December 28, 2018
3 mins read

አባገዳዎች በሚቀጥለው ሳምንት ኦነግን ሊያነጋግሩ ነው

93406

የኦሮሞ አባገዳዎች በምእራብ ኦሮሚያ የሚታየውን አለመረጋጋት ለመፍታት ወደ ስፍራው ሊያቀኑ መሆኑን ገለፁ፡፡ አባገዳዎቹ በመጪው ሳምንት ከኦዲፒና ከኦነግ አመራሮች እንዲሁም ከአካባቢው ህዝብና ከኦነግ ሰራዊት ጋር በመምከር እርቅ እናወርዳለን ብለው ዛሬ ቃል ገብተዋል። ሀዩ ወይም መካሪ እየተባሉት የሚጠሩት ነባር አባገዳዎችም ሆኑ አዳዲስ ተተኪ አባገዳዎች በክልሉ የሚታየው ግጭት ‹‹በዚህ ወቅት ሊኖር የማይገባ ነው›› ካሉ በኋላ ‹‹አሁን ላይ እንደ ክልልና ሀገር ተያይዘን የምናድግበት እንጂ የምንጋጭበት መሆን የለበትም።›› ሲሉ ድርጊቱን ኮንነውታል::

በአለም እውቅና የተሰጠው የአባገዳ ስርአት ተጸንሶ የተወለደባት ኦሮሚያ ክልል በዚህ ሁኔታ ውስጥ መገኘቷ የሀገር ሽማግሌዎችንም ሆነ አባገዳውን አሳዝኗል። ‹‹አለመግባባቶች ካሉ እንኳን ገዳን የሚያክል መታላቅ ስርአት ይዘን መፍታት እየቻልን ጠብ መንጃን ምርጫ አድርገን መጓዝ ይብቃን›› በማለት አባገዳዎቹ ተናግረዋል፡፡ የገዳ ስርአት ዴሞክራሲያዊ ስርአት ሲሆን በሀገሪቱ ላይ አሁን የሚታየው ጭላንጭል ዴሞክራሲ ስርአቱ በመንግስት በኩልም መተርጎም መቻሉን የሚያሳይ ነው።

ተተኪ አባ ገዳዎች በበኩላቸው ‹‹በኛ ወቅት ይህ መሆኑ ከመንግስት ጋር በጋራ ለመስራት የበለጠ እድል የሚፈጥር ነው›› ብለዋል፡፡ ሀዩ ወይም መካሪ አባገዳዎች ግጭቱ በፍጥነት እንዲቆምና በሰላማዊ መንገድ ችግሮችን መፍታት ይገባል ሲሉ አሳስበዋል። ይህ እንዲሆን መንግስት ብቻውን የሚወጣው አይደለምና የሀገር ሽማግሌዎች አባገዳና የሀይማኖት አባቶችም ማገዝ አለብን የሚል መልእክትን አስተላልፈዋል፡፡ ጨምረውም ‹‹ህዝቡም ሆነ የፖለቲካ ሰዎች ይህን ታሳቢ እንዲያደርጉ የሚያስችል ውይይትና አርቀ ሰላምን ለማውረድ ወደ ስፍራው እናቀናለን›› ብለዋል፡፡ በምእራብ ኦሮሚያ በሚኖራቸው ቆይታ ሰላም ሳናወረድ አንመለስም ያሉት አባገዳዎቹ፤ ለዚህ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።

የኦሮሞ ህዝብ አባገዳንም ሆነ ስርአቱን ሲያከብር ለየኖረና ወደ ፊትም የሚያከብረው በመሆኑ ችግሮቹን ተፈተው ሰላም ወርዶ እንደሚመለሱም እምነታቸውን ገልጸዋል።
https://www.youtube.com/watch?v=KcPKUXGZAys&t=28s

93394
Previous Story

የኢንተርፖልና ዓለም አቀፍ የፖሊስ ትብብር ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር ኢንተርፖል ሰሞኑን አሳልፎ ለኢትዮጵያ መንግስት ስለሰጣቸው 2 ግለሰቦች ያልተሟላ መረጃ ለሚዲያዎች ሰጡ

93412
Next Story

በደብረማርቆስ በተደረገ አስቸኳይ ስብሰባ በመለስ ዜናዊ ስም ይጠራ የነበረ ፓርክ ስሙ እንዲቀየር ተወሰነ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop