የ35 ሀገራት አምባሳደሮች የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበርን ጠርተው አነጋገሩ

በዘሪሁን ሙሉጌታ

በኢትዮጵያ የሚገኙ የ35 ሀገራት አምባሳደሮች የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር የሆኑትን ኢንጂነር ይልቃል ጌትነትን ጠርተው አነጋገሩ። ትናንት በአሜሪካን ኤምባሲ በተካሄደው የአምባሳደሮቹ ስብሰባ ላይ በቅርቡ የተመሰረተውንና በአዲስ አበባ ከተማ በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎች የተገኙበትን ሰላማዊ ሰልፍ ማካሄድ የቻለውን ሰማያዊ ፓርቲ ብቻ ጠርተው አነጋግረዋል። በተለምዶ ‘‘የኢትዮጵያ ለጋሾች ቡድን’’ የሚል መጠሪያ ያለውና የአሜሪካንን ጨምሮ በርካታ የአውሮፓ ሀገራት አምባሳደሮች በአባልነት የሚገኙበት የለጋሾች ቡድን በተለያዩ ጊዜያት በሀገሪቱ የሚንቀሳቀሱ ከፍተኛ የተቃዋሚ አመራሮች ጋር በሀገሪቱ ወቅታዊ የፖለቲካ ጉዳዮች ላይ እንደሚወያይ ይታወቃል። የአምባሳደሮቹ ቡድን ትናንት በአሜሪካ ኤምባሲ ባካሄደው ስብሰባ ላይ ሰማያዊ ፓርቲ በተለየ ሁኔታ ተጋብዟል። የፓርቲው ሊቀመንበርም ከአምባሳደሮቹ ጋር አንድ ሰዓት ተኩል የፈጀ ውይይት ማድረጋቸውን በተለይ ለሰንደቅ ጋዜጣ ገልፀዋል። ከአምባሳደሮቹ ጋር በተደረገው ውይይት ላይ የፓርቲው ፖሊሲ ምንነት፣ ፓርቲው በወጣቶች ላይ ከማተኮሩ አንፃር በስራ ዕድል ፈጠራ ላይ ምን አይነት ፕሮግራም እንዳለው፣ የኢኮኖሚ ፖሊሲው ምን እንደሆነ፣ የፌዴራሊዝምና የመሬት ፖሊሲው ምን እንደሚመስል፣ እንዲሁም በኢትዮጵያ የሰሜን አፍሪካና የአረብ ሀገራት አይነት አብዮት ይነሳ ይሆን የሚለው ጨምሮ ሌሎች ፓርቲውን በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ ውይይት መደረጉን ኢንጂነር ይልቃል ተናግረዋል። በተጨማሪም የፓርቲው ሊቀመንበር የፓርቲውን ራዕይ የሚያመለክት 10 ገፅ ያለው ፅሁፍ ለአምባሳደሮቹ እንዲደርሳቸው ማድረጉንም ገልፀዋል። ፓርቲው በአምባሳደሮቹ ቡድን ስብሰባ ላይ እንዲገኝ ከአንድ ወር በፊት ጥሪ እንደተደረገለት የጠቀሱት ኢንጂነር ይልቃል፤ 70 ከመቶ የኢትዮጵያ ወጣት ዕድሜው ከ35 በታች እንደመሆኑ፣ ፓርቲው ለወጣቶች የተለየ ትኩረት እንደመስጠቱ፣ የዲፕሎማሲ እውቅና መሰጠቱ ተገቢ መሆኑን የፓርቲው ሊቀመንበር አያይዘው ገልፀዋል። ፓርቲው ከተመሰረተ ጀምሮ በተናጠል ከኤምባሲዎቹ ጋር ሲሰራ መቆየቱን ያስታወሱት ኢንጂነር ይልቃል፤ ነገር ግን በለጋሾች ቡድን አመታዊ ስብሰባ ላይ በይፋ ንግግር እንዲያደርጉ መጋበዛቸው ለፓርቲው ከፍተኛ የፖለቲካ ጥቅም እንዳለውም ገልፀዋል። በተያያዘ ሰማያዊ ፓርቲ በየሳምንቱ ቅዳሜ በሀገሪቱ ፖለቲካ ላይ የወጣቶች ክርክር መድረክ ማዘጋጀት መጀመሩንና ባለፈው ቅዳሜና እሁድ በአዲስ ቪው ሆቴል ከፓርቲ አደረጃጀት ጋር በተያያዘ በፓርቲው የአደረጃጀት ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ 35 ለሚሆኑ የአሰልጣኞች ስልጠና መሰጠቱን የፓርቲው የሕዝብ ግንኙነት አስታውቋል። የአሰልጣኞች ስልጠናው ፓርቲው በቅርቡ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶችን ለመክፈት የቅድመ ዝግጅት ስራ አካል መሆኑንም የፓርቲው የሕዝብ ግንኙነት በላከው መግለጫ አስታውቋል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የወያኔ አመራሮችን ግፍ ለማጋለጥ እጄን ሰጠሁ ESAT [እውነት እና ንጋት] Oct 26 2022

(ምንጭ ሰንደቅ ጋዜጣ አዲስ አበባ ጁላይ 10 2013)

11 Comments

  1. What makes The Blue party special is the fact that they use the ‘constitution’ to assert the rights of the people to hold public demonstrations. They have not done any thing illegal so the woyane thugs cannot (in theory) stop the blue party from exercising their rights and this has been what the Ethiopian people have been waiting for for a long time. The people need leaders who can lead them.

    Why are the opposition led by people like Merrara gudina, Beyene petros etc not doing the same thing.

  2. RO$$,

    Other groups cannot do the same because they have not been permited to. Blue party has been intentionally allowed to hold public demonstrations through the offices of ANDM, Amhara poltical groups aligned with the TPLF particularly through Bereket Simon. We do not know how long the honey moon will last and we do not know what the ramifications of these activities will be down the road.

  3. peoples, always need that brave leaders who holds puplic issues with endurance. like blue party. bravo blue party.

  4. I don’t think your assessment is a valid one. Dr. Merrara and Dr. Petros have done their part under trying circumstances. The late PM fully knew that the Drs were formidable political opponents and did not give any room and thus we witnessed the 2005 tragedy. So, I cannot be sure why EPRDF seems to give a breathing room to the Blue party. Time will tell. As for me, knowing what I know first hand, I would not be surprised if the Blue party turns out to be a cloned younger generation of EPRDF but with a different name. I said many times and I say it now: Only God is the ultimate hope for Ethiopians.

  5. It seems to me history is repeating itself.I remember when members of kinijit went to the American embassy roaring like a lion and coming back like a pussy cat. Ask Beyene Petros, the loyal opposition leader who managed to avoid jail term for so long by playing cahoots with the Americans. I hate to see Mr. Yelekal step in his shoes and make a mockery of Semayawi party’s progress until now. In exchange for his cooperation, America or London might facilitate full scholarship in their renowned universities a la Birtukan, Lidetu, seye, so that he can drift away into oblivion abandoning the struggle. My suspicion is the American embassy have already put in a request to cancel the eagerly expected demonstration on behalf of woyane. If that happens, rest assured American embassy influence or pressure has something to do with it. Remember, American’s always involve themselves in this type of negotiations solely from their advantage point. My advice to Yelekal watch out!

    FREE ALL POLITICAL PRISONERS IN ETHIOPIA!!!!

  6. ኢትዮጵያውያን ከበስተጀርባ በረቀቀና በተቀነባበረ መንገድ በባእዳን ሃሎች በተለይም በምእራባውያን መንግስታትና በግሎባል ካፒታሊስቱ ልሂቃን የሚሸረብንን ሴራ በቅጡ ለመረዳት የቻልን አይመስለኝም፡፡ሰማያዊ ፓርቲን 35 የምእራብና ሌላም ሀገር መንግስታት አነጋገሩ ማለት ሰማያዊ ፓርቲ የተለየ ሃይል ወይንም ለውጥ ያመጣል ማለት አይደለም፡፡እንዲያውም ነገሩ በተቃራኒ በዋናነት በወጣቶች ላይ ያተኮረው ይህ ሰማያዊ ፓርቲ በቂ የፖለቲካና የህይወት ተሞክሮ የሌላቸውንና በስሜት ብቻ የሚመሩትን ነገር ግን በስራ-አጥነትና በሌላም አይነት ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግር ዋና ተጠቂና በዚህም የተነሳ ለአመፅና ለተቃውሞ ደግሞ ፈጣንና ኃያል የሆኑትን ወጣቶች አስቀድሞ በቀላሉ ለመቆጣጠር ተብሎ የተሰራ ስራ ሊሆን ይችላል፡፡ግሎባል ካፒታሊዝምን እንደ አለም አቀፍ ስርዓት በዋናነት የሚያራምዱት ምእራባውያን መንግስታት በእንደኛ አይነት ታዳጊ ሀገር ውስጥ ለእነሱ አለም አቀፍ ስርዓት የማይመች እንቅስቃሴን እንዴት በረቀቀና በተቀነባበረ መንገድ ከበስተጀርባ መቆጣጠርና ማጨናገፍ እንደሚችሉ የብዙ ዘመናት ልምድ አላቸው፡፡በግብፅ እየሆነ ያለውም የዚሁ አይነት አካሄድ ነው፡፡ቁምነገሩ ያለው ሙባረክን መጣል ሳይሆን ከሙባረክ ቀጥሎ ምን አይነት ሃይልና ስርዓት ነው ያለው ነው፡፡በኢትዮጵያም ያለው በተመሳሳይ የወያኔን የተወሰኑ ቁንጮ ባለስልጣናት ከስልጣን ማስወገዱ ላይ ሳይሆን በቀጣይ የሚተካው ምን አይነት ሃይልና ስርዓት ነው የሚለው ወሳኝ ነገር ነው፡፡አሁን ከሰማያዊ ፓርቲ ጋር በተያያዘ በረቀቀና በተቀነባበረ መንገድ ከበስተጀርባ እየተሰራ ያለው ስራ በቀጣይ ሊመጣ የሚችልን ስር-ነቀል የለውጥ አብዮት አስቀድሞ ለመግታት አርተፊሻል የሆነ ለውጥ የሚያመጣ አርተፊሻል ተቃዋሚና ተቃውሞ ሰልፍ ለማዘጋጀት የታሰበ ሊሆን ይችላል፡፡ይህ ፈረንጆች “Manufacturing Dissent” የሚሉት ማደናገሪያና ማዘናጊያ ስልት ነው፡፡ሰማያዊ ፓርቲ ላይ ከፍተኛ ጥርጣሬ አለኝ፡፡ለምሳሌ ሰማያዊ ፓርቲ ከሰጠው መግለጫ ውስጥ አንዱ ወጣቱን ከኮሙኒዝም አስተሳሰብ ማላቀቅ የሚለው አባባል እጅግ የዓለምን ታሪካዊና ተጨባጭ ሁኔታ በጥልቀትና በስፋት ያልተረዳ ጥራዝ-ነጠቅና በጣሙን የሚያስቅና እጅግ ያልበሰለ አሳሳች የፖለቲካ አካሄድ ነው፡፡ወያኔ ስልጣን ላይ የወጣው የቀዝቃዛውን ጦርነት ማክተም ተከትሎ የሶሻሊስቱ ጎራ ጊዚያዊ ውድቀትንና የምእራቡን ዓለም የግሎባል ካፒታሊዝም ጊዚያዊ የበላይነት ተከትሎ የዘቅቃዛው ጦርነትን ማክተም ተከትሎ ነው፡፡ስለዚህም ላለፉት 22 ዓመታት በኢትዮጵያ በአፍሪካ በታዳጊው ዓለምና በጠቅላላው በዓለም ላይ በአብዛኛው ሰፍኖ የቆየው የግሎባል ካፒታሊዝም ኒዎ-ሊበራል ኒዎ-ኮሎኒያሊዝም ኢምፔሪያሊስታዊ ፕሮጀክት ነው፡፡ወያኔ ንቃተ-ህሊናው በቅጡ ያልዳበረውን ሕዝብ ለማሳሳት ሲል አብዮታዊ ዲሞክራሲ (ኢህአዴግ=ኢትዮጵያ ህዝባዊ አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ግንባር) የሚል ጭንብል ስላጠለቀ ብቻ ወያኔን ኮሙኒስት ነው ብሎ ማሰብ እጅግ ከፍተኛ ምሁራዊ ድንቁርና ነው፡፡ወያኔ በተግባር ላለፉት 22 ዓመታት አሁንም ወደፊትም በረቀቀና በተቀነባበረ መንገድ በዘረኛነት በዘራፊነት በቅጥረኛነት እያራመደ ያለው የግሎባል ካፒታሊዝም ኒዎ-ሊበራል እና ኒዎ-ኮሎኒያሊዝም ኢምፔሪያሊስታዊ ፕሮጀክት ነው፡፡ታዲያ የቀዝቃዛው ጦርነት ካከተመ ከ22 ዓመታት በኋላ በወያኔ ዘመን እድሜው ገና ከ40 ዓመት በታች የሆነ ወጣት ትውልድ ኮሙኒዝምን ከየት ተምሮት ነው ኮሙኒዝምን ለመዋጋት የሚባለው፡፡አዎ በእርግጥ አንድ የማይካድ እውነት እያፈጠጠ መጥቷል፡፡ይኸውም ግሎባል ካፒታሊዝም እንደ ስርዓት ግለኛ ጦረኛና ተስፋፊ የሆነ በኢኮኖሚያዊ ብዝበዛ ላይ የተመሰረተ ስርዓት የጥቂቶችን ህልውና ደህንነት ፍላጎት ጥቅም የሚያስጠብቅ ስርዓት ስለሆነ እንደ ስርዓት የብዙሃኑን የሰው ልጆችን መሰረታዊ ፍላጎት ለማሟላት አይደለም ጭራሽ አጠቃላይ አለም አቀፋዊ ቀውስ ውስጥ እየከተተ ነው፡፡በዚህ የተነሳም እንደ ህፃን ልጅ ዳዴ ይል የነበረውና ጊዚያዊ ውድቀት ውስጥ ገብቶ የነበረው ሶሻሊዝም አቅም ገንብቶ ዳግም የአለም ስርዓት መሆኑ የማይቀር የታሪክ ግዴታ የሆነ ይመስላል፡፡ምናልባትም እንደ ሰማያዊ ፓርቲ አይነት የዓለምን ታሪክና ተጨባጭ ሁኔታ በጥልቀትና በስፋት በቅጡ ያልተረዱ በወጣቱ ላይ ያተኮሩት ስብስቦች ይህንን አይነት ቀጣይ ሶሻሊስታዊ አስተሳሰብና እንቅስቃሴ አስቀድመው ለመግታት የተመሰረቱ የምእራቡ ዓለም ቅጥረኛ ሃይሎች እንዳይሆኑ መጠራጠሩ ይበጃል፡፡ግሎባል ካፒታሊዝም እንደ ስርዓት ከዚህ በኋላ በዲሞክራሲ ሽፋን እያጭበረበረ የራሱን ኒዎ-ሊበራል እና ኒዎ-ኮሎኒያሊዝም ኢምፔሪያሊስታዊ ፕሮጀክትና ኢኮኖሚያዊ ምዝበራውን ለመቀጠል የማይችልበት ደረጃ ላይ ነው፡፡እንደ ሰማያዊ አይነት ፓርቲንም በተለየ ሁኔታ 35 የውጪ ሀገር ዲፕሎማቶች ያነጋገሩት ምን አይነት ስርዓትና ርእዮተ አለም እንደሚያራምዱ ለመረዳትና ከዚህ የግሎባል ካፒታሊዝም ኒዎ-ሊበራል እና ኒዎ-ኮሎኒያሊዝም ኢምፔሪያሊስታዊ ፕሮጀክትና የዓለም ስርዓት ማእቀፍ ውጪ ውልፍት ለማለት እንደማይችሉ ለማስጠንቀቅ ጭምርም ሊሆን ይችላል፡፡ሰማያዊ ፓርቲ ይህንን እስከተቀበለ ድረስ ህዝብ እየሰበሰበ ሰላማዊ ሰልፍ እያደረገ የፈለገውን ያህል እንደቁራ መጮህ ይችላል፡፡ከዚህ በኋላ የኢትዮጵያ ህዝብ መጠየቅ ያለበት እንደ ሰማያዊ ፓርቲ የሽብር ህጉ ይሰረዝ ወይንም የታሰሩ ፖለቲከኞች ይፈቱ አይነት ቀሽም ጣያቄ አይደለም፡፡ከዚህ በኋላ የኢትዮጵያ ህዝብ መጠየቅ ያለበት የስርዓት ለውጥ ነው፡፡የሽብር ህጉ ወይንም የታሰሩ ፖለቲከኞች ጉዳይ ወይንም አፈናው ዘረኝነቱ ዝርፊያውና ይህንንም ተከለትሎ ያለው ድህነቱ ርሃቡ በሽታው ስደቱ ወዘተ ሁሉ ከወያኔ ቅጥረኝነቱና ከስርዓቱ የመነጨ ነው፡፡ስለዚህም እንደ ሰማያዊ ፓርቲ አይነቶች ከውጪ ምእራባውያን ዲፕሎማቶች ጋር ይበልጥ ወዳጅነት በፈጠሩ ቁጥር እንዲያውም የበለጠ መጠራጠር ነው ያለብን፡፡ምእራባውያን መንግስታት አገልግሎት ጊዜያቸው ኤክስፓየር እስካደረገ ድረስ የወያኔ ባልስልጣናት ከስልጣን ላይ ቢወገዱ ጉዳያቸው አይደለም ነገር ግን እነሱ የሚፈልጉት በቀጣይ የራሳቸውን የግሎባል ካፒታሊዝም ኒዎ-ሊበራል እና ኒዎ-ኮሎኒያሊዝም ኢምፔሪያሊስታዊ ፕሮጀክት በሌሎች ተመሳሳይ ቅጥረኞች ማስቀጠል ነው፡፡ስለዚህም የተቃዋሚው ጎራ ማንነት ይበልጥ የሚመዘነው የተወሰነ የወያኔን ባለስልጣናት ከላይ በማስወገድ ሳይሆን በቀጣይ በሚተካው ስርዓት ምንነት ነው፡፡ወያኔ በዘረኝነት በዘራፊነት በቅጥረኝነት ለራሱና ለግሎባል ካፒታሊዝም ኒዎ-ሊበራል እና ኒዎ-ኮሎኒያሊዝም ኢምፔሪያሊስታዊ ፕሮጀክት አሰራር ሲባል በጥልቀትና በስፋት የዘረጋው የሚሊታሪ የደህንነት የኢኮኖሚ የቴክኖክራቲክ ቢሮክራሲ የአካዳሚ የሚዲያ የኢንተርቴይንመንት ኢንደስተሪ ወዘተ ስርዓትና መዋቅር ሁሉ ለብዙሃኑ ህዝብ በሚጠቅም መንገድ ህብረ-ብሄራዊ ሆኖ እንደገና መዋቀር አለበት፡፡እንደ ኢፈርት አይነት የወያኔ ትልቅ የኢኮኖሚ ኢምፓየር ናሽናላይዝ መደረግ አለበት፡፡ይህ ሁሉ የሚሆነው ደግሞ እውነተኛ የሥርዓት ለውጥ ሲመጣ ብቻ ነው፡፡ሰማያዊ ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፍ ከማስወጣት በዘለለ ይህንን ማደረግ ይችላል፡፡መልሱ በአጭሩ ፈፅሞ አይችልም ነው፡፡ይህ አይነት የስርዓት ለውጥ በእነደዚህ አይነት የተቻኮለ ሆያሆየና የአደረጃጀትና የትግል ስልት ሊመጣ አይችልም፡፡ሁሉን አቀፍ ትግል ይጠይቃል፡፡ሁሉን አቀፍ ምሁራዊ የሰከነ ጥልቀትና ስፋት ያለው ውይይትና ክርክር ይጠይቃል፡፡ዛሬም ከ22 ዓመታት ዓለም አቀፋዊ ይዘት ካለው የግሎባል ካፒታሊዝም ኒዎ-ሊበራል እና ኒዎ-ኮሎኒያሊዝም ኢምፔሪያሊስታዊ ፕሮጀክትና ይህንን ተከትሎ እየተፈጠረ ካለ ይህ አይነት አለም አቀፍ ቀውስ በኋላ ስለሶሻሊዝምና ኮሙኒዝም ያለፈ ችግር የሚያወራ ፖለቲከኛ ወይንም የፖለቲካ ሃይል የዚህን አለም ታሪካዊና ተጨባጭ ሁኔታና የፖለቲካ ሀሁ በቅጡ አያውቅም ማለት ነው፡፡ሌላው እንደ ሰማያዊ ፓርቲ አይነት ብዙ ኢትዮጵያውያን ፖለቲከኞች የሚገርሙት የሶሻሊስትና የኮሙኒስት ስርዓት አራማጅና አቀንቃኝ ሃይሎች ጥንቱንም ሆነ ዛሬም ድረስ በምእራቡ አለም አሜሪካ ውስጥ ጭምር እንዳሉ በቅጡ አለመረዳታቸው ነው፡፡በፈረንሳይ በጀርመን በስዊድን ወዘተ አሁንም ድረስ የሶሻሊስትና የኮሙኒስት ስርዓት አራማጅና አቀንቃኝ ሃይሎችና የፖለቲካ ፓርቲዎች በብዛት አሉ፡፡ስለዚህም ሰማያዊ ፓርቲ ከኮሙኒዝም የፀዳ ወጣት ትውልድ ለማፍራት ማለቱ እርስ በርሱ የሚጋጭ ከፍተኛ ምሁራዊ ድንቁርና ነው፡፡ምክንያቱም አሁን ያለው ወጣት በምእራቡ አለም ባእድና መጤ የባል ወረራ የተመረዘና የተኮላሸ ስለሆነ እንኳንስ ስለኮሙኒዝም ሊያስብ ቀርቶ ታሪኩንም በቅጡ አያውቀውም፡፡

  7. First of all I need to extend my deep appreciation to visionary and well articulated leader of Blue party.yesterday I was listening to ESAT radio interview of the honourable Engineer conducted by Kassahun Ayele and I found it very irritating what the journalist had tried to divulge confidential matters brought in public so that TPLF could plot against their move. It is not the first time to watch this guy has tried to dig secret matters out of the opposition camp and make make efforts to give credit for TPLF regime out of no where. So ESAT should keep close eyes to this guy and others and do research on his family and political background. Regarding Dr Beyene Petros I insist to e every one that this selfish person was the one who betrayed opposition parties in 2005 historical election and joined Woyane parole ant and very lately he was teasing on ethiopian diaspora by saying quote an quote “they give you $50 and demanded you to sacrifice”. So this guy only needs a seat in parliament and enjoys empty talk. He must retire from politics he is no better than LIdetu no one would like to see him in ethiopian politics. Good job engineer Zeleke. Go for it! You will conquer TPLF very soon.

  8. The Blue party has got the recognition that it desrves from aid donors for its service to democracy and justice. Democracy is something you fight for., something you demand. Even in the mature democracies of the western world, you have to fight for democracy.

    The Ethnofascist Tigre people liberation front who walked to addis abeba fully loaded with guns and bullets are not surely going to hand over power on a silver platter to the opposition.

    The oppositon should demand the respect of human rights, democracy and justice and be prepared to pay the price for it. If not it is day dreaming waiting for the woyane thugs to be persuaded to hand over power.

    Tigre people liberation force came to power by the barrel of the gun and no body can move them unless a sacrifice is paid. That is what the Blue party is doing.

  9. yehem yegermal !! lemen semayawe becha ??

    ty Daye ante negeru teru argo gebtoha

    sefa argeh betakerbewes

    teru asteyayet new ty

  10. Dave, Sintun teratreh techelewaleh? selezih arfo mekemet yeshalal maleteh new?
    Men aynet bahel new yalen?

Comments are closed.

Share