መታሰቢያነቱ ፦ በዓለም አቀፍ ሴራ ከቀዬአቸው ለሚሳደዱ የኢትዮጵያ ልጆች (አሁንገና ዓለማየሁ)

የመስተባርር ድግምቱ
ጉሙዝ አራጅ ሆኖ
አገው ታራጅ ቢሆን በገዛ መሬቱ
አሳራጁ ሰነድ ያ ሕገ መንግሥቱ
መለሰና ሌንጮ የጻፉት ሁለቱ
የውቅያኖስ ጆፌ እያያቸው ንሥር
በአቆርዳት በረሃ በኢሳያስ ጥላ ሥር።
….
ትግሬ አሳዳጅ ሆኖ
አማራ ቢሳደድ ከገዛ መሬቱ…
እስላም አራጅ ሆኖ
ክርስትያን ቢታረድ በገዛ መሬቱ…
ወንድሜ
መልሰው!
መላልሰው! አንድ ነው ድግምቱ
በሎንዶን ብራና የስታሊን ምትሐቱ
“አብርርልኝ! ልምጣ” ነው ሚሉት ቃላቱ።

መታሰቢያነቱ ፦ በዓለም አቀፍ ሴራ ከቀዬአቸው ለሚሳደዱ የኢትዮጵያ ልጆች

ተጨማሪ ያንብቡ:  አልቃሾ - በመኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ 

2 Comments

  1. አገር በ ህብረት እንደሚያድግ፣ የማያውቁ መሃይሞች
    በ በረሃ ተሰባስበው ተማማሉ፣ ሊለያዩ የ ኢትዮጵያን ልጆች
    ተመኝተው ሊሆኑ የ መንደር ንጉሦች
    ደግሞም ሊያበለጽጉ የእነሱን ወገኖች።
    ምኞታቸው ተቃንቶ አገር አጠፉ
    ሚሊዮኖችም እንደ ጤዛ ረገፉ።
    በ ረሃብ እና ጥይት ስንቱ ተቀጠፉ
    በ ጎሰኝነት በሽታ በተጠለፉ።
    እጅግ ብዙ ጉዳት

  2. አገር በ ህብረት እንደሚያድግ፣ የማያውቁ መሃይሞች፤
    በ በረሃ ተሰባስበው ተማማሉ፣ ሊለያዩ የ ኢትዮጵያን ልጆች፤
    ተመኝተው ሊሆኑ የ መንደር ንጉሦች፤
    ደግሞም ሊያበለጽጉ የእነሱን ወገኖች።
    ምኞታቸው ተቃንቶ አገር አጠፉ፤
    ሚሊዮኖችም እንደ ጤዛ ረገፉ።
    በ ረሃብ እና ጥይት ስንቱ ተቀጠፉ፤
    በ ጎሰኝነት በሽታ በተጠለፉ።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share