January 24, 2019
3 mins read

ድሬዳዋ ዛሬ በጎማ ጭስ ስትታጠን ዋለች

በዛሬው እለት ከጠዋቱ አራት ሰአት ጀምሮ በድሬደዋ ከፍተኛ ተቃውሞ ተደርጓል፡፡ ከንቲባው ያነጋግሩን ያሉ ወጣቶች መንገድ ዘግተው ጎማ በማቃጠል ተቃውሟቸውን ሲያሰሙ የዋሉ ሲሆን በፖሊስ ላይም ድንጋይ ወርውረዋል፡፡

https://www.youtube.com/watch?v=pJpzsue5H3c&t=917s

ተቃውሞው ከፍተኛ ደረጃ ሲደርስ መከላከያ ገብቶ የማረጋጋት ስራ መስራቱን ከስፍራው የደረሰን መረጃ አመልክቷል፡፡ የተቃውሞው መነሻ በጥምቀት በአል አከባበር ወቅት የተፈጠረው ረብሻ ነው፡፡ የድሬዳዋ ፖሊስ ትላንት ባወጣው መግለጫ በጥምቀት በአል ማግስት ጥር 13 ቀን 2011አ.ም የእግዚአብሔር አብ ታቦትን አስገብተው በሚመለሱ ምእመናኖች ላይ የተወረወረ ድንጋይን ተከትሎ በተፈጠረው ግጭትና ሁከት ተጠያቂ ናቸው ያላቸውን ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን መግለፁ ይታወቃል፡፡ፖሊስ 84 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ በማጣራት ላይ እንደሚገኝ ቢናገርም በዛሬው ተቃውሞ የታሰሩት ይፈቱ የሚል መፈክርም ተሰምቷል፡፡

በተጨማሪም በከተማው ውስጥ ከፍተኛ የነዳጅ እጥረት ስላለ አስተዳደሩ መፍትሄ እንዲሰጥም ተጠይቋል፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘም ከፍተኛ የስራ አጥነት በመኖሩ የሚመለከተው አካል በተለይም ከንቲባው በዚህ ዙሪያ እንዲሰሩ ወጣቶቹ ጠይቀዋል፡:

የድሬደዋ ፖሊስ ኮሚሽን አስተማማኝ ሰላም ለማስፈንና የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ እየሰራሁ ነው ብሏል።
የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ዲቪዥን ኃላፊ ዋና ሳጅን ባንተአለም ግርማ ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት ጥር 12/2011 ፖሊስ የችግሩ ቀስቃሾች ናቸው ብሎ የጠረጠራቸውን ሰዎች በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራ እያካሄደ ነው፡፡
በተጠርጣሪዎች ላይ መረጃና ማስረጃ አሰባስቦ ለፍርድ ለማቅረብ  የተቀናጀ ሥራ ይከናወናል ብለዋል፡፡
ግጭቱ ከየትኛውም ብሔር ሆነ እምነት ጋር ግንኙነት እንደሌለው ኃላፊው ተናግረዋል።
አንድ መድኃኒት ቤት በከፊል ቃጠሎ እንደደረሰበትም አስታውቀዋል፡፡
በአስተዳደሩ የሕዝቡን ሰላም ለማደፍረስ በሚንቀሳቀሱ አካላት ላይ ፖሊስና የፀጥታ አካላት ተቀናጅተው እርምጃ እንደሚወስዱ ዋና ሳጂን ባንተዓለም  ገልጸዋል፡፡
ኅብረተሰቡም የሕግ የበላይነትን ለማስከበር የሚያደርገውን እንቅስቃሴ እንዲያጎለብት  ጠይቀዋል።

john legrand zhO4JJv0zi4 unsplash
Previous Story

Best ways to cook beefs

93808
Next Story

መንግስትና ኦነግ ተኩስ ለማቆም ተስማሙ

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop