August 14, 2013
4 mins read

የ6 አመቷን ህፃን የደፈሩት የ60 አመት አዛውንት በ14 አመት እስራት ተቀጡ

ሰንደቅ
*ዐቃቤ ህግ ቅጣቱ አንሷል ሲል በውሳኔው ላይ ቅሬታ አለኝ ብሏል
በአሸናፊ ደምሴ
የ6 አመቷን ህፃን አታለው ደፍረዋታል ሲል የፌዴራሉ ዐቃቤ ህግ ክስ የመሰረተባቸው የ60 አመቱ አዛውንት አቶ አምደላ ነአምሳ ጥፋተኛ ሆነው በመገኘታቸው ፍርድ ቤት በ14 አመት ከ5 ወር ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ሲል የቅጣት ውሳኔውን አስተላለፈ። የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ፍትህ ጽሕፈት ቤት ዐቃቤ ህግ ግን በቅጣት ውሳኔው ላይ ቅሬታ እንዳለው በመግለፅ ለፍርድ ቤቱ ደብዳቤ ፅፏል።
በፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት 7ኛ ወንጀል ችሎት ግለሰቡን ጥፋተኛ ያላቸው የዐቃቤ ህግን የክስ መዝገብ መርምሮና የሰውና የሰነድ ማስረጃዎችን መርምሮ ነው። ዐቃቤ ህግ በክሱ እንዳመለከተው፤ ተከሳሽ ለአቅመ ሔዋን ካልደረሰች ልጅ ጋር የግብረ-ሥጋ ግንኙነት ለመፈፀም አስበው በሐምሌ 8 ቀን 2004 ዓ.ም በግምት ከቀኑ 7 ሰዓት ሲሆን በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 14/15 ክልል ልዩ ቦታው ገብስ ሜዳ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ስሟን የማንገልጽላችሁን የ6 አመቷን ህፃን አታለውና አግባብተው ወደመኖሪያ ቤታቸው በማስገባት፤ አልጋ ላይ እንድትተኛ አድርገው የመድፈር ወንጀል ፈፅመውበታል ሲል ይከሳል።
የጉዳዩን ግራና ቀኝ ሲመረምር የቆየው የፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት 7ኛ ወንጀል ችሎትም ተከሳሹ ዐቃቤ ህግ ያቀረባቸውን የሰውና የሠነድ ማስረጃዎች በአግባቡ ማስተባበል አልቻሉም ሲል ጥፋተኛ ብሏቸዋል።
ፍ/ቤቱ ሐሙስ ሐምሌ 30 ቀን 2005 ዓ.ም ባስቻለው ችሎት፤ ተከሳሹ ጥፋተኛ በሆኑበት ወንጀል ላይ ቅጣት ያስተላለፈ ሲሆን፤ የወንጀሉን ደረጃ ከባድ በማለት የህፃኗን ዕድሜ እንደምክንያት ያቀረበው ፍርድ ቤቱ ከ20 አመት እስከ 22 አመት ሊያስቀጣ እንደሚችል ይጠቅሳል። ዐቃቤ ህግ ምንም አይነት የወንጀል ማክበጃ ያላቀረበ ሲሆን፤ ተከሳሹ በበኩላቸው የቤተሰብ አስተዳዳሪና ምንም አይነት የወንጀል ሪከርድ የሌለባቸው መሆናቸውን መጥቀሳቸው የቅጣት እርከኑን ዝቅ እንዳደረገላቸው ለመረዳት ተችሏል። በዚህም የቅጣት መነሻው 22 አመት ላይ እንዲያርፍ ሆኗል።
የግራቀኙን አስተያየት ያደመጠው ፍርድ ቤቱም ጉዳዩን መርምሮ የ60 አመት አዛውንቱን ጥፋተኛ በተባሉበት ወንጀል በ14 አመት ከ5 ወር ፅኑ እስራትና ለአምስት አመታት በሚዘልቅ ከመምረጥ መመረጥ ህዝባዊ መብታቸው እንዲታገዱ ሲል ውሳኔ አሳልፏል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ በፍርድ ቤቱ የቅጣት ውሳኔ ደስተኛ ያልሆነው የክፍለ ከተማው ፍትህ ጽ/ቤት ዐቃቤ ህግ ቅሬታውን ጠቅሶ ደብዳቤ መፃፉንና ቅጣቱ መሻሻል እንደሚገባው ማመልከቱን ለማወቅ ተችሏል።n

ምንጭ፡ ሰንደቅ ጋዜጣ

2 Comments

  1. What was Esknder Nega’s crime and got 18 years but this stupid arrogant crazy 60 years old abused the 6 years old baby girl got 14.5 years and his voter privileges suspended what a joke. it doesn’t matter whether he votes or not because the only winner in Ethiopia is weyane. why the DA didn’t ask for Eskinder Nega’s harsh judgment to be lenient? this showsTHER IS NO JUSTICE IN ETHIOPIA.

Comments are closed.

MillionsVoice1
Previous Story

የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት ግብረኃይል በዳያስፖራ አስተባባሪ ኮሚቴ በሰሜን አሜሪካ ጥሪ አደረገ

ሰንደቅ
Next Story

ከአንድ ሥጋ ቤት ሥጋ ገዝተው የተመገቡ 60 ሰዎች በህመም እየተሰቃዩ ነው

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop