትም ዙሩን እያከረሩት ነው፡፡ ከወያኔዎችም ብሰው አማራን ለማስፈጀት የመጨረሻውን ቀይ መስመር አልፈዋል፡፡ ይህም በታሪክና በእግዚአብሔር እየተመዘገበ ነው፡፡ ከወፈሩ ሰው አይፈሩ ነው፤ በእርግጥም ጥጋባቸው ገደብ አጥቷል፡፡ “ነፍጠኛ ከክልላችን ይውጣ” ብሎ ማስፎከር “አማራን በያለበት ፍጅ” እንደማለት ነው፡፡ ኦነግ ሸኔን ለይምሰል በመናጆነት አብሮ አስቀምጦ ሰላማዊ ታጋዮችን መወንጀልና እንዳሰሩ ማቆየት ልበድፍንነት ነው፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ደም እና አጥንት የተከፈለውም ሆነ እየተከፈለ ያለው፥ በነፃነት ለሚቋጨው ኢትዮጵያዊነት ነው። የቀደመ፤ ቀላል ስሌት

ሰልፉ ጥሩ ምልክት ነው፡፡ የነፃነት ዘመን ቀርባለች፡፡ የመከራ ቀምበር ሊሰባበር ትንሽ ጊዜ ቀርቶታል፡፡ እነዚህ አክራሪዎች ደም አስክሯቸዋል፡፡ የዘረኝነቱ አባዜ አሳብዷቸው የሚሠሩትን አጥተዋል፡፡ በአንድ በኩል ጥሩ ነው፡፡ በሌላ በኩል ጥሩ አይደለም፡፡ ሟች ይዞ ባይሞት ጥሩነቱ ባመዘነ፤ ግን ብዙ ነገሮች እንደሚታሰቡት አይቀሉም፡፡ ያለ መስዋዕትነት ድል አለመኖሩ ተዘውትሮ የሚዘከረውም ለዚህ ነው፡፡ ክፉ ቀን እየመጣ ነው፡፡

የአዲስ አበባ ህዝብ በተለይም ወጣቱ እንደከብት እንደሚነዳው የገጠር ቄሮ በጭካኔና በዕኩይ ተግባራት ተኮትኩቶ አላደገም፡፡ ገር ነው፤ ሩህሩህ ነው፡፡ በዘርና በጎሣ፣ በሃይማኖትና በባህል ልዩነቶች ተነድቶ አንዱ ሌላውን አይጎዳም፡፡ ያደገበትና ያሳለፈው ማኅበረሰብኣዊ መስተጋብር ክፉ ነገርን በማንም ላይ እንዲያደርግ አይፈቅድለትም፡፡ ከዚህ ተቃራኒ የሆኑት አክራሪ ወገኖች ይህን የአዲስ አበባ ህዝብ ጠባይ በመረዳትና “ምንም ጉዳት አይደርስብንም” ብለውም በማሰብ አዲስ አበቤን ለማፈን እየተራወጡ ነው፡፡ በሌላ በኩልም ዝምታውንና ትግስቱን ይፈራሉ፡፡ ስለዚህም ፀጥ ረጭ አድርገውና ወደ ግዑዝነት ለውጠው ቀጥቅጠው ሊገዙት ይጥራሉ፡፡ አንድም ወኪልና ብሶቱን የሚተነፍስለት አለሁህ ባይ እንዳይኖረው ቀን ከሌት ይማስናሉ፡፡

ዘረኝነት መጥፎ ነው፡፡ ዘረኛ ሰው “ከነሱ ደግ የኔ ክፉ ይሻለኛል፤ ከነሱ ሩህሩህ የኔው ዐረመኔ ይበልጥብኛል፤ ከነሱ ቸር የኔው ንፉግ ይሻለኛል፤…” በሚል እሳቤ የታወረ የስንኩል አእምሮ ባለቤት ነው፡፡ ይህን እውነታ በስዬ አብርሃ ወራዳ ተፈጥሯዊ ባሕርይ ማረጋገጥ ይቻላል፡፡ በጻድቃን ገ/ትንሳይ ብልሹ ጠባይ መገንዘብ ይቻላል፤ በአበበ ተ/ሃይማኖት ወልጋዳ ሥነ ተፈጥሮ ማየት ይቻላል፤ ከነሽመልስ ዕብሪት መረዳት ይቻላል …፡፡ ዘረኝነት መጥፍ ክርፋት ነው፤ ህክምና የሌለው ግማት ነው፤ ጥምባቱም የሽዎች ኪሎ ሜትሮች ርቀት አይገድበውም፡፡ ይህን በሽታ በድል የሚወጡ ቁጥራቸው እጅግ አነስተኛ ነው፤ ከምፈልገው አካባቢ ቁጠር ብባል አሥር ሰው የምደርስ አይመስለኝም፡፡ የዘርን አጥር ዘልሎ መውጣት የተራራ ያህል ከባድ ነው፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ከነመላኩ ፈንታ በኋላ የቆመ መርከብ የሆነው ፀረ - ሙስና ኮሚሽን

የአዲስ አበባ ሕዝብ ይጠንቀቅ፡፡ ኢትዮጵያውያን እንጠንቀቅ፡፡ የተደገሰልን መከራ ከባድ ነው፡፡ የመንግሥትን በትረ ሥልጣን የያዘ አካል ሙሉ ስፖንሰር ያደረገው የዘር ፍጂት በየበራችን ቆሟልና ወደ ፈጣሪ እንጸልይ፡፡ አንሞኝ፡፡ የሃይማኖት አባቶችና እናቶች በርትታችሁ ጸልዩ፡፡ ጥጆችንና ሕጻናትን ከጡት በማገድ ጭምር ወደላይ እንጩህ፡፡ እግዚአብሔር ቅጣቱን ቀለል እንዲያደርግልን ምህላና ሱባኤ እንግባ፡፡ እስካሁን ከታረደው ወደፊት የሚታረደው እጅግ ይበዛል፤ ጨለማው እየከፋ ነውና እንንቃ፡፡ የድንቁርና መብዛት ክፉ ቀንን ሸፍኖ አያስቀርምና ልባሞች እባካችሁን የተቻላችሁን ሁሉ አድርጉ፡፡ ቀን የሰጣቸው ሰዎች ኢትዮጵያን ይዘው እንዳይጠፉ ሀገራዊ ምህላ ይደረግ፡፡ ይህን የምለው ውድመቱ የትንሣኤውን ትሩፋት እንዳያደበዝዘው እንጂ ነጻነታችን የማይቀር ነው፡፡ ሩዋንዳ፣ የመን፣ ዩጎዝላቪያ፣ ሶማሊያ፣ … በመንግሥታችን አማካይነት ወደሀገራችን ተጋብዘው መጥተው እንደሚከፋፈል የሸቀጥ ዕቃ በቤተ መንግሥታችን ተከማችተዋል፡፡ በሻሞ ልንቀራመታቸው የኦነግ/ኦህዲድን ፊሽካ ብቻ እየተጠባበቅን ነው፡፡ ዕድሉ ያለው ይህን ወጥመድ ያክሽፍ፡፡ ዘንዶው ሥራውን እየሠራ ነው፡፡ ለጊዜው ሁሉን ተቆጣጥሯል፡፡ ግን ይከሽፍበታል፡፡ …

 

5 Comments

  1. ለነገሩ ዘ ሃበሻም አስተያየት ማስተናገድን የተወ ይመስላል። ግራም ነፈሰ ቀኝ የእኔ አስተያየት እንሆ። እውቁ ደራሲ ስብሃት ገ/ሄር እንዲህ ብሎን ነበር። “የምንኖረው በውሸትና በእውንት መካከል ነው”። ፓለቲካ የቆሻሻ ክምር ውሾች በተገኘው ሽርፍራፊ እንደሚጣሉት አይነት ነገር ነው። ማርክስና ኤንግልስ መደብ አልባ ህብረተሰብ ለመፍጠር የተፋተጉበት ያ የሶሻሊስታዊ እይታ አሁን የጎጥና የዘር የቋንቋ ተገን አበጅቶ አንድ አንድን ሲኮንን ከጣት እጣት ይበልጣል እያለ ሲማታ መስማትና ማየት ያማል። ግን የት ይደረሳል? ልብ ላለው እኮ የፓለቲካ እሽክርክሪት ውስጥ ነው ያለነው። መስሎን ለውጥ አዲስ ነገር እንላለን እንጂ! ይህ ሁሉ የቀኑን ጥላ እንደመከተል እንጂ ለውጥ የለም። ቆዪ አትቆጡኝ ላስረዳ። የቆመን እያፈረስን ሌላ ስንተክል ነው የኖርነው። የንጉሱን ዙፋን በማታለልና በሸፍጥ ፈንቅሎ ንጉሱንም ገድሎና አስገድሎ ቢሮው ስር የቀበራቸው ያ ስብዕና የጎደለው የደርግ አሰራር 60 ዎቹን ጉድጓድ ሲከትና እልፍ ወጣቶችን በቀይ ሽብር ሲገድል ሲያጋድሉት የነበሩት የወያኔና የሻቢያ የውስጥ ሰዎችም ጭምር ነበሩ። ቆም ብለን የ 1953 የእነ ጄ/መንግስቱ ንዋይን መፈንቅለ መንግሥት ስንመለከት ደግሞ የሚያስተምረን ነገር አለው። ያኔ ድሮ ገና ሰው ደግ እያለ ማለት ነው መፈንቅለ መንግስት ተብሎ ሰዎች ሲረሸኑ የታህሳስ ግርግሩን ለማብረድ ሽርክና ቀይረውም ሆነ ከሞት ተርፈው ዘጥ ዘጥ ያሉት እፎይታ የተሰማቸው ጄ/ መንግስቱ ንዋይ አንገቱ በገመድ ሲታነቅ ነው። ያኔ ቆመው ያጨበጨቡ፤ የገደሉ፤ ንጉሱን ከስልጣናቸው በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ እንዲሰነብቱ የረዱትን ነው ደርግ በማርሽ መገደላቸውን ለህዝብ ያስታወቀው። ይህ ነው በወረፋ መገዳደል የሚባለው። አንድ ልጨምርበት። ደ/ች በላይ ዘለቀ ወንበዴ ነህ ተብሎ አንገቱ ላይ ገመድ ሲገባ ቆመው ካዬት መካከል አንድ ጄ/መንግሥቱ ንዋይ ነው። ታዲይ ይህ ሁሉ ሰው የሚገዳደለው ግን በህዝብ ስም ነው። ለነጻነት፤ ለእኩልነት፤ ለሰላም ታምቡር እያስመቱ ነው።
    አሁን ያለውን ፍትጊያ ስንመለከት ደግሞ ያልታሰበ ነገር ተፈጥሯል። ወያኔ ተነኮሰ በተባለው ግፍ ሰዎች ከዚህም ከዚያም ይሞታሉ፤ ይራባሉ። ተረጋግቶ ለተመለከተው የሃበሻው ፓለቲካ ውሃ መልስ ውሃ ቅዳ አይነት ነገር ነው። መቅጃውን እቃ እንጂ ውሃነቱን የማይለውጥ መንቻካ ፓለቲካ። ቢያኝኩት የማይዋጥ። አሁን አካኪ ዘራፍ እንዲህ አርገን እንዲህ ሰርተን እያሉ የሚደነፉት ወያኔ እባብ ነው ራሱን ቢመታ በጅራቱ ብቻ ቆሞ ይሄዳል። በምንም ሂሳብ ወያኔ ሞተ ማለት አይቻልም። በተግባርም ሆነ በአፍ ያው የተካኑበትን የተንኮል ሥራ ሲፈጽሙና ሲያስፈጽሙ ዘመን እንሻገራለን። ለዚያውም ከኖረን ነው። በውጭ ሚዲያ ስለ ትግራይ ህዝብ መራብ፤ ስለ ሴቶች መደፈረ (ይታያችሁ ወያኔ እያለ ሴቶች በመቀሌ ሰልፍ አርገው ክፉኛ ተዘልፈዋል)፤ በትግራይ ስለሚደረግ ግድያ በየጊዜው ሲጻፍና የአረብ ሚዲያዎች በተለይም አልጀዚራና እንዲሁም በዪቱብ ማይ ቪውስ ኦን ዘ ኒውስ የሚል ህንድ መሳይ ነገር ከኩበት ለቀማ ሲመለስ የሚያሰራጨውን ለሰማ ሃገሪቱ እረፍት ጭራሽ አይኖራትም። ይህ አይነቱ የውሸት ጋጋታና የውጭ መንግስታትና የአረብ ሰውር ሴራ ከእኛ ተንኮል ጋር አብሮ ሃገርን እያፈረሰ እንዳለ ዓይነ ሰውር ሰው ይረዳል፡፤
    አሁን ለጠ/ሚሩ ድጋፍ ተብሎ በተደረጉ አንዳንድ ሰልፎች ላይ የሚነገረው ነገር ሁሉ ቀነኞቹ እኛ ነን እንዳሻን እንሁን እንደማለት ነው። በምን ሂሳብ ነው አብንና ኦነግ ሼኔ ተግባራቸው የሚገናኘው። ግን ግንፍል ፓለቲካ የት እንደሚፈስ ተናጋሪውም ሆነ አድማጩ አያስተውልም። ያው እንደ እሳተ ገሞራ ፍንዳታውን እንጂ የእሳቱን ፍሳሽ ሰው ከስሩ አያይም። ያሳዝናል። ጦርነቱ አሁን ተጀመረ የሚለውን እንኳን አላምንበትም። ከተጀመረ ቆየ። መጠየቅ ያለብን መቼ ነው መግደልና መገዳደል የሚያቆመው ቢሆን እንዴት መልካም ነበር። በቃኝ!

  2. ድምፅን በማፈን ጦርነት ስለማስኬድሳ?
    ምድሪቱ ካፈለቀቻቸው ታላላቅ ሰዎች አንዱ የሆነው Giordano Bruno፣ እውነት ተናግርሃልና በእሳት ተቃጥለህ መሞት አለብህ ብለው የቫቲካን እንኩዚቶሮች በእርሱ ላይ የጣሉትን ፍርዱን ሲነግሩት እንዳለው፣ “ይሄንን ፍርድ ለእኔ ስትነግሩኝ እኔ ከሚሰማኝ በላይ በፍርሃት እየተንቀጠቀጣችሁ ነው” የሚለውን ኮሜንት ጣለባቸው:: (Ihr sprecht mir das Urteil mit großerer Furcht als ich es empfinge) የ’DC ህልመ ጭሰኝነት አምሃራስ ቅራቅንቦ ፕሮፓጋንዳ ማሺነሪ ዘ-ሓበሻም፣ እኔ ለኢትዮጵያ ጭቁን ህዝቦች ሶሊዳርትየን ለማሳየት የምፅፈውን ኮሜንት ካንባብያን ስትደብቅ፣ እኔ ከሚሰማኝ ብስጭት የበለጠ ብስጭት እየተሰማህ ነው:: ለምን ቢባል፣ እኔ አንተ ከምትኖርበት አለም በላይ ከፍ እና መጠቅ ብዬ እንደምኖር ከኮሜንትዎቼ ስለምትገነዘብ ነው:: ሸፍጠኝነት ቆልፎ የያዘህ ልበ ድፍን ባትሆን ኖሮና፣ አንዱ ከአንዱ በመማማር ብታምንና የግልፅነት ተከታይ ብትሆን ኖሮ፣ባባባሎቼ ባልተበሳጨህና የዲያሎግ ባላባትም ሆነህ በተገኘህ ነበር::
    Da du doch ein Gott- und Vernunftlose Kerl bist (Since you’re a godless and senseless guy), የተሻለን ቀን ብቻ ያምጣልህ::

    • የኔ ዘርዓ ያዕቆብ፥ ምን ማለት እንደፈለግህ ለመረዳት ፈልጌ አሥተያየትህን ደጋግሜ ባነብም ሊገባኝ አልቻለም። እሥኪ አብራራው

  3. (Since you’re a godless and senseless guy) የሚለውን አንተ ነህ የጨመርከው እንጂ እኔ አላስቀምጥኩትም ነበር! መተርጎሙ ክፋት የለውም፣ ግን ተርጓሚው አንተ እና ኮምፑተሩ ለመሆናችሁ ማስመልከት በተገባህ ነበር:: ከዚህም በላይ ደግሞ በየቀኑ 30 ቫይረሶችን አትላክብኝ::

  4. ውድ ግሩም፣
    ባጠቃላይ በኢትዮጵያ ህብረተሰብ ዘንዳና፣ በተለይም እዚህ ድረ ገፅ ዘንዳ fairness የሚበል ነገር ጠፋ፣ ዝቃጭ ወገናዊነት ብቻ ነው የሚሽቀረቀረው፣ ክሪቲካል አስተሳሰቦች ተቀባይነት የላቸውም፣ everything is non communicative, and only instrumental, ከዚህም በመነሳት ነው ሁሌ ስርአት በተለወጠ ቁጥር ሁናቴዎች ወደ ከፋ እንጂ ወደ ተሻለ የማይሸጋገሩት፣ ዛሬ ነገን አርግዛ ትጓዛለች፣ የዛሬ ሸፍጠኛ ዝግጂቶች የነገን ክፉ ስርአቶችን ይወልዳሉ ወወዘተ ነው ለማለት እየሞከርኩኝ ያለሁት!
    አባባሌ ባጠቃላይ ላይ ካሉት ሶስት-አራት መስመሮች ለማስመልከት እንደሞከርኩት ሲሆን፣ በጭብጥ ግን ይሄ ድረ ገፅ በተለይ በትግራይ ላይ የፈለገውን ያስነብብና፣ እንዲሁም ፀረ ትግራይ ሀይሎችንም በትግራይ ላይ ያስጨፍርና ግን የሆኑ የትግራይ ተወላጆች አስተያየታቸውን ሲሰነዝሩ አያስነብብም፣ በእንደዚህ በበለጠ ትግራይን ከደረሰው ካታስትሮፊ የባሰ በደል ሊያደርስባት የሚችል ይመስለዋል፣ የእርሱና የብጤዎቹ መደዴው አስተያየት ብቻ አገልግሎት ያለው ይመስለዋል፣ አክሽን ረአክሽን ለመኖሩ አይገባውም፣ ከዛሬ ነገ ታሪካዊ ለውጦች ሊመጡ እንደሚችሉ እንደማሰብ ይልቅ፣ ራሱን እንደ ብቸኛው ባለሃቅ የሚሆን ይመስለዋል:: ስለ ሌላኛው ግን ምንከረደሽ ነው፣ አንዱ ራሱን እንደ የዚህ ድረ ገፅ ዋና ተዝናኝ አድርጎ የሚወስደው አንዴ እንዳለው (ስሙ ግድየለም ይቆይልን) ጭራሽ ትግሬዎች አትምጡብን ብሎ ደደብነቱን ግልፅ አድርግዋል፣ እንዴት ይሆናል፣ እርሱ በትግራይ ላይ ሊጨፍር፣ ግን ትግሬዎች ላይመጡበት?
    በበለጠ እንግባባ ዘንዳ አርአያነት ያላቸው ሰዎች የድያሎግ መግባባያ መድረኮችን ሃላፊነት መቀበል ይኖርባቸዋል::
    ቸር-ቸሩን

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share