ሸንጎ የኢትዮጵያ ሕዝብ በቀጣይነት እያካሄደ ካለው ትግል ጎን እንደሚቆም አስታወቀ

July 16, 2013

ሐምሌ 7 ቀን 2005 ዓ. ም

የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ (ሸንጎ) ዕሁድ ሐምሌ 6 ቀን 2005 ዓ. ም በጎንደርና በደሴ ከተሞች የተካሄዱትን ትዕይንተ-ሕዝቦች ይደግፋል። ”የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት!” በሚል መሪ ሃሳብ ሥር በአንድነት ፓርቲ አቀነባባሪነት የተጀመረው የሕዝብ እንቅስቃሴ፤ የተጋረጠበትን እንቅፋት ሁሉ አልፎ እነሆ በደሴና በጎንደር ከተሞች በከፍተኛ የሕዝብ ተሳትፎ በሕዝባችን ላይ እየደረሰ ያለውን ግፍ የፍራቻ ድባብን ሰብሮ በይፋ ለመግልጥ መቻሉ ሁሉንም ኢትዮጵያዊ የሚያኮራ ተግባር ነው።

ሃሳብን በሰላማዊ መንገድ መግለጥ የሰው ልጅ የተፈጥሮ መብት ነው። ይህ መብት ደግሞ ሰው በሰውነቱ ሊከበሩለት ከሚገቡት በርካታ መብቶች ውስጥ አንዱ ሲሆን በዓለም አቀፍ ሕግጋትም የተደነገገ ነው።

የኢትዮጵያ ሕዝብ ብሶቶች እጅግ ብዙ ናቸው። በኑሮ ውድነትና ሥራ አጥነት መሰቃየት፣ ከዚህም የተነሳ ስብዕናውን የሚያዋርዱ ተግባራት ውስጥ እንዲሰማራ መገደዱ፤ የሕግ የበላይነት ተደፍጥጦ የሕዝቡ በሆነ ባልሆነው ምክንያት መደብደብ፤ መታሰር፣ መሰቃየት፤ መገደልና ለስደት መዳረግ ዕለታዊ ተግባራት መሆናቸው፤ ሙስና በስፋት መንሰራፋቱ፤ የመፃፍ፤ የመናገር፤ በነፃነት የመደራጀት መብቱ ሊከበርለት አለመቻሉ፤ በሃይማኖቱ ውስጥ የአገዛዙ ጣልቃ ገብነትና አያደረሰበት ያለው ሰቆቃ፣ ሕዝብ ለዘመናት ከኖረበት ቀየው ያላግባብ መፈናቀሉ፤ በሀገሩ ጉዳይ ላይ ድምፁን ሊያሰማ አለመቻሉ፣ በሚናገረው ቋንቋ ምክንያት በገዛ ሀገሩ እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ተዘዋውሮ ለመሥራትና ለመኖር አለመቻሉ፣ ሕዝብ የሚፈልገውን መንግሥት ሊመርጥ አለመቻሉ…ወዘተ በዚህ ሥር የሚጠቃለሉ ሰቆቃዎች ናቸው፡

ከላይ የተጠቀሱትን ሰቆቃዎች አስወግዶ መብቶችን ለማቀዳጀትና እንደሰው ለመኖር የፍራቻ ድባብን ወርውሮ በመጣል አጠንክሮ መታገል የግድ ነው። ተደጋግሞ እንደሚነገረው፤ ያለትግል ድል የለምና።

አዎ ያለው አገዛዝ በጭካኔ የተሞላ ነው። ያለው አገዛዝ ሕዝብ በፍርሃት ተሸብቦ ፀጥ ለጥ ብሎ እንዲገዛ የማያደርገው ነገር የለም። አገዛዙ በሥልጣን ላይ ለመቆየት ይረዱኛል የሚላቸውን እርምጃዎች ሁሉ ቢወስድም፤ ለመብቶቹ መከበር የሚታገልን ቆራጥ ሕዝብ ግን ለረጅም ጊዜ አንበርክኮ መግዛት አይችልም። ይህን ሃቅ ከራሳችን የትላንትና የትላንት በስቲያ ታሪካችን፤ እንዲሁም ዛሬ በሰሜን አፍሪካና በመካከለኛው ምሥራቅ ከሚታየው እውነታ ትምህርት መውሰድ ይቻላል።

ከጥቂት ሳምንታት በፊት በአዲስ አበባ፤ አሁን ደግሞ (ሐምሌ 6 ቀን 2005 ዓ. ም) በጎንደርና በደሴ ከተሞች የተካሄዱት ሰላማዊ ሰልፎች፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ የፍራቻ ድባብን ሰብሮ በመውጣት መብቶቹን ለማስከበር ቆርጦ የተነሳ መሆኑን ያረጋግጣሉ። ይህ በቁርጠኝነት እየተካሄደ ያለው አበረታች ትግል ውጤታማ እንዲሆን ደግሞ የፖለቲካ ድርጅቶች ጥቃቅን ልዩነቶችን ወደጎን በመተው በአንድነትና፣ በቀጣይነት የሕዝቡን ትግል ማስተባበር ይጠበቅባቸዋል። ስለሆነም ይህንን ታሪካዊ ግዳጅ ለመወጣት ይቻል ዘንድ የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ (ሸንጎ) ድርጅቶች ተባብረው እንዲታገሉ አሁንም ጥሪውን ያቀርባል። ሸንጎው ከምሥረታው ጀምሮ በተደጋጋሚ እንደገለጸው ሁሉ ዛሬም ከሁሉም ኢትዮጵያዊ ድርጅቶች ጋር ተባብሮ ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን ያረጋግጣል።

የተባበረና የቆረጠን ሕዝብ ፍላጎት የሚገታ ምንም ኃይል ከቶውንም አይኖርም!
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop