December 20, 2023
6 mins read

ብርቱ ምስጢር: የድሮን ጥቃትን ለመከላከል ባለፈው ጊዜ በፍኖተሰላም የደረሰ የድሮን ጥቃት – ተግባር ቁጥር ፩

ተግባር ቁጥር ፩-  DOC-20231220-WA0012.

Fano Drones Defence Squad

ህዳር 28 ቀን 2016 ዓ.ም

tegbar

ለፋኖ ታጋዮች ጥንቃቄ ይረዳ ዘንድ

ማህተም ፣ የማይነበብ

ወታደራዊ ድሮን ለመከላከልና ለማምከን ብዙ የተለያዩ በቴክኖሎጂ የተደገፉ ዘዴዎች አሉ ፣ ሆኖም በቴክኖሎጂ እየታገዙ ድሮንን ለመጣል ወይም ተልእኮዋን ለማምከን የሚረዱ መሳሪያዎች በፋኖ እጅ እስከሚደርሱ ድረስ በዩክሬንና በአፍጋኒስታን የነፃነት ታጋዮች እራሳቸውን ከድሮን ጥቃት ለመከላከል እና የጠላትንም ሀይል ለማዳከም የሚያስችል የሚከተሉትን ሚስጥራዊ የማሳሳቻ ዘዴዎች ተጠቅመው ከጠላት የሚሰነዘሩ የድሮን ጥቃቶችን አምክነውበታል ፣

፩) የሚሰሩ የሞባይል ስልኮችን በመሰብሰብ ፣ በተለይም ከዚህ በፊት ለጠላት መረጃ የተጋለጡ ሲም ካርዶችን ወይም ጠላት (መንግስት) የፋኖ ናቸው ብሎ የሚጠረጥራቸው የስልክ ቁጥሮችን (ሲም ካርዶችን) የያዙ የስልክ ቀፎዎችን በዛ ባለ ቁጥር ማዘጋጀት ፣

፪) እነዚህ ለዚህ ተግባር እንዲውል የተሰበሰቡት ስልኮች ባትሪዎቻቸው ሙሉ ሆነው ቻርጅ መደረግ አለባቸው ፣

፫) ጠላት (መንግስት) ቀደም ሲል ፋኖዎች ይኖሩበታል ብሎ በአየር እና በምድር ጭምር የስለላ አሰሳ በሚፈፅምባቸው አካባቢ ወይም በተደጋጋሚ ጠላት በምድርም በመሬትም ጥቃት የሚፈፅምባቸው የፋኖ ወረዳዎች ፣ መንደሮች ወይም አካባቢዎች ለይቶ ለዚህ ግዳጅ እንዲውሉ ማድረግ ፣

፬) የፋኖ ምሽጎች ሊመስሉ በሚችሉ የቋጥኝ ስፍራዎች አካባቢ ከዛፍ የተቆረጡ በሰው ቁመት አካባቢ እርዝመት ያላቸው የግንድ ቁራጮችን በማዘጋጀት የፋኖ ዩኒፎርሞችን በማልበስ ምሽግ፭) ውስጥ የተቀመጡ ፋኖዎች አስመስሎ ማስቀመጥ ፣ በሌላ አነጋገር እውነተኛ የፋኖ ወረዳ ምሽጎች ማስመሰል ፣

፮) ከጥቅም ውጭ የሆኑ ግልጋሎት የሌላቸው መሳሪያዎችን በተዘጋጁት የማሳሳቻ ምሽጎች ውስጥ “ፋኖ ተመስለው” ለተዘጋጁት የግንድ ቁራጭ አሳቻዎች መሳሪያውን አስይዞ በምሽጉ የተዘጋጁ አስመስሎ ማቀናበር ፣

፯) ከፍ ብሎ በተራ ቁጥር ፩ እና ፪ ላይ የተጠቀሱትን ስልኮች ላይ ሞልተው ቻርጅ የተደረጉትን ባትሪዎቻቸውን ከየስልክ ቀፎዎቻቸው ውስጥ መግጠም ። በተራ ቁጥር ፩ ላይ የተገለፁት ስም ካርዶችም በእያንዳንዱ ስልክ ውስጥ መኖራቸውን ማረጋገጥ ፣ የጂ ፒ ኤስ መተግበሪያ መስራቱን (GPS Feature ON) ማረጋገጥ ፣ ቀጥሎም ለአሳቻነት በተሰራው ምሽግ ውስጥ እና አካባቢ ምንም የስልክ ሲግናል ብሎክ መሆን በማይችልበት ስፍራ እየመረጡ ስልኮቹን በተሰባጠረና ዘርዘር ባሉ ስፍረዎች ላይ ማኖር ፣

፱) ከዚህ በሗላ ይህንን ዝግጅት ያደረጉት ፋኖዎች በአስቸኳይ ስፍራውን በፍጥነት ለቀው በርቀት ወደሚገኘው የወገን ወታደራዊ ወረዳና ምሽጎች መሄድ ይኖርባቸዋል ።

ይህንን ተከትሎ ጠላት (መንግስት) በሁለት አይነት መንገድ በሚያደርገው የድሮን አሰሳ ትክክለኛ የፋኖ ተዋጊዎችን የስልክ መስመር ግንኙነት ያገኘ መስሎት ተክለፍልፎ ወደ ተዘጋጀለት ወጥመድ ሊገባ ይችላል ። ድሮኑ የጂ ፒኤስ GPS እና የስልኩን ሲግናል ማሰስ ይችላል ።

በዚህም ረገድ ጠላት አሳቻ በሆነ ኢላማ ላይ በከንቱ የድሮን ተተኳሾቹን ክማባከኑም በላይ ፣ በርቀት ምሽግ ውስጥ የተዘጋጁ የርቀት ተተኳሽ መሳሪያ ያላቸው ድሮኗን ከአየር ላይ መተው ሊጥሏት ይችላሉ ።

ከፍተኛ ጥንቃቄ ፣

በዚህ ፋኖ ባዘጋጀው አሳቻ ምሽግም ሆነ አካባቢ አንድም ፋኖ ወይም የአካባቢው ነዋሪ መገኘት የለበትም ምክነያቱም የደሮን ጥቃት ከኢላማው ውጭ ስቶ ሊያጠቃ ስለሚችል፣ ከዚህ አካባቢ ፈጥኖ ርቆ መሄድ ቸል የማይባል የወታደራዊ ደህንነት ግዴታ ይሆናል ።

ድል ለዐማራ ፋኖ !

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Prisoners
Previous Story

እሳትና ውሀ – አልማዝ አሸናፊ

8779799oyk
Next Story

የድሮን ጥቃትን ለመከላከል – ተግባር ቁጥር ፪

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop