አክራሪነት በኢትዮጵያ – ጥያቄዎች ለሃጂ ናጂብ

አማኑኤል ዘሰላም
amanuelzeselam@gmail.com

July 17, 2013

ከማከብራቸው የዲሞክራሲ አክቲቪስት መካከል አንዱ የሆኑት፣ አቶ ተድላ አስፋዉ፣ አቶ ጃዋር መሃመድ ለተናገራቸው አንዳንድ አባባሎች የሰጡትን ምላሽ አነበብኩ። አቶ ጃዋር የተወለደው በአርሲና በሃረርጌ ድንበር አካባቢ ነዉ። በዚያ አካባቢ ነዉ አርባ ጉጉ (ምእራብ አርሲ) እና በደኖ (ምስራቅ ሃረርጌ) የሚገኙት። ወያኔ/ኢሕአዴግና ኦነግ ስልጣን በጨበጡ ጊዜ፣ በአርባ ጉጉና በደኖ የተፈጸሙትን ሁላችንም የምናወቀዉ ነዉ። አካባቢዉን ከክርስቲያኖችና ከ«አማራዎች» ለማጽዳት ፣ ብዙዎች በቤታቸው ተቆልፎባቸው ተቃጥለዋል። ብዙዎች፣ ነፍሰ ጡር እህቶቻችን ሳይቀሩ፣ ጥልቅ በሆነ ጉድጓድ ዉስጥ፣ አይኖችቸው በጨርቅ ታስረዉ፣ በሕይወት ተወርውረዋል። አርባ ጉጉን ኦሕዴድ/ኢሕአዴግ ፣ በደኖን ደግሞ ኦነግ ነበር የሚያስተዳድሩት። በዚያን ወቅት ከፍተኛ ፀረ-አማራና ፀረ-ክርስቲያን የጥላቻ ዘመቻ ይደረግ ነበር። ብዙ ያልተማረው ሕዝብ፣ ተማሪዎች፣ ልጆች ፣ የዚህ ጥላቻ ፕሮፖጋንዳ ሰላባዎች እንዲሆኑ፣ ይህን አይነት የጥላቻና የአክራሪነት አስተሳሰብ እንዲኖራቸው ተደርጓል።

አቶ ጃዋር መሃመድ የዚህ ዉጤት ናቸው። አሁን የሚያንጸባርቁት፣ ያኔ በልጅነታቸው ከኦሕዴድና ኦነግ አክራሪዎች የተማሩት ነዉ። ይህ አይነቱ የጥላቻና የአክራሪነት ፖለቲካ በኢትዮጵያ ዉስጥ ቦታ ሊኖረው የማይገባ፣ ለአገር ትልቅ ጠንቅ የሆነ ፖለቲካ ነዉ። አቶ ተድላም በዚህ ጉዳይ ላይ ጊዜያቸዉን ወስደው አክራሪነትን እና ጥላቻን ለማጋለጥ ላደረጉት አስተዋጾ ላመሰግናቸው እወዳለሁ።

በቅድሚያ አክራሪነት ላይ ትንሽ ልበል። በአለማችን የሙስሊም አክራሪዎች በርካታ ጥፋቶች እየፈጸሙ እንደሆነ ሁላችንም የምናወቀዉ ነው። እነዚህ አክራሪዎች ዋሃቢስት ወይንም ሳላፊስት ይባላሉ። አላማቸው ሰው ሁሉ ሙስሊም እንዲሆን ነዉ። «ከሙስሊም (ይሄ ሱፊዎችና ሺያዎችን አይጨምርም) ውጭ ያሉ በሙሉ፣ እዉነተኛ ሙስሊም መሆን አለባቸው። አሊያም መጥፋት ይኖርባቸዋል» የሚል እምነት ነዉ ያላቸው። ሁሉንም በፍቃደኝነት ሆነ በሃይል ካሰለሙ በኋላ፣ በአንድ ከሊፋ የሚመራ፣ የሽሪያ እስላማዊ መንግስት ማቋቋም ነዉ አላማቸው።

የግብጹ ሙስሊም ወንድማማቾችን እንመልከት። አካባቢዉን ሁሉ (ግብጽ፣ ሶሪያ፣ ሳዉዲ አረቢያ፣ ዮርዳኖስ ፣ ሊባኖስ …) በሙሉ ተቆጣጥሮ፣ ዋና ከተማዉን ኢየሩሳሌም አድርጎ ፣ አካባቢዉን ሙስሊም ካልሆኖት ቃፊሮች አጽድቶ፣ አንድ ታላቅ እስላማዊ የከሊፋ ግዛት ለሟቋቋም ነዉ ሲሰሩ የነበሩት። በየቦታዉ፣ ዉስጥ ዉስጡን የተደራጁ ናቸው። ከሰማኒያ አመታት በኋላ ፣ የግብጽ ወጣቶች በቀሰቀሱት አብዮት ላይ ተረማምደው በግርግር ስልጣን ጨበጡ። የክርስቲያኖችን እና አክራሪ ያልሆኑ ሙስሊሞች ጥያቄ ወደ ጎን አደረጉ። እስላማዊ ሕገ መንግስት አጸደቁ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  መንገድ ላይ የታገተው የኢህአዴግ የመተካካት ዕቅድ

አላማቸው ሕዝቡን በሙሉ ማገልገል፣ ግብጽን ማሳደግ ቢሆን ኖሮ፣ የሁሉንም መብት የሚያስከበር ሕግ መንግስት እንዲኖር ያደርጉ ነበር። ነገር ግን አላማቸው አገራዊ ሳይሆን አክራሪነት በመሆኑ፣ የማታ ማታ ከሕዝባቸው ጋር ተጋጩ። ሞርሲ ከስልጣን ወረዱ። ይኸው ግብጽም በነዚህ አክራሪዎች ምክንያት እየታመሰች ነዉ።

አንድ ነገር አንርሳ። እነ ሞርሲ ለምርጫ ይወዳደሩ በነበረበት ወቅት፣ ስዉር አላማቸውን ደብቀዉት ነበር። ስልጣን ከያዙ በኋላ ነዉ እዉነተኛ ማንነታቸው የተጋለጠው።

ኢትዮጵያ ዉስጥም አክራሪዎች አሉ። ለጊዜው ማንነታቸውን ደብቀዉ፣ ኃይላቸዉን እስኪያፈረጥሙና ስልጣን እስኪጨብጡ ድረስ ሞደሬቶች ሊመስሉን ይችላሉ። የአዲስ አበባ ከንቲባ የነበረ፣ አንድ አክራሪ የኢሕአዴግ ባለስልጣን ሙስሊም ነበር። (በዚህ አጋጣሚ ኢሕአዴግ እራሱ በአክራሪዎች የተሞላ ድርጅት መሆኑን የሚያሳይ ነው) አብያተ ከርስቲያናት እንዳይገነቡ እየከለከለ፣ መስኪዶች እንዲገነቡ ይፈቅድ ነበር። መስኪዶች መሰራታቸው ችግር ባይኖረዉም፣ ቤተ ክርስቲያናት እንዳይሰሩ እያከላከሉ መስኪድ እንዲሰራ መፍቀድ ግን፣ ሌሎች እምነቶችን ለማዳከምና ለማጥፋት የሚደረግ አክራሪነት ነዉ።

እነ ጃዋር መሃምድ፣ እስላማዊ ኦሮሚያን፣ ብሎም እስላማዊ ኢትዮጵያን ለማቋቋም አላማቸው አድርገዉ ሲንቀሳቀሱ፣ ብዙ ልንደነቅ አይገባም። እነዚህ ከአለምአቀፉ የሙስሊም ወንድማማች ጋር እየተመካከሩ፣ እጅና ጓንት ሆነው የሚሰሩ ናቸው። ወጣት ጃዋር መሃምድ፣ ቸኩሎ የረጅም ርቀት አላማቸዉን አጋለጠባቸው እንጂ፣ በአሁኑ ጊዜ በአብዛኛዉ፣ ሰላማዊ፣ ሞደሬት ፣ ከሁሉም ጋር መስራት እንደሚፈልጉ፣ አድርገዉ ነዉ እራሳቸውን የሚያቀርቡት። በአሁኑ ጊዜ ትኩረታቸው ሙስሊም ያልሆነው ክርስቲያኑ ላይ ሳይሆን፣ ሞደሬት ሙስሊሞች ላይ ነዉ። ከዋሃቢዝም ዉስጥ የተሳሰተ እስልምና የሚከተሉ የሚሏቸውን ማጥራት፣ ለዚህ ዘመቻም መሰናክል የሚሆኑትን፣ ታላላቅ የሙስሊም አባቶችን፣ ማስወገድ ዋና አላማቸው ነዉ።
ይሄንን ኢትዮጵያዉያን ሁሉ ከወዲሁ ማገናዘብ ያለብን ይመስለኛል። ጉግል እያደረግን ትንሽ ጥናት ብናደርግ ብዙ የአክራሪዎችን ታክቲኮች እንረድለን።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ስህተትን በስህተት በማረም የተሄደበት ረዥም መንገድ! - ዳዊት ከበደ ወየሳ

አብዛኛው ኢትዮጵያዊ፣ ለዜጎች መብት መከበር፣ ለእምነት ነጻነት፣ ለዴሞክራሲ ያለዉን ቁርጠኝነት እያሳየ የሚገኝበት ወቅት ነዉ። እነ ኡስታዝ አቡበከር፣ ከመታሰራቸው በፊት ሲያስተምሩት በነበሩ ትምህርቶች ላይ ተቃዉሞ የሚኖርን ብዙ አለን። ነገር ግን የሚያስተምሩትን ብንቃወምም፣ ትምህርታቸውን በትምህርት መመክት ሲቻል፣ ሃሳባቸውን በነጻነት የመግልጽ መብታቸው ተረግጦ፣ አንዲት ጠጠር ሳይወረዉሩ ሽብርተኛ ተብለዉ፣ አሳፋሪ በሆነ መንገድ፣ በኢቲቪ ስብእናቸውና ክብራቸው ተዋርዶ ማየታችን እንደ ሰው፣ እንደ ኢትዮጵያዊ አሳዝኖናል። በነርሱም ላይ የደረሰው ግፍ ፣ የሃይማኖት ጉዳይ መሆኑ ቀርቶ የሰብዓዊ መብት ጉዳይ በመሆኑም፣ ከነእስክንድር ነጋ፣ አንዱዋለም አራጌ ጋር፣ የነአቡበከርንም መፈታት ሕዝቡ እየጠየቀ ነዉ።

በእስረኞች መፈታት፣ በእምነት ነጻነት፣ በሰብዓዊ መብት መከበር፣ በሕግ የበላይነት ዙሪያ፣ በአንድ ድምጽ መናገር እንደጀመርነዉም፣ በአክራሪነት ዙሪያም አንድ ድምጽ መናገር አለብን። በጋራ ሁላችንም ዋሃቢዝም አክራሪነትን መቃወም ይኖርብናል።

የመጀመሪያው ከጂራ ፋንዉንዴሽን መሪ ለሆኑት ለሃጂ ነጂብ መሃመድ አቶ ተድላ በጻፉት ደብዳቤ «It is unfortunate you did not condemn Jawar Mohamed hateful speech » ብለዋል። ሃጂ ነጂብ መሃመድ፣ በተለያዩ የዳያስፖራ ኢትዮጵያዉያን ጉባዔዎች ላይ ሙስሊም ማሀብረሰቡን ወክለው የሚናገሩ ናቸው። በርግጥም እነ አቶ ጃዋርና መሰሎቻቸው የሚያራግቡትን አክራሪነት አለማውገዛቸው ተገቢ አይደለም። «ምናልባት ሃጂ ነጂብ ከላይ ሞደሬት ከዉስጥ ግን እንደ ጃዋር አክርራሪ ይሆኑ ይሆን ?» የሚል ጥያቄም ሊነሳ ይችላል።

የሳዉዲ ታላቅ ሙፍቲ (የዋሃቢስቶች ፓትሪያርክ እንደማለት ነዉ) ፣ ሼክ አብዱል አዚዝ ቢን አብደላ፣ ያለፈው አመት፣ በአካባቢዉ ያሉ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ እንዲጠፉ ጥሪ አቅርበዉ ነበር። አንድ ተራ አክራሪ ይሄን አይነት አስተያየት ቢሰጥ፣ ብዙ ትኩረት ላይሰጠው ይችላል። ነገር ግን እኝህ ሰው ዋና መሪ ሆነው ነዉ፣ በነጃዋር የተንጸባረቀዉን አክራሪነት በይፋ ሲያወጁ የምንሰማዉ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ያለፉት ሃያ አንድ ዓመታት ፖለቲካ - ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ

http://rt.com/news/peninsula-saudi-grand-mufti-701/

እንግዲህ ለሃጂ ነጂብ ያሉኝ ጥያቄዎች «እርሳቸውና የሚመሩት የሃይማኖት ተቋም ፣ ይሄንን አክራሪነት ለምን በይፋ አይቃወም ? ዋሃቢዝምን ለምን አያወግዝም ? በርግጥ ዋሃቢዝምና አክራሪነት የሚቃወሙ ከሆነ ደግሞ አክራሪነትን ለመወጋት በተግባር አስተምህሮ ይሰጣሉ ወይ ? » የሚሉት ይሆናል።

ለነዚህ ጥያቄዎች ግልጽ ምላሽ ባልተገኘበት ሁኔታ፣ ከነዚህ ሰዎች ጋር መንቀሳቀስ በተዘዋዋሪ መንገድ አክራሪነትን ማጠናከር ሊሆን እንደሚችል መገንዘብ ያለብን ይመስለኛል። የሃይማኖት ነጻነትን በማስከበር ስም፣ አክራሪነትን በማስፋፋት የሃይማኖት ነጻነትን እንዲገፈፍ መስራት የለብንም።

እዚህ ላይ አንድ ነገር ግልጽ ላድርግ። ዜጎች የፈለጉትን የመሆን መብት አላቸዉ። እምነታቸውን የማስፋፋት፣ ክርስቲያኖችን አስተምሮና አሳምኖ ሙስሊም የማድረግ፣ መስኪድ የመከፈት ሙሉ መብት አላቸው። ክርስቲያኖችም ፣ ቤተ ክርስቲያን የመክፈት፣ ሙስሊሙን ክርስቲያን የማድረግ፣ ወንጌልን በሁሉም ቦታ የማስተማር ሙሉ መብት እንዳለቸው መረጋገጥ አለበት። ሙስሊሞች ክርስቲያን በመሆናቸው የሞት ፍርድ ሊፈረድባቸው አይገባም።

እንግዲህ አብረን እንድንሰራ ከተፈለገ «ሃይማኖት የግል አገር የጋራ» በሚለው መርህ ተስማምተን፣ አገራችንን እንደ አንድ ሕዝብ እያሳደግን፣ በፊናችን ደግሞ የምናምንበትን እምነት በሰላም ማስተማር፣ የምንከተለዉን ሃይማኖት ይዘን በሰላም መቀጠል ያስፈልጋል። ሰው የመረጠዉን የወደደዉን ሃይማኖት ይያዝ።

በአክራሪነት ላይ ይሄን ካልኩ ይበቃል። በጠባባ ብሄረተኝነት ላይ ያተኮረዉን ክፍል ሁለት በሚቀጥለው ጊዜ ይዤ እቀርባለሁ። ያኔም ጃዋር «ኢትዮጵያዉያን ከኦርሚያ ይዉጡ» ያለው አባባል በክልል ሕገ መንግስቶች በሰነድ የተንጸባረቀ መሆኑን ለማሳየት እሞክራለሁ።

25 Comments

  1. What a sad Amhara campaign. Any of you before you point finger have you:

    1. Denounced that Amara did a crime on Muslims?
    2. That Muslim discrimination was and is rampant in Ethiopia because of your forefathers?
    3. That Axum People are terrorists who deny Muslims the right to worship.
    4. Orthodox church played a significant role in the segregation of Muslims before the Palace.

    5. No one apologized when Meles pronounced Ethiopia as Christian Island.

    6. No one apologized for what Yohannes IV airport being built.

    7. Than no one apologized for Christianization of public hospitals at the expense of Muslim tax payers such as Paulos.

    8. That no one apologized for the christening of street names.

    9. That no one denounced the pentization of Ethiopia.

    10. No one apologized the coptization of our public media with “timikete” and other celebrations… running all day long.

    Before you ask us to be moderate, have you not moderated yourself? How many times did Muslims get betrayed by extremist Christians who fought along them>?
    How many Muslims got disappointed while working for their country labeled as Egypt sympathizers? How much did we sacrifice but later got betrayed???

    There is such hypocrisy in the name of Ethiopia. All you people want is to abuse Muslims once you get to power. I for one question the authenticity of Amhara Christians or tigre Christians. They all want to step on Muslims to grab power. Most of them act like they love Muslims, but they never lift a pent to defend the plight of Somalis or Axum Muslims. Now, they are all over the place denouncing Juhar or demanding Nejib to do this or that. Get life with your amara chauvinism. You guys terrorists who love Orthodox inside but never openly admit it outside.

    “Monihen felge”. we do not need your collaboration which will turn out to be a miscalculation anyways. Muslims have enough power to liberate themselves. No need to solicit your malicious cooperation.

  2. Ato Amanuel, are you from Amanuel Hospital? you smell like the chief fundamentalist. All your accusations are nonsense. the area for one church in Addis Ababa may equivalent to ten Mosques but u still complain.hey don’t repeat like a parrot what the corrupted world media tells u. use your brain if you have one

    • this guy is not amanuel,cause amanuel means god with us.by reading his article,he is sick/a person associated with evil/.

  3. many thanks ato Amanuel!
    Thank you again for taking all my idea high to the people of Ethiopia to watch around and in particular to Haji-Nejib.

    I now ask ESAT and all other FORUMs who in one way or another worked and working with This relegious father to ask him his personal idea on throat cut. This is one of the most painful to hundreds of thousands of Ethiopians today. Still Jawar is promoting it! Kena sel angetun bemecha new yemenekenetesew…

    I say again, to America, why you go far to Afganistan and SOmali to look for terrorist, while you have some of them in you!!!?!!

  4. @Amanuel betam tigermaleh silematakew haymanot batzebarik melkam new ene ende 1 ethiopiawenete yemimekirih silematakew haymanotagul tintenahin kemestet sile haymanotih yebelete bitak emnetih yemiyazihin bitsera lamenkibet neger melkam new elalehu be Amet andi/1 /gize church/BETEKRISTIYAN / yematihed sew silematakew yawum silesew emnet batzebarik melkam new
    ETHIOPIA BE KIBR LE ZELALEM TINUR
    AMEEEEEEEEENNNNNNNNNN

  5. Yes, we are with our muslim brothers on the questions they raise. We absolutelly reject and fight the governments move to sponser Alhabash. Equally we don’t want to see wahabisim and sufisim in our land!! Our muslim brothers and sisters shall come clear on this. We know what wahabisim and sufisim stands for and we want to make sure our countrymen and women are not in any wat connected to these extreme groups. We want to estabilish a secular democratic ethiopia for all.

    The way our young Ethiopian muslim brothers and sisters are behaving is odd not only to us but the moderate muslims too. We have to discuss this before it is too late. Our muslim brothers are isolating themselves not only from christians but from moderate muslims too.

  6. Islam has to be eradicated from Ethiopia. Ethiopia did wrong to save Islam. If the axum king did not save the islamiicist, the first hijira ( the first murders ) today we would not have terrorist islam. Islam is terrorizing us. Our freedom is taken by islam. European, Norther Americans governments and people are terriffied and they have to record emails, teleophone conversations, face book chats, skype conversations, …. all these because of the devilish religion called ilsam. We have lost our privacy now because governments has to sensor our emails, telephone, our money transaction. Those of you who say muslim brothers and sisters, you must be joking guys. A muslim can not be your brother, but your mortal enemy only. Islam even does not recognize as human being. Islam teaches you to be muslims or get killed on spot. you can cut your throat by saying Allah Akubur. Those Ethiopians like ESAT, the Zehabesha,… you are just fooling yourself only. You are not fooling anyone else. Islam has to be eradicated from earth. All Europeans, North Americans, Asians, Africans, even Arabs terrified by islam. You can see Egyptian rejecting islam. The majority of people in muslim in muslim countries hate islam. They are just forced by extremists. What we need it to eradicate islam from our planet.Eradicate islam, not muslims. Muslims are victims of islam. Wake up adn smell the coffee and stand against islam.

    • Ante yehonk yekoshasha lij, yante haymanot be alem kalew amliko hulu yewerede ina yekosheshe haymanot indaleh tawkaleh yehonk inchet amliki beyegedamu wust inchet askemitachuh aydalam inde mitamelku, tabot minamimin iyalachuh mitakebrut ante chifin iwnetun satak zimbileh inde insisa atiguaz kezi belay mawrat aliyam wand kehonk silkih askemit idewililahalew ante koshasha

  7. No more question ,no more open letter for those guys ( johar and negb) …because both of them are clearly declare war on Ethiopian Christ ,am not gonna support any Muslim demonstration esat and voa should be stop broadcasting the so called eth Muslim news bcs they are 1 wing extremist …speciallyESAT please stop …..unless we will decide to stop our support(me & my friends)….gena legna Ethiopian unit endergalen senl yemanm tebab mechawecha mehon anflgm….STOP STOP STOP

  8. Gragn Ahmed.
    Welcome to zehabesha from nazret.com, typical you. Now you are telling us future agendas of wahabists, very informative.

  9. be supplements tunchachewun asdegachu ahun yemen ye article gagata newu.
    le ze hulu teteyakiwu , 1..ESAT, 2,,TAMAGE BEYENE. AND ye DIASPORA DISCUTION FORMS..NACHEWU.
    TARIK HULUNEM NEGER GEHAD YAWETAWAL.
    MOTE LE BANDA DIASPORA.
    ETHIOPIA LEZELALEM TENURE.

  10. Amanuel ante yehonk insisa yewusha lij islam ashebari bileh taweraleh bergit islam lendante aynetu wusha bota yelewum jewar yetenagerew kante kewerede angager betam yeteshale new wusha neh

  11. This guy is spreading false information.
    1. Muslim Brotherhood is not Wahabis/Salafists!
    2.More than half Ethiopian muslims are wahaabis; so they are not calling for converting everybody to muslims!
    .3. Arba Gugu is not in West Arsi as you said.
    Bedeno is not in East Haraghe as you said!

    Please try to have all the facts in front of you before you write.

  12. We told you people long ago; but you never hear or listen. Can you sleep with a snake? You can not sleep with islam; islam will not allow u to sleep it with it. Dr. Berhanu has been trying to fish from the wrong fishing pond. He does not know the shark inside the fish pond. Sharku yzo angetachu new yemikoratachu. There is a maxim that that says who who build thier house their using other people’s money are collecting stones for their burial mound. ESAT has been collecting stones for its burial tomb. EPRDF metlat or opposing is great, but sleep with islam is suicidal.

  13. @አማኑኤል፡በእርግጥ፡እንዲህብለህ፡የምታምን፡ከሆነይህቺን፡ሀገር፡አትወዳትም፡ወይም፡ለርካሽ፡ወያኔዊ፡ሰበካብለህ፡ሀገሪቱን፡ልታፈራርሳት፡ተነስተሀል፡አሲረሀል፡ማለትነዉ፡አይሳካልህም፡ወይም፡አንተሀገር፡ስታፈርስ፡ልንተባበርህ፡አንችልም፡ያተረፍከዉ፡ነገር፡ቢኖር፡ትዝብትን፡እና፡የህዝብን፡ጥያቋ፡ላለመመለስ፡ቁ2’3የሆነዉን፡ወያኔያዊ፡ማስቀየሻ፡ማደናገሪያ፡ተባባሪ፡መሆንህንና፡ራስህን፡ማጋለጥህ፡ብቻ፡ነዉ”ጃዋር፡የእምነት፡መሪ

  14. አይደለም፡የግሉን፡ነዉ፡ያወራዉ፡ለምን፡ከሰላማዊ፡እምነትጥያቋ፡ጋር፡አያያስከዉ?ጥያቋዉን፡እንዴት፡ማቅረብ፡ነበረብን?መብቱን፡የጠየቀ፡ሁሉ፡አክራሪ፡ይሆናል፡ያሰጋናልካልን፡እስክንድር፣ርእዮት፡እና፡በቅርቡ፡ከደቡብናቤኒ፡ሻንጉል፡የተፈናቀሉት፡ዜጎች፡የአማራ፡ክርስትያናዊአክራሪ፡ኢትዮ’ያን፡ለመመስረት፡ነዉ፡ማለት፡እንችላለን?ለእኔ፡ግን፡አይመስለኝም፡የሰሞኑየስላሴ፡መንፈሳዊ፡ተማሪዎች፡ጥያቋስ፡ምንልትለዉ?

  15. ፖለቲካዊነዉ?ወይስ፡ለ1000አመታት፡በዉድምበግድም፡ክርስትያንማድረግ፡ያልቻሉትን፡ሀገርናህዝብ፡ክርስቲያን፡ለማድረግ፡ነዉየሚጮሁት፡ብለን፡እንድናስብ፡ወይስ፡እንድንቃወም?@አማኑኤል”ዛሬ፡ሞደሬት፡መስለዉነገ”ብለሀል፡ነገ፡ስጋት፡አለመሆናቸዉን፡በምን፡ይግለፁ?ይፈርሙልህ?ክር፡ይሰሩ?አንተ፡እንደምትለዉ፡ነገ፡ሙስሊሞች፡ተነስተዉ”ነገ፡ክርስቲያኖች፡ስጋት፡እንዳይሆኑብን፡ማረጋገጫ፡ይሰጠን”ብለዉእንዲጠይቁ፡ነዉ?

  16. wow i cannot believe what i am reading,for me it is clear that ethiopian chrisitian hate muslims big time.i have seen the video/jawar and najebe/,its not something can create big deal.stop this islamophobia,relax muslims are not like crusaders,read history,get the fact.dont bring western crap to home,and try to watch independent news rather than fox or murdoch propoganda.think with your brain,dont be ass.we lived together in past,we will continue live together.we all known our history.It can not continue like past time,muslims are ethiopian too,they did not ask their freedom,perhaps demand it.there is no power in world to stop that it just a matter of time.euqality and freedom for all ethiopians,go to hell stupid woyanne.

  17. @ Amanual Zslam Ken Wushetk Teftk Nebr Degmo Tmlsek Be Jaware Asabke,Ethiopian Muslimoch Betmlkt Yehe Le 3 Geez Mehonu Newu Ene Sanbe,Tyakey Leante 1/ Lemndnwu Hulgeeze Wushet Yemtetfewu? 2/ Endabde Wusha Bemayemelktk Gudaye eyegebakess Yemtanefenfewu Lmendnwu? Ye Saudi Arebyan Alime(Ye Haymanot Abate Btemlkete ) Nebiu Serak Ke Saudi Arebya Ermet Beta Setoke Nebre Tastawusalke? “ER ALALUM ” Belo,3/ Egiypt Hadek Zare Degmo? Lemn? Melsu NEKTE NEWU YEMTETEFELETEN MAHABERESSEB ZEKK ADERGO MEMLKETE NEWU ALAWAKEY MADEREGE NEWU. Yehe Betam Yassaferal. Ethiopia Wuste Andm Ashebarey Yelem Lengreke Ke Gebake Weyane Ke Meraabawuyan Korjo Yaltrgeze Lemewuld Yermtemetale Ende ante ayentu Degmo Esat belelebat Yechessal, Ethiopia Wust Ahebarey WEYAN ENA HODAM KADERAWOCHU NACHEWU!!! Be Mechersham Ethiopiawuyan Ejge Betam Lentenkeke Yegebal YE MERABAWUYAN KOSHASHSHA BE DEME YETCHEMALKE EJE YALGEBABETE BOTAA YELEM ASEKEYAMEY YE POLTICA KUMARE LEMECHAWETE BELEN YEMANWETABET MANKO WUSETE ANEGEBA KE BEKEY BELAY CHEGROCH ALUBEN !!!.

Comments are closed.

Share