December 31, 2018
2 mins read

በኢትዮጵያ የታገቱትን 4 ህንዳዊያን ለማስለቀቅ 12.4 ሚሊዮን ብር ተጠየቀ

4

ከታገቱ በርካታ ቀናትን ያስቆጠሩት አራት ህንዳዊያን ሰራተኞችን ለማስለቀቅ የተደረገው ድርድር ያለውጤት ተበተነ፡፡ ድርድሩ የተደረገው ባለፈው አርብ ሲሆን በዚህ ድርድር ወቅት የህንድ ኤምባሲና የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ተወካዮች ቢገኙም ምንም መስማማት ሊደረስ አልቻለም፡፡ ህናዳዊያኑ ሊታገቱ የቻሉት የሚሰሩበት የህንዱ የኮንስትራክሽን ድርጅት ለሰራተኞቹ ደመወዝ ሳይከፍል ወራትን በማስቆጠሩ ነበር፡፡

 

የህንዱ ቢዝነስ ላይን ጋዜጣ እንደዘገበው እነዚህን ህንዶች ለመልቀቅ የድርጅቱ ሰራተኞች 12 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር ጠይቀዋል፡፡ ከታገቱት ውስጥ አንዱ የሆነው ቻይታነያ ሀሪ ሲናገር ‹‹የህንድ ኤምባሲ በህይወት እንደምንቆይ ብቻ ማረጋገጫ ሰጥቶናል፣ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣንም  እንደማንገደል ነግሮናል›› ብሏል፡፡ እነዚህ ሁለት አካላት የታገቱበትን ካምፕ ደህንነት ከማረጋገጥ ውጭ እነሱን ለማስለቀቅ የሚያስችል ምንም አቅም እንደሌላቸውም አስረድቷል፡፡

 

ጉዳዩ ከአቅም በላይ በመሆኑም የህንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጣልቃ እንዲገባም ታጋቹ ጠይቋል፡፡ የተጠቀሰው ገንዘብ እስካልተከፈለ ድረስ የመለቀቃቸው ነገር የማይታሰብ እንደሆነም ለዜና ምንጩ ተናግሯል፡፡ የህንዱ አይኤል ኤንድ ኤፍ ኤስ ኩባንያ የመንገድ ስራ ላይ ተሰማርቶ የነበረ ሲሆን ደመወዝ ያልከፈለው በመክሰሩ እንደሆነ ከዚህ ቀደም ዘግበን ነበር፡፡

https://www.youtube.com/watch?v=Pe4vPoSA5JM&t=223s

93454
Previous Story

ኢትዮጵያና ሱዳን በሶስት ሳምንት ውስጥ ለሶስተኛ ጊዜ ተገናኙ

93478
Next Story

የኢንጂነር ስመኘው አባት “ልጄ ራሱን አጠፋ የሚባለው ፖለቲካ ነው” አሉ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop