ኦሪት ዘፍጥረት ኦሮሞ ከውሃ ነው የመጣው! የእርግማን ትውልድ! – ሰርፀ ደስታ

  • ኦሮሞ ከወሃ ነው የመጣው የሚለው ከአባ ባሕሬ መጻፍ ያነበብኩት ሳይሆን የዛሬው የኦሮሞነት ልክፈት ካህን የሆነው ምሁር ነው የተባለ …. ነው ያለው፡፡ አባ ባሕሬ ከባሕር ወጣ ያሉበት አግባብማ ለዛሬው የማይረባ አእምሮ ትውልድ አይገባውም፡፡
  • መሳይ ስለሸኔ ኦነግ የጠየቀው ተጠያቂ በኃይለስላሴ ጊዜ የገበሬ ልጅ ከ4ኛ ክፍል በላይ መማር አይፈቀድለትም ማለቱ ብቻም ሳይሆን እስከዛሬ እንደዚህ ማሰቡ እጅግ ገርሞኛልም አሳሳቢም ነው፡፡ ነገ አንዱ ወይም ተናጋሪው ሌላ መርዝ ታሪክ ይዘውበት ይነሳሉ፡፡ኃይለሥላሴ ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ትምህርት መሳካት ከጠረፍ ገጠሬዎች ሳይቀር ራሳቸው እያመጡ ብዙዎችን አስተምረው ዛሬ ትልልቅ ቦታ ላይ የደረሱ አሉ፡፡ ውለታቢስ ስለሆነ ስለተደረገላቸው አያወሩም፡፡ ለነገሩኮ ይሄ ሁሉ ፖለቲከኛ ነኝ እያለ እስከዛሬም መዥገር ሆኖ የኖረበት ያ የ60ዎቹ ትውልድ ከገጠር ሆነ ከከተማ  አስተምረው ዩኒቨርሲቲም አድረሰውት ነበር፡፡
  • በወያኔና ኦነግ ሕግ እየተገዛንና የአባቶቻችን ደምና አጥንት የታተመበት ሰንደቅ ዓላማ ላይ ሰይጣናዊ ምልክት አሁንም እየተጠቀምን ስለኢትዮጵያ ሠላም ማሰብ ዘበት ነው፡፡ መጀመሪያ የወያኔና ኦነግ ሕግ ይጣል፣ ለጠላት የሚያስፈራው የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ወደነበረበት ይመሰለስ፣ሸዋ የኢትዮጵያ ሕዝቦች ሁሉ መዕከል እንደመሆኑ ራሱን የቻለ አስተዳደር ይሁን፡፡

እግዚአብሔርን ለማወቅ ባልፈለጉት መጠን የማይገባውን ያደርጉ ዘንድ ለማይረባ አእምሮ አሳልፎ ሰጣቸው ይላል ታላቁ ፈላስፋ፡፡  ከላይ በርዕስነት የተጠቀምኩት የእኔ አደለም የኦሮሞ ቁቤ ትውልድ ካህንና ትውልድን በአእምሮ እየገደለ ያለው የተናገረው ነው (ከታች በሊንኩ ስሙት፤ ብትችሉ ባትስቁ ጥሩ ነው ልክፍት ስለሆነ)፡፡ ርዕሱንም የወሰድኩት ሰዎች ከለጠፉት ነው፡፡ መጀመሪያ ኦሮሞ ከውሀ ወጣ የመጀመሪያው ፍጥረት ኦሮሞ ነው ይልሀል፡፡  መቼም ወደው አይስቁ ሆኖብኝ እንጂ ነገሩ የሚያስቅ ጉዳይ አደለም፡፡ እርግጥም ነው አያስቅም መርዛቸወን እንዲህ ባለ ሁኔታ እየዘሩ ብዙ ተከታይ አፍርተዋል፡፡  ሰዎች አእምሮአቸው ካልሰራ በምን ያስባሉ? ለማንኛውም ሁሉም ይይና ወይ ይሳቅ ወይ የዘን ከታች ያለውን ሊንክ ይዩት፡፡

https://www.facebook.com/girma.biru2/videos/3138159362958036

በነገራችን ላይ ኦሮሞ የሚባል ቃል ለብዙ ሰው ብዙ ታሪክ ያስቆጠረ ሊመስለው ይችላል፡፡ ዛሬ ማመን ሊያስቸግር ይችላል ከዛሬ 30 ዓመት በፊት አብዛኛው ኦሮምኛ ተናጋሪ ኦሮሞ ተብሎ አይጠራም ነበር፡፡ ከዛሬ 50 ዓመት በፊት ከወለጋ በቀር ይሄን ቃል የሚያውቀውም አልነበረም፡፡ ከዛሬ 200 ዓመት በፊት ኦሮሞ የሚባል ቃል ከነጭርሱም አልነበረም፡፡   እንደሚመስለኝ በወለጋ ሚሲዮናውያን በሚያስተምሩበት ወቅት የተፈጠረ ቃል ነው፡፡ እንደማስበው በወለጋ የዛሬው ኦሮምኛ ቋንቋ ተናጋሪዎች ነጮቹን ኦሮማ (ባዕድ/እንግዳ/ሌላ) እያሉ ሲጠሩ ነጮቹ ኦርማ የሚለውን ቃል ኦሮሞ በሚል መልሰው የአካባቢውን ሰው ይጠሩበታል፡፡ በዚህ ሂደት የተፈጠረ ቃል ነው የሚመስለው፡፡ ይህ ቃል ወደ ሐረርና የመሣሰሉት በሚገርም ሁኔታ በጣም በቅርብ ነው በኦነጋውያን ዘመን ማለት ነው፡፡ ግፋ ቢል 60 ዓመት ቢሆነው ነው፡፡ በጅማ ቃሉ ቀደም ብሎ ቢታወቅም የጂማ ሕዝብ በዚህ ቃል መጠራት አይፈልግም ነበር፡፡ ምክነያቱም እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ይሄ ቃል ለማያምኑ ብቻ የተሰጠ ስያሜ ነበርና፡፡ ለዚህ ደግሞ አባጅፋርን ማንበብ ነው፡፡ አባ ጅፋር እኛ ኦሮሞ አደለንም እስላሞች ነን ብለው ነበር፡፡ በሌሎች አካባቢዎችም ተመሳሳይ ነው፡፡ ቦረና ከቦረናነቱ በቀር ኦሮሞ የሚለውን ቃል አያውቀውም ነበር፡፡ ዛሬ በኬንያ ያሉ የቦራን (ቦረና) ነገዶች (ኦሮምኛ ተናጋሪዎች) ኦሮሞ ስለሚባለው ቃል አያውቁም፡፡ ግን በዜና አንዳንዶች እየሰሙ ስለሆነ ኦሮሞ ስለሚለው ቃል በአድናቆት ምን እንደሆነ ሲናገሩ ትሰማላችሁ፡፡ በአጠቃላይ ዛሬ ልክ ዘመናት ያስቆጠረ የሚመስለው ኦሮሞ የሚለው ቃል እንኳን ከዘፍጥረት የዛሬ 30 አብዛኛው ዛሬ ኦሮሞ የተባለው መጠሪያው እንዳልሆነ ሁሉም ቢያውቅ ጥሩ ነው፡፡  ይሄ እውነት ነው፡፡ ብዙዎች ዛሬ እብድ እስከመሆን ሊክዱ ይችላሉ፡፡  እንግዲህ ዋናው ቦረና ቦረና ነበር እንጂ ኦሮሞ ሆኖ አያውቅም ከ30 ዓመት በፊት፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ወያኔ እና ግንቦት 7

ሰሞኑን መሣይ አንድ የሜጫ ቱለማ ሰው ስለ ኦነግ ሸኔ ሲጠይቅ ሰማሁ፡፡ ተጠያቂው በኃይለሥላሴ ጊዜ የገበሬ ልጅ ከ4ኛ ክፍል በላይ አይማርም ነበር ሲል ሰማሁ፡፡ እንግዲህ ነገ ጠዋት አንዱ ይሄን የሰማ ዋይመ ተናጋሪው ራሱ ታሪክ ጸሐፊ ሆኖ ብቅ ይልና ይሄንኑ ስህተት የዘራል፡፡ ከዛ አሁን ይሄው ሁሉም እንደፈለገው የሚነዳው ትውልድ ተቀብሎት ተጨማሪ ሮሮ ያሰማናል፡፡ እርግጥ ነው ተናጋሪው ወይ የሚያስተምረው አንዱ አስተማሪ፣ ወይም የትምህርት ቤቱ ሰው እንደዛ ብሎት እሱኑ አምኖ ወደቤቱ ሄዶ ይሆናል፡፡ ወይም ደግሞ በዛ አካባቢ ገዥ የሆነው ባላባት ራሱ የፈጠረው ሕግ ሊሆን ይችላል፡፡ በተለይ እነ ራስ መስፍን ስለሺ በዚህ አይነት ነገር ከማድረግ ላይመለሱ ይችላሉ፡፡ የሆነ ሆኖ ግን ኃይለሥላሴ በትምህርት እጅግ የለፉና ከጠረፍ ቦታዎች ሳይቀር እያመጡ በራሳቸው በአዳሪ ትምህርት ቤቶች እያስተማሩ ዛሬ ድረስ ትልልቅ ቦታዋች ላይ የሚገኙ ምሁራን አሉ፡፡ እንደ እድል ሆኖ እነዛ ምሁራን ውለታ ቢስ በመሆናቸው ዛሬ ስለዛ ዘመን አያወሩም፡፡ ይልቁንስ የልደረሰባቸውን በደል ፈጥረው ለዛሬው ትውልድ መርዝ ይግቱታል፡፡ ለዚህ እንደነ ዶ/ር ገመቹ የሚባሉ ሰዎች እዩ፡፡ ለነገሩ ዛሬም ድረስ ይሄው አገር እያመሰ ያለ ፖቲከኛ ነኝ እያለ ያለው በብዛት እኮ በዛን ወቅት ትምሮ እስከ ዩኒቨርሲቲ ደርሶ ትምህርት ጥሎ የሸፈተ ነው፡፡ ከገበሬም ከሌላም የመጣ፡፡ እኔ የገበሬ ልጅ ነኝ ኃይለስላሴን ባልደርስባቸውም በእሳቸው ጊዜ በተሰራ የገጠር ትምህርት ቤት ነው የተማርኩት፡፡ ይህ ትምህርት ቤት ሲጀምር እስከ 6ኛ ነበር የሚያስተምረው፡፡ እኔም ስማርበት እንደዛው ነበር፡፡ በጣም የሚገርመው ዩኒቨርሲቲ ሁሉ ገብቼ ስማር እንደዛ ያለ ዘመናዊ ትምህርት ቤት አልገጠመኝም፡፡ በኋላ ለማስተርስ አውሮፓ ስሄድ ነው እንደዛ ያለ የመማሪያ ዕቃዎች ያሉት ዩኒቨርሲቲ ያየሁት፡፡ በእርግጥም ይህ እኔ አንደኛ ደረጃ የተማርኩበት የገጠር ትምህርት ቤት የተሰራው በስዊድኖች እርዳታ ስለነበር ሁለነገሩ ከአውሮፓ በመጣ እቃዎች የተሟላ ነበር፡፡መቀመጫ ወንበሮቹና ዴስኮቹ እጅግ የሚያማምሩ፣ ዳስተሮቹ፣ ሰሌዳዎቹ ጥቁር ሳይሆኑ አረንጓዴ ነበሩ፡፡ እኔ እስከተማርኩበት ጌዜ ድረስ እንኳን  የእነዚህ ቁሳቁሶች ወበት አሁን ድረስ ይታወሰኛል፤፡ አረንጓዴ ሰሌዳ ያየሁ ከዚያ በኋላ ከኢትዮጵያ ወጥቼ አውሮፓ ነው፡፡ እንግዲህ ይሄ ሁሉ ነገር የተሟላለት ቦታ እልም ያለ ገጠር ነው፡፡ የገበሬ ልጆች እንዲማሩበት፡፡ እንደውም በወቅቱ ችግር የነበረው ሰዎች ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት አንሰልክም በማለታቸውነ ነው ሲባል ነው የሰማንው፡፡ ይሄን አይነት ልማት በእርግጥም በቀጥታ የንጉሱ እቅድ ሲሆን በአንዳንድ አካባቢዎች ባላባቶች የራሳቸውን ሴራ ሊሰሩ ይችላሉ፡፡ ለምሳሌ መሳይ የጠየቀው ሰው በእርግጥም ተብሎ ሊሆን ይችላል፡፡ ግን የማዝናው እስከዛሬ ድረስ ይሄንኑ የኃይለስላሴ ሥርዓት የትምህርት ፖሊሲ እንደሆነ ማሰቡ ነው፡፡ መቼም ውሎው ሁሉ መርዘኛ ከሆኑና ነገሮችን በተቃራኒው እንዲታዩ ከሚያደርጉ ጋር መሆኑ እንጂ የሆነ ከክፋት የጸዳ ዜጋ ጋር ቢኖር ይሄን ያህል ዘመን ችግሩ የኃይለስላሴ የትምህርት ፖሊሲ ሳይሆን ሌላ እንደሆነ በተረዳ፡፡ ትውልድ የሚጠፋው እንዲህ ነው፡፡ እሱም ይሄንኑ ለልጆቹ እየነገረ አሳድጎ ይሆናል፡፡ እንዲህ በሆነ መልኩ ነው ትውልድ እየጠፋ ያለው

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሞትን የመረጡ ወጣት ሴቶች የመጀመሪያውን ብቻኛ የነፃነት ተጋድሎ ምዕራፍ ከፈቱ። የምዕተ ዓመቱ ማህጸን ተስፋን ሰነቀ!

በመጨረሻም ኢትዮጵያ እንደአገር እንድትቀጥል ከታሰበ ይሄን ያህል ዘመን በጥፋት ሲሴርብን የኖረውን ነገር ሁሉ መንግለን መጣል አለብን፡፡ እስካሁንም እኮ ወያኔና ኦነግ በሠረቱ ሕግ ነው እየኖርን ያለንው፡፡ እስካሁንም እኮ ወያኔና ኦነግ በሰጡን ሰንደቅ ነው ያለነው፡፡ ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚል መንግስትም ሆነ ቡድን እንግዲህ እስኪ መጀመሪያ ወንጀለኞች የሰሩትን ሕግ በሕጋዊ ሕግ ይቀይር፣ ከኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ላይ ይሄን የጥንቆላ ምልክት ያንሳ፡፡ በሰንደቅ ዓላማው ላይ ያለው ምልክት በግልፅ የእርግማን ምልክት እንጂ አንዳቸውም ከኢትዮጵያ ሕዝቦች መተሳስር ወይም ሌላ ሕዝብን የሚመለከት ምልክት እንዳልሆነ ሁሉም የወቅ፡፡ ይሄን ምልክት ስላልነካው እስከዛሬም ድረስ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ብቻ በጀመረው ሂደት ከፍታውን ቀጥሏል፡፡ ሊያውም ይሄ ሁሉ ወሮበላ እየተፈራረቀበት፡፡ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ያስተውል፡፡ ይሄ እውነት ነው፡፡ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ሰንደቅ የብዙዎች ደምና አጥንት የታተመበት የማይነበብ ለኢትዮጵያ ጠላቶች ማህተብ ይዟል፡፡ በዚህ የአባቶቻችን አጥንትና ደም ማሕተባ ላይ ነው የሰይጣናዊ አምልኮ ተከታዮች ምልክት የተደረገው

ሌላው በኢትዮጵያ ኢትዮጵያውያንን ሁሉ በማዕከላዊ ብዝሐነት የሚያማክለው ሸዋ ለኢትዮጵየዊነት ምልክትም እንዲሆን የ30 ዓመት መርዙንም ለመንቀል መሳሪያ እንዲሆን ሸዋ ራሱን የቻለ የብዝሀ ቋንቋና ባኅል የሚንጸባረቅበጽ ልዩ መስተዳድር ሆኖ እንደገና የመለስ፡፡ ከሸዋ ውጭ ሁሉም ሕዝብና መልካም መሪዎች በሚወስኑበት አስተዳደር መዋቅሩ ይሰራ፡፡ ክልል የሚባል ነገር ሥሙ ራሱ ቀፋፊና የእርግማን ስለሆነ ክፍለ ሀገር፣ ወይም ጠቅላይ ግዛት፣ ወይም አስተዳደር፣ የሚመቸው ሌል ስም ይሰጠው፡፡ በነገራችን ላይ ደጋግሜ ተናገሬዋለሁ፣ ሰሞኑን ብዙዎችም እያነሱት ነው፣ አብዛኞቹ ክልሎች ለምሳሌ ኦሮሚያ የኦሮሞ እንጂ የሌሎች እንዳልሆነ በግልጽ በኦሮሚያ ሕገ-መንግስት በተባለው ተጽፏል፡፡ እንዲህ ያል ወነጀለኛ ሰነድን ሕግ አድርጎ እየኖረ ያለ መንግስት በምን መስፈርት ነው ሕግ የሚያስከብረው፡፡ ስለዚህ ሕግ ለማስከበር ወንጀኖች ያወጡት የወሮበላ ሰነድ እንደሕግ መስራቱ ይቁም፡፡ እስካሁን አንድም ነገር በህግ አግባብ ወደፊት ሊያስኬት የሚችልና የኢትዮጵያዊነት የሆነ ምንም ዓይነት ተግባራዊ ሥራ ሳይሰራ በወሬ ብቻ ስለኢትዮጵያዊነት እየሞሉት ጭራሽ ኢትዮጵያን ወደ አደጋ እየመሩና ያው በኖሩበት እየቀጠሉ መሆኑን አስተውሉ፡፡ አገር በሕግ ነው የምትመራው፡፡ ስለዚህ ጠላት ባወጣው ሕግ እየኖርን ሕግና ሥርዓት ብንል የቱ ሕግ እንዲከበር ነው? ክልል የተባሉት እኮ በሕግ ሌሎች የመኖር መብት እንደሌላቸው የተጻፉትን ሕግ ነው ክልል የሚያስተዳድሩበት፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  የሞራል ዝቅጠት እና የአድርባይነት ልክፍት ፡ ጣምራ ደዌዎቻችን! - ጠገናው ጐሹ

ቅዱስ እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ከክፉ ይጠብቅ! አሜን!

ሰርፀ ደስታ

9 Comments

  1. “ዛሬ ማመን ሊያስቸግር ይችላል ከዛሬ 30 ዓመት በፊት አብዛኛው ኦሮምኛ ተናጋሪ ኦሮሞ ተብሎ አይጠራም ነበር፡፡”

    ሰርፀ
    እጅግ ግራ የገባህ ትመስለኛለህ:: እኔ ደግሞ የዛሬ 40 አመት መላው ኦሮሞ እራሱን ኦሮሞ ቋንቋውን “አፋን ኦሮሞ ” ብሎ ይጠራል ህዝብም የሚያውቀው ይህን እንደሆነ አረጋግጬ እነግርሀለሁ:: ምናልባት ለህዝብ ንቀት ያላቸው ሰዎች ሌላ ቃል ሊጠቀሙ ይችሉ ይሆናል:: አንተም ህዝብን ለመለያየት እንደወያኔ የምትፍጨረጨረው ውጤት አይኖረውም:: እንኳን 30 አመታት የ80 አመት እድሜ የነበረው አማራው አባቴም እጅግ ብዙ ታሪክ የሚነግረኝ የኦሮሞ ተረቶችና ዘይቤዎችን ነበር::

  2. በነገራችን ላይ ኦሮሞ የሚባል ቃል ለብዙ ሰው ብዙ ታሪክ ያስቆጠረ ሊመስለው ይችላል፡፡ ዛሬ ማመንሊያስቸግር ይችላል ከዛሬ 30 ዓመት በፊት አብዛኛው ኦሮምኛ ተናጋሪ ኦሮሞ ተብሎ አይጠራም ነበር፡፡ከዛሬ 50 ዓመት በፊት ከወለጋ በቀር ይሄን ቃል የሚያውቀውም አልነበረም፡፡ ከዛሬ 200 ዓመት በፊትኦሮሞ የሚባል ቃል ከነጭርሱም አልነበረም፡፡ እንደሚመስለኝ በወለጋ ሚሲዮናውያንበሚያስተምሩበት ወቅት የተፈጠረ ቃል ነው፡፡” አቶ ሰርፀ እንደቀላመደው

    Wow, I honestly thought you are an elderly Ethiopian who should have known better somehow. I had no idea you are this gullible. How dare you?
    እንደሚመስለኝ ብሎ የታሪክ ሀተታ በዬት አገር ነው እንደ ታሪክ የሚወራው? ከ 50 አመታት በፊትስ ተወልደን የዖሮሞነትን ህልውና አፏጭተንበትስ ከሆነና ዝንተአለም ዖሮሞ እራሱን አለ ዖሮሞ በቀር በሌላ እንደማይጠራ የምናረጋግጥ በህይወት ካለንስ? ከዚህ በላይስ ማስረጃ ከባለቤቱ በላይ የሚያውቅ ቡዳ ነው ይባላል። ዋላ አለቃ ባህሬ ይሁን ታምሬ ማንም ይሁን ማን፣ ከራሴው ቤተሰብ እስከማውቀው ህብረተሰብ በህይወት ዘመኔ በሥራም ይሁን ትምህርት ፣ እንደ እጄ መዳፍ በማውቀው ሸዋ ዖሮሞ እራሱን አለ ዖሮሞ በቀር ሲጠራና ሲጠራራ ሰምቼ አላውቅም ። ከዚህ መግቢያህ ትልቅ ስህተት ቀፅሎ ያለውን ለማንበብ እንኳ ተቸግሬ ትቼዋለሁ። ለታላቁ ዖሮሞ ህዝብ ያለህን ንቀት ከማሳየት ሌላ ምንስ ሊሆን ይችላል?እህ ብለን ከሰማን ገና ብዙ ትርክት እንሰማለን። ያሳዝናል።

  3. ውድ ሰርፀ፣
    አውሮጳ መሄድክን ማስተርስ እንዳለህ ዛሬ ነው ያወቅሁት፤ ምን ተምረህ እንደመጣህና ለምን ያህል ጊዜ በዚያ እንደኖርክ ባላውቅም ካደግህበት ከገጠሪቷ ኢትዮጵያ ብዙ የተለወጥክ አትመስልም።
    ያለ መረጃ “ይመስለኛል” ማለት ታበዛለህ፤ አውሮጳ የሄደ ማስተርስ ያለው ሰው መረጃ ሳይይዝ አደባባይ አይወጣማ!
    1/ “ኦሮሞ ከውሃ ነው የወጣው?” ትንሽ ብታስብ ወይም መንገደኛውን አስቊመህ ብትጠይቅ ይነግሩህ ነበር፤ “አባ ባሕሬ” አንድ መነኲሴ ናቸው፤ ቃላቸውን እንደ ወንጌል አንተና መሰሎችህ ትደጋግማላችሁ።
    2/ “ኦሮሞ” የሚባል ቃል ከ30 ዓመት በፊት በብዙዎች ዘንድ አይታወቅም፤ ኦሮሞ ነን የሚሉም አያውቁም ነው የምትል? “አንተና ፕሮፌሰር ጌታቸው እና አባ ባሕሬን አስበህ ከሆነ ሦስት እንጂ ብዙ አትባሉም፤ አንተ ሰነፍ “ኦሮሞ” ስለሚለው ቃል እዚህ ጠቁም። https://twitter.com/nigigebi/status/1155108064019845120/photo/2
    3/ “የገጠር ትምህርት ቤት የተሰራው በስዊድኖች እርዳታ ስለነበር ሁለነገሩ ከአውሮፓ በመጣ እቃዎች የተሟላ ነበር” ያልከው ስህተት ነው፤ ዴስኮቹ የተሠሩት አስመራ ነው። ሰነፍ ነህ፣ አንተም አቻምየለህም “ተመራማሪ” ነን ትሉ የለ? ታዲያስ?
    ትጋትህን ወድጄልሃለሁ። ሰነፍ መሆንህ ግ ን ያሰለቻል። ዐይንህ ቅርብ ያለውን ማየት ያቃተበት ምክን ያቱ በጥላቻ ስለ ተያዝክ ነው። ልብህ ጠቊሯል። ሁሌ ኦሮሞ ኦሮሞ ትላለህ፣ አንድ ጀዋር ትወስድና ኦሮሞ እንዲህ ነው እንዲያ ነው ትላለህ፤ ምኒልክ ፍጹም ናቸው፤ እስክንድር ንጹሕ ነው፤ አይነኩም፤ የነካቸው ውጉዝ ነው!? ኢትዮጵያ ያንተ ብቻ ወይም አንተን ለሚመስሉ ብቻ እንደሆነች አስበህ ከሆነ ጊዜህን እያጠፋህ ነው ወይም ሥራ ፈት ነህ!

  4. “ዛሬ ማመን ሊያስቸግር ይችላል ከዛሬ 30 ዓመት በፊት አብዛኛው ኦሮምኛ ተናጋሪ ኦሮሞ ተብሎ አይጠራም ነበር፡፡” ጋላ ብለው ስትጠራው ነበራ! አወቅሁ አወቅሁ ባይ፣ ሂድና የአባ ባህርይን “ዜናሁ ለጋላ” (1593) ሲፈልግ ጋላ ሌላም ጊዜ ወሮሞ እያለ የጻፈውን አንብብ ! 50 ሚሊዮን ህዝብ ለመሳደብ አይናችሁን የማታሹ፣ ከዕውቀት የጸዳችሁ፣ በጥላቻ የናወዛችሁ ዘረኞች፣ ምን ለመፍጠር ቀለም እንደምትለቀልቁ እናንተው ራሳችሁ የምታውቁት አይመስለኝም። መሳደብ የበታችነት ምልክት መሆኑን አታዉቁም! የወደፊት የህዝቦችን ሰላማዊ ግንኙነት ጨርሶ እንዲቀር በመጣር ምን እንደምታተርፉ አይገባኝም። ስለሰደባችሁን አንገት ደፍተን ለናንተ አሽከር ሆነን የምንኖር ከመሰላችሁ፣ በስንተኛው ክፍለ ዘመን እንደምትኖሩ አስታዉሱ!

  5. ልትል ያስብከው ገብቶኛል በአጭሩ ኦሮሞ ነኝ እና ከልሉኝ እያለ የቀወሰ አልነበርም፡፡ በወያኔ ዘመን በሩቅ ንበር የሚያጓሩት እንጂ እንደ አቢይ ዘመን ህዝብ ላይ አልቅዘኑም ነበር። የደርግ ዘምን ድህነትና አረመናዊ አገዛዝም ቢኖር በመጠኑም ቢሆን እትዮጵያዊነት እና የኢትዮጵያ ታሪክ ይከበር ነበር፡፡
    ያነሳሃቻው ችግሮች በጥቂቱ የወያኔ ህገመንግሥቱ ቢቀደድ ብዙ ችግሮችን ይቀርፋል ብዬ አስባልሁ፡፡

  6. እኔ እስከማውቀው ያኔ በ17ኛው መቶ ክፍለዘመን የግጦሽ መሬት ፍለጋ የገላንን ወንዝ(ገናሌ ) ተሻግራችሁ ወደ ሀገራችን ስትገቡ ያ እንግዳ ተቀባይነት የማያልቅበት ሀበሻ (ቅልቅል) ህብረሰብ የገላን ሰዎች ብሎ ሰየማችሁ፣ ያም ውሎ አድሮ ገላኖች ከዛም ጋሎች (ልክ ሸዋዎች፣ ወሎዎች እንደሚባለው)ሆነ።ይህኛውን ስማችሁን በደርግ ግዜ አስተዋወቃችሁን፣ እኛም አፍ ኸመክፈት ወደ አፍ ማሞጥሞጥ ስለተሸጋገርን ደስ ብሎን ጋላን ትተን ኦሮሞ ማለት ከጀመርን ከራርመናል። ምጣታችሁ ደስ ብሎን እናንተ ወተት ማለብ እኛ ደሞ አርሶ መብላት ተማምረን የናንተም ዘላንነት ሰክኖ አብረን መኖር ከጀመርን አነሆ ጥሩ 400 አመት ሆነን። በሺዎች አመታት የሚቆጠር ታሪካችንንም አብረን አጠናከርን። እናንተ ከረግረግ ውስጥ እንደ ትል ተፈጠርን ስትሉ እኮ እኛ የራሳችን ማንነትና ታሪክ ነበረን። ይህንንም ታውራችሁ ካልሆነ በቀር ከአለም ሀይማኖት መጻህፍት ልታገኙ ትችላላችሁ። ዛሬ የወረራችሁትን መሬት የኛ ብላችሁ ባለቤቱን ስትገፉ እንዴት ያሳዝናል።ለዚህም ” The great Oromo migration” የሚለውን በውጭ ፀሀፊዎች የተጻፈውን መመልከት ተገቢ ነበር። ለነገሩ አውቆ የተኛን መቀስቀስ ጉንጭ መልፋት ነው። የተማሩትና ታሪኩን የሚያውቁ የተንኮል መርዛቸውን እንኳን ታሪክ የራሱን ስም በቅጡ በማይጽፍ መሀይም ማህበረሰብ ስለበተኑ ፣ ይሄም ቄሮ የሚባለው ዘገምተኛ ቡድን እንደወረቀት የያዘውን አለቅ ብሎ ይኸው ለዚህ ተዳርገናል። ለማነቻውም የስማችሁ መቀያየር የከብት አንገት በጦር እየወጉ ደም በመቅዳትና ከወተት በመቀላቀል የሚጠጣው የቦረናው ባህላችሁ ዛሬ አናታችሁ ላይ ወቶ የሰው ደም በማፍሰስ አረመኔነታችሁን ( እሪያነታችሁን)እያመለከተ ነውና ሰከን በሉ። ይሄ በየሰው ሀገሩ ተነስቶ ኢትዮጵያ ዳውን ዳውን የሚለው ሚስኪን ከብት፣ አንድም ውጪ ስለተወለደ የሀገሩን ታሪክ ስለማያውቅ ነው፣ ቀሪው ደግሞ የመኖሪያ ፈቃዱን ለማስተካከል ነው።
    ያኔ እኛም አርገነው ነበር፣ ነገርግን መንግስትን እንጂ ውድ ሀገራችንን ዞሮ መግቢያችንንመተኪያ የሌላትን ኢትዮጵያችንን አልነበረም። በሷ ድርድር የለም። ዘገምተኛ የሆኑ ማሰብ የተሳናቸው ጠላቶቿ ከስመው ይቀራሉ። ሰንደቃችን ሁሌም ከፍ ብላ ትውለበለባለች።

    • “የገላንን ወንዝ(ገናሌ ) ተሻግራችሁ …” ገላንን እና ገናሌን ማን አንድ አደረገው?? ታሪክን የማዛባት እርኩስ መንፈስ የተጠናወታችሁ ለመሆኑ ይህ አንዱ ማስረጃ ነው። አባ ባህሬ የጻፉት “ገላና የሚባል ወንዛቸውን ተሻግረው መጡ” ነው! ያውም “ወንዛቸውን”! በኦሮሚፋ “ገላና (galaana)” ማለት “ወንዝ” ወይም “ጅረት” ማለት ነው! እና ዬትኛው ወንዝ? ‘ገላና’ን “ገናሌ” ብለው የሚያምታቱት የዘመኑ “ታሪክ ጸሃፊዎች” ነን ባዮች ናቸው!
      ኦሮሞ “ከረግረግ ውስጥ እንደ ትል ተፈጠርን” አላለም! ኦሪጅናል ቃሉ “namiyye Walaabuu baate!” “ትርጉሙም የሰው ልጅ ከወላቡ ወጣ” ነው! ልብ በል ኦሮሞ ሳይሆን “የሰው ልጅ” ነው የሚለው። ዋላቡ ዉሃም ቢሆን የባስ ነገሩን ሳይንሳዊ ያደርገዋል እንጂ የደንቆሮዎች ማላገጫ ሊሆን አይችልም። በሳይንስ ነፍስ ያለው ሁሉ ጅምሩ ከዉሃ ነው፣ ያለ ዉሃ ህይወት እንደሌለ የተረጋገጠ ነው።
      ሰው ሳይፈጠር በፊት የያዛችሁት ይመስል”የወረራችሁትን መሬት …” የምትለው ደግሞ፣ ነገደ ሃበሻት እና ነገድ አግዐዚያን ቀይ ባህርን ወደ ምዕራብ ሳይሻገሩ ምድሩ በፊት ጀምሮ የአፍሪካ ቀንድ የኩሽ ልጆች እትብት መቀበሪያ ነበር።
      ከዕውቀት ነጻ ናችሁ የምንለው እኮ በማስረጃ ነው!!

  7. ይገርማል ሁላችሁም የእሩምታ ተኩስና ስድበ እንጂ ያቀረባችሁት ማስረጃ የለም አናሲሞስ መጽሃፋ ቁልቁሉን ጻፈ ያ ምን ማለት ነዉ? ሰርጸ ካቀረበዉ ሚዛን ደፍቶ ነዉ? አባዊርቱም እኔ አለሁ አሉ እሳቸዉሰ ለኦሮሞነት ማረጋገጫ ማስረጃ ሁነዉ ሊቀርቡ ይችላሉ? ፕሮፌሰር ጌታቸዉም ሆኑ የምታብጠረጥሩት መጽሀፍ በሳይንሳዊ መልኩ የተጻፈና እናንተ የምታመልኩት አስሮም ለገሰ ዶ/ር የጻፈበት ነዉ።
    ለማንኛዉም አንድን ሰዉ ኦሮሞ፤አማራ፤ጉራጌ….. የሚያደርገዉ ሳይነስሳዊ በሆነ መልኩ መተንተን አለበት ከጥቂት አመት በፊት ኦሮሞ አልነበርንመ አላችሁ አሁን ደግሞ ሳር ቅጠሉም ታሪኩም ወንዙም ኦሮሞ ነዉ አላችሁ ይህ ለማንም አይጠቅምም። ለአንድ ነገድ ዋናዉ መገለጫዉ ቋንቋ ሊሆን አይቸልም የናንተዉ አዳነች አቤቤ አቶ ቡልቻ ደመቅሳ አማርኛን ከአማራ በላይ ይናገሩታል አቻምየለህ ታምሩ የአድዋን ትግርኛን ይናገራሉ ነገር ግን አዳነችና አቶ ቡልቻ ዛሬ አማራ ነን አላሉም አቻምየለህም እንደዛዉ።
    መገለጫችን ነገዳችን ነዉ ካላችሁ በዚህ ነገር ከማንም በላይ ሊረዳን የሚችለዉ ሰርጸ ነዉ ስለዚህ አገር ከሚታመስ መንግስተ የDNA ማሺን አምጥቶ በመጀመሪያ አለን አለን የምትሉትን ቀጥሎ ደግሞ ኢትዮጵያዊ አይደለንም ዋናዉ ዘራችን ነዉ የሚሉትን መመርመር ያስፍልጋል። እንግዲህ በዚህ ስሌት ሌንጮ ለታ፤በያን ሱጰ፤ነጋሶ ጊዳዳ በምን ታምረ ከበቀለ ገርባ፤ ከጁዋር መሀመድ፤ ቡልቻ ደመቅሳ ጋር እንደሚመሳሰሉ ይለያል ጉዱ ኢትዮጵያም ታርፋለች።
    በተረፈ ወደኛ ብእር ተቀሰረ ብሎ ስብእናን የሚነካ ተራ አስተያየት ባይሰጥ ጥሩ ነዉ። ሰርጸ በምሁር ብእሩ ምልከታዉን ሰጥቷል አቅም ካለ በዛዉ ልክ ሂሳብ ማወራረድ ነዉ። ስለ ኦሮሞ ታሪክ ጻፈ ተብሎ የስብጥር ተኩስ መክፈቱ ሀቅን ለማፈን ጥረት ማድረጉ ሀቅን ገንፍሎ ያወጣዋል እንጂ ያሰባችሁትን አያሟላላችሁም። በከፍተኛ ጥልፍልፍ የተገመደዉ የትግሬም አገዛዝ ሆኑ የመንግስቱ ሐይለ ማርያም አስተዳደርም እንደማይሆን ሁኗል ከታሪክ ካልተማራችሁ ለናንተም አይቀርም። አዉነትን እሹ
    ዘረኝነት ይዉደም

    • አንድን ህዝብ በጭፍኑ “የለም” የሚለውን ሰው “ምሁር” ማለትህ የምሁርነት አረዳድህን ስፋት ገላጭ ነው። አንድን ነገር “የለም” ብሎ መነሳት ራሱ አላዋቂነት ነው። You can not prove that something does not exist! You can prove the contrary though!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share