January 26, 2019
3 mins read

‹‹ሀገርን ለማረጋጋት እየተሄደበት ያለው እርምጃ ግን አዝጋሚ ነው›› አረጋሽ አዳነ

ዛሬ በአዲስ አበባ ለንባብ ከበቃው ኢትዮጲስ ጋዜጣ ጋር ቃለምልልስ ያደረጉት ወ/ሮ አረጋሽ አዳነ በአገሪቱ ውስጥ የተፈጠረውን ለውጥ አድንቀው ‹‹ሀገርን ለማረጋጋት እየተሄደበት ያለው እርምጃ ግን አዝጋሚ ነው›› ብለዋል፡፡ 

https://www.youtube.com/watch?v=p8iBU5RCUVc&t=50s

የህወሀትና ኢህአዴግ ማእከላዊ ኮሚቴ አባልና የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪና ሌሎች ስልጣኖች ላይ ቆይተው የህወሀት ክፍፍልን ተከትሎ ከእነስዬ አብርሃ ጋር የተባረሩት ወ/ሮ አረጋሽ በአገሪቱ ውስጥ መልስ የሚያስፈልጋቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሊሰጣቸው እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ 

በዚህ ቃለምልልስ እንደተናገሩት ጥያቄዎቹ ምላሽ የሚያገኙበት ሁኔታ ግን በሰከነ መንገድ መሆን ይኖርበታል፡፡ አሁን የአረና ትግራይ ፓርቲ አመራር የሆኑት ወ/ሮ አረጋሽ ሲናገሩ ‹‹በአገሪቱ እየተነሱ ላሉ ፖለቲካዊ ጥያቄዎች መሰረታዊና የማያዳግም ምላሽ ለመስጠት፣ የመድብለ ፓርቲ ስርአቱን ወደሙሉ ቁመናውና መገለጫው ለማሸጋገር፣ ቀጣዩ ሀገር አቀፍ ምርጫ ተአማኒነት ያለው እንዲሆን፣ ፍትሀዊ በሆነ የመወዳደሪያ ሜዳ ላይ እንዲከናወን፣ እውነተኛ ፉክክርና የሀሳብ ፍጭት የሚታይበት እንዲሆን ለማድረግ ዋነኛው ሀላፊነት ያለበት ኢህአዲግ ነው›› ብለዋል፡፡ ይሁንና ከቀጣዩ ምርጫ በፊት መሰራት ያለባቸው ነገሮች እንዳሉም ጠቁመዋል፡፡

 ወ/ሮ አረጋሽ ለኢትዮጲስ በሰጡት በዚሁ ቃለምልልስ ሲያስረዱ ‹‹ከምርጫው በፊት በአገሪቱ ላይ ፍፁም ሰላም ሊኖር ይገባል፡፡ ምርጫው ከመደረጉ በፊት አገሪቱን የማረጋጋት ስራ መቅደም አለበት፡፡ ምርጭውን ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ለማስኬድ እንዲቻል ሁሉም የሞመለከተው አካል የተግባባበት የምርጫ ፍኖተ ካርታ ማዘጋጀት ያስፈልጋል›› በማለት ተናግረዋል፡፡ 

በሙስና ተጠርጥረው የታሰሩትን ግለሰቦች በተመለከተ በጅምላው ለቀረበላቸው ጥያቄ ደግሞ ‹‹ሁሉም የሚመለከተው አካል ሊጠየቅ ይገባዋል፡፡ ያ ካልሆነ የተሳሳተ ትርጉም ይሰጠዋል›› ብለዋል፡፡

93876
Previous Story

የትግራይ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት እስከዛሬ በኢትዮጵያ ውስጥ ታይቶ በማያውቅ ሁኔታ የተወካዮች ምክር ቤት ያፀደቀውን ህግ ተቃውሟል

93882
Next Story

“በቤተክርስቲያን ውስጥ አፈና አለ” – አቡነ መቃርዮስ

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop