December 27, 2018
4 mins read

ተጨማሪ ሚስጢራዊ የማሰቃያ እስር ቤቶች ተገኙ

93379

 የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት በተለያዩ ሀላፊነት ሲሰሩ በነበረበት ወቅት የተሰጣቸውን ስልጣን ወደጎን በመተው በዋና ወንጀል አድራጊነት  በመሳተፍ የጌታቸው አሰፋን ትዕዛዝ በማስፈጸም ሕዝብን ሲያሰቃዩ ነበር በሚል ተጠርጥረው የታሰሩት ማእሾ ኪዳኔ እና ሃዱሽ ካህሳይ ዛሬ ፍርድ ቤት ሲቀርቡ  መርማሪ ፖሊስ የስብዓዊ መብት ጥሰት ሲፈፀምበት የነበረ ተጨማሪ ሚስጥራዊ የማሰቃያ እስር ቤቶችን ማግኘቱን ለፍርድ ቤት ገለጸ::

1ኛ ተከሳሽ ማእሾ ኪዳኔ  ተጠርጣሪው አሁን ካልተያዙት የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት የቀድሞ ሀላፊ አቶ ጌታቸው አሰፋ ጋር በመመሳጠር በህገ ወጥ መንገድ በወቅቱ በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የነበሩ ግለሰቦች ላይ ድብደባና ስቃይ እንዲሁም አስነዋሪ ተግባራትን በመፈፀም እንዲሁም በኬተሰቦቻቸው ጋር እንዳይገናኙና ፍርድ ቤት እንዳይቀርቡ አድርገዋል በሚል ተከሰዋል: እንዲሁም ከሚያገኙት ገቢ በላይ ምንጩ ያልታወቀ ከፍተኛ ሀብት አፍርተው መገኘታቸውም  በሌብነት ወንጀል እንዳስጠረጠራቸውም በክሱ ላይ ቀርቧል::

2ኛ ተጠርጣሪ አቶ ሀዱሽ ካህሳይ የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ሲሰሩ በቁጥጥር ስር ባሉ ተጠርጣሪዎች ላይ የሰብአዊ መብት ጥሰት ወንጀሎች እንዲፈፀሙ በማድረግ፣ወንጀሉ መፈፀሙን እያወቁ ለህግ አካል ባለማቅረብ እና ከሚያገኙት ገቢ በላይ ምንጩ ያልታወቀ ከፍተኛ ሀብት አፍርተው ተገኝተዋል በሚል በሌብነት ወንጀል ጭምር መጠርጠራቸው ከፖሊስ ክስ ለመረዳት ተችሏል::

በዛሬው የችሎት ውሎ ፖሊስ ከዚህ ቀደም በተሰጠው የምርመራ ጊዜ ወቅት ያከናወናቸውን ስራዎችም ለፍርድ ቤቱ ያስረዳ ሲሆን፥ በዚህ ወቅትም ከአምስት ሰዎች ተጨማሪ የቃል ምስክር መቀበሉን ገልጾ ሲሰሩበት ለነበሩበት መስሪያ ቤትም የነበሩበትን የስራ ሀላፊነት ለመለየት ደብዳቤ ልኮ ውጤት መቀበሉንም ለፍርድ ቤቱ ነግሯል::

በተጨማሪም ከዚህ በፊት ከተጠቀሱት ሚስጥራዊ የማሰቃያ እስር ቤቶች በተጨማሪ አንድ አዲስ ሚስጥራዊ የማሰቃያ እስር ቤት ማግኘቱንም የገለጸው  መርማሪ ፖሊስ ተጨማሪ የምስርክ ቃል መቀበል፣ የተጎዱ ዜጎችን የህክምና ውጤት መቀበል፣ ለመስሪያ ቤቶች የተጻፉ ደብዳቤዎችን ማሰባሰብ እና የምርመራ ቡድን በማቋቋም በሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች ከሚገኙ ተጎጂዎች የቃል ምስክርነት መቀበል እንደሚቀረው ገልጾ 14 ቀን ተጨማሪ ጊዜ ቢጠይቅም የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 10ኛው የወንጀል ችሎት  10 ቀን ብቻ ፈቅዷል::

https://www.youtube.com/watch?v=rcbWeNfbu_o&t=32s

93370
Previous Story

ኢትዮጵያውያኑ ‘የይለፍ ፍቃድ የላችሁም’ በሚል በትግራይ በኩል ኤርትራ እንዳይገቡ ተከለከሉ

93382
Next Story

ሌተናል ጄነራል ባጫ ደበሌ ‹‹ከአዜብ መስፍን ጋር ጫት አልነገድኩም›› አሉ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop