January 2, 2019
2 mins read

ብርጌድየር ጄኔራል አሳምነዉ ፅጌ ትላንት በጆንያ ስለተያዘው ሽጉጥ ተናገሩ

93481

የአማራ ክልል የሰላምና የፀጥታ ቢሮ ሀላፊ የሆኑት ብርጌድየር ጄኔራል አሳምነዉ ፅጌ የአማራ ክልል የቪአይ ፒ ጥበቃ ሀላፊ መኖሪያ ቤት ስለተገኙት ሽጉጦች መግለጫ ሰጡ፡፡ 

https://www.youtube.com/watch?v=5nRC0uUMz70&t=141s

እንደተናገሩትም የመስተዳድሩ የልዩ ጥበቃ አዛዥ በነበሩት በኮምንደር ዉበቱ ሺፈራዉ መኖሪያ ቤት፣ በሰባት ጆንያዎች ተቋጥረው የተገኙት ሽጉጦች በየሥፍራዉ ሊከፋፈል እና ሊሰራጭ የተቃደ ነበር፡፡ 

ሽጉጦቹ በሙሉ አዳዲስ እና ቱርክ ሠራሽ መሆናቸውን ያስረዱት ብ/ጄ/ል አሳምነው የተያዙትም ጉዳዩን በቅርብ በሚያዉቁ ወገኖች ጥቆማ እና ትብብር መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ሽጉጦቹ የተያዘባቸዉ ኮማንደር ዉበቱ ወዲያውኑ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገልፀውም፤ «ባንድ እና በሁለት ሰዉ ይሠራል ብለን እንገምትም» ብለዋል። 

በመሆኑም በአባሪና ተባባሪዎች ላይ ክትትሉ እንደቀጠለ ተናግረዋል፡፡ አንድ የክልሉ ፀጥታ ኃይል ከፍተኛ ባለሥልጣን ይሕን ያክል ጦር መሣሪያ ደብቀዉ መገኘታቸዉን፣ ጄኔራል አሳምነዉ «አሳዛኝ እና አሳፋሪ» ብለዉታል። የክልሉ ቪአይፒ ጥበቃ ሃላፊ መኖሪያ ቤት 498 ሽጉጦች መገኘቱን ትላንት በዘሃበሻ ዜና መዘገባችን ይታወሳል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ብ/ጄ/ል አሳምነው ፅጌ ደም መለገሳቸውን ሰምተናል፡፡

93478
Previous Story

የኢንጂነር ስመኘው አባት “ልጄ ራሱን አጠፋ የሚባለው ፖለቲካ ነው” አሉ

93487
Next Story

“የገዛ ወገኖቼ በቁሜ ቀበሩኝ” – የሚወዷቸውን የተነጠቁ እናት ዋይታ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop