December 22, 2018
2 mins read

ደምስ በለጠ ከአገሩ ከወጣ ከ30 አመታት በኋላ ዛሬ ወደ ኢትዮጵያ በገባ በ21 ቀኑ በተኛበት አርፎ ተገኘ

የአማራ ድምፅ ራዲዮ ዋና አዘጋጅ ደምስ በለጠ ከአገሩ ከወጣ ከ30 አመታት በኋላ ዛሬ ወደ ኢትዮጵያ በገባ በ21 ቀኑ በተኛበት አርፎ ተገኘ::

የጋዜጠኝነት ስራውን ገና ተማሪ እያለ በሞስኮ ራዲዮ የአማርኛ ዝግጂት ክፍል የጀመረው ፤ ደምስ በለጠ ከ2016 አም ጀምሮ የአማራ ድምፅ ራዲዮ ሲያዘጋጅ ነበር። ደምስ ከረጅም ጊዜ የውጪ አገር ቆይታ በኋላ በፈረንጆቹ አቆጣጠር እሁድ ዲሴምበር 2 ቀን ኢትዮጵያ ገብቶ ነበር።

ከዛሬ 30 አመት በፊት ፤ ለትምህርት ወደ ሩሲያ ተልኮ ፤ ትምህርት ላይ እያለ በኢትዮጵያ የመንግስት ለወጥ በመደረጉ ፤ ይማርበት ከነበረበት አገር ከሩሲያ ወደ አሜሪካም ተሰድዶ ፤ ከትምህርት ዘመን በኋላ ያለውን ጊዜውን በሰሜን አሜሪካ አሳልፏል።

ደምስ በለጠ በአሜሪካ ስደት ላይ በቆየባቸው ጊዚያት ፤ በተለያዩ የራዲዮ ጣቢያዎች በጋዜጠኝነት ሰርቷል ። በተለይ በታሪካዊው የምርጫ 97 የቅንጅት ጊዜ የመጀመሪያውን “ንጋት” የተባለውን የኢንተርኔት ራዲዮ በመጀመር ፤ በአለም ላይ የተበተነውን ኢትዮጵያዊ በተመሳሳይ ሰአት ላይቭ በቀጥታ ዝግጂቱ ሲያገናኝ እንደነበር እናስታውሳለን::

ደምስ በለጠ በዚህ ብቻ ሳይገታ ፤ ከ2005 አም ጀምሮ እስከ 2012 የአውሮፓውያን ዘመን ድረስ ፤ ወደ ኤርትራ በመመላለስ ፤ በጊዜው የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ይባል የነበረው ድርጅት ያደርግ የነበረውን ትግል ሲደግፍ ነበር::

ደምስ በለጠ በተለይ ተቺና አስተማሪ የሆኑ መጣጥፎቹን በተለያዩ ድረገፆች እያወጣ ያስነበበን ሲሆን ፤ በዘሃበሻ የሚወጡ ፅሁፎችንም በተገቢው መንገድ በንባብ በማቅረብ ሕዝብ የማወቅ መብት አለው የሚለውን መርህ በተግባር ያሳየ ጋዜጠኛ ነበር::
https://www.youtube.com/watch?v=FKORGOIm5_E&feature=youtu.be

1 Comment

Comments are closed.

93310
Previous Story

ኤርትራዊው ፕሮፌሰር አስመሮም ለገሰ ከኢትዮጵያው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ ጋር ዛሬ ተነጋገሩ፡

93321
Next Story

አቶ ለማ መገርሳ ‹‹ዶክተር አብይን በጉልበት እሳት አቀጣጥለን እናስወጣዋለን የሚሉ ከመጡ እንሟሟታታለን እንጂ አይለቅም›› አሉ

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop