Sport: የባርሴሎናው ቴክኒሻን ኢኔሽታ ውለታውን እየመለሰ ነው

July 3, 2013

በውጤታማው የካታላኑ ክለብ በባርሴሎናና በስፔን ብሔራዊ ቡድን የመሐል ሜዳ ቴክንሽያንነቱ ይታወቃል የ29 ዓመቱ አንድሬስ ኢኔሽታ።
በአውሮፓውያኑ 1996 በአስራ ሁለት ዓመቱ ይስፔኑን ኃያል ባርሴሎናን ከመቀላቀሉ በፊት በአገሪቱ ሁለተኛ ዲቪዚዮን ቢ በመወዳደር ላይ ለሚገኘው አልባሴቴ በተሰኘው እግር ኳስ ነው ከእግር ኳስ ስፖርት ጋር የተዋወቀው።
ተጫዋቹ ታዲያ የቀድሞ ክለቡ ወደ አራተኛው ዲቪዚዮን ከመውረድ በመታደግ ውለታ መላሽነቱን አስመስክሯል።
ለተጫዋቾቹ ደመወዝና ላለበት የተለያዩ ዕዳዎች የሚከፍለው ገንዘብ በማጣቱ ምክንያት ካለበው ዲቪዚዮን ወደ ታችኛው ዲቪዚዮን የመውረድ ከፍተኛ አደጋ ተጋርጦበት የነበረውን የልጅነት ክለቡን አልባሴቴን ሁለት መቶ ሺ ፓውንድ በመስጠት አለሁልህ ማለቱን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ተጫዋቹ የክለቡ ከፍተኛ የአክሲዮን ድርሻ ባለቤት ሲሆን ከሁለት ዓመታት በፊት በተመሳሳይ አራት መቶ ሺ ፓውንድ ድጋፍ ማድረጉን ዘገባዎቹ አስታውሰዋል።
በፊፋ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ከስፔን ብሔራዊ ቡድን ጋር የአውሮፓና የዓለም ዋንጫ ያነሳው የ29 ዓመቱ ኢኔሽታ በአልባሴቴ እግር ኳስ ክለብ ሁለት ዓመት ቆይቷል።
በተያያዘ ዜና የባርሴሎና የከተማ ተቀናቃኝ የሆነው የስፓኞል እግር ኳስ ክለብ ፐሬዚዳንት ዮአን ኮሌት ባርሴሎና ታዳጊ ተጫዋቾቻችንን ከአካዳሚያቸው አላግባብ ከመውሰድ ሊቆጠብ ይገባዋል ማለታቸውን ዴይሊሜል ዘግቧል።
የእስፓኞል የወጣቶች አካዳሚ አባላት የሆኑ አምስት ተጫዋቾች በቅርቡ አላግባብ በሆነ መንገድ ባርሴሎናን መቀላቀላቸውንም ዘገባው አመልክቷል።

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop