December 27, 2018
2 mins read

የኢንተርፖልና ዓለም አቀፍ የፖሊስ ትብብር ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር ኢንተርፖል ሰሞኑን አሳልፎ ለኢትዮጵያ መንግስት ስለሰጣቸው 2 ግለሰቦች ያልተሟላ መረጃ ለሚዲያዎች ሰጡ

93394

የኢንተርፖልና ዓለም አቀፍ የፖሊስ ትብብር ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር ኢንተርፖል ሰሞኑን አሳልፎ ለኢትዮጵያ መንግስት ስለሰጣቸው 2 ግለሰቦች ያልተሟላ መረጃ ለሚዲያዎች ሰጡ::

“ዓለም አቀፉ የፖሊስ ተቋም ኢንተርፖል እአአ ከ2014 እስከ አሁን ድረስ 11 ተጠርጣሪ ወንጀለኞችን አሳልፎ ሰጥቷል፡፡ ተጠርጣሪ ወንጀለኞችን አሳልፎ ለህግ ከመስጠት አኳያ ከኢትዮጵያ ጋር በመስራት ላይ ነው፡፡” ያሉት  የኢንተርፖልና ዓለም አቀፍ የፖሊስ ትብብር ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር ጸጋዬ ኃይሌ በተለይ ለመንግስታዊው ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ በቅርቡ ሁለት ሰዎች ተላልፈው ለኢትዮጵያ የተሰጡ ሲሆን፣ አንደኛው ከባንክ ማጭበርበር ጋር ተያይዞ የሚፈለግ ተጠርጣሪ ወንጀለኛ ነው፡፡ እኤአ በ2014 እና 2015 ባለው ግዜም ዘጠኝ ተጠርጣሪ ወንጀለኞች  ከተለያዩ አገሮች ለኢትዮጵያ ተላልፈው ተሰጥተዋል፡፡” ብለዋል:: የአንደኛውን ተጠርጣሪ የተከሰሰበትን ወንጀል ቢጠቅሱም ስሙን ያልገለጹት ምክትል ኮማንደሩ ተላልፎ ስለተሰጠው ሁለተኛው ሰው ወንጀልም ማንነትም ሳይገልጹ በደፈናው ሁለት ሰው ተላልፎ ተሰጥቷል በሚል ያልተሟላ መረጃ ለሚዲያ ሰጥተዋል::

በኢንተርፖል ተላልፈው ለኢትዮጵያ መንግስት ሰሞኑን ስለተሰጡ ሁለት ሰዎች ጉዳይ ተጨማሪ ማብራሪያ የሚሰጥ የመንግስት ባለስልጣን አልተገኘም::

https://www.youtube.com/watch?v=rcbWeNfbu_o&t=32s

93391
Previous Story

በዶክተር አብይ የተሾሙት የአምባሳደሮች ምደባ ይፋ ሆነ

93406
Next Story

አባገዳዎች በሚቀጥለው ሳምንት ኦነግን ሊያነጋግሩ ነው

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop