“በአማራ ብሄር ተወላጅ ወገኖቻችን በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል እየደረሰባቸው ያለው ዘግናኝ ጭፍጨፋ ኣጥብቄ እኮንናለው” አምዶም ገብረሥላሴ

ይህ ዜጎች ባገራቸው ይህ የመሰለ ጭፍጨፋ መካሄዱ እጅጉን የሚያሳዝንና የሚያሳፍር ሰብኣዊነት የጎደለው ተግባር ነው።
መንግስት ለዚህ ኣስደንጋጭና ዘግናኝ ተግባር ሃላፍነት በመውሰድ ወንጀሉ በኣስቸኳይ እንዲያስቆመውና ወንጀለኞች ለፍርድ እንዲቀርቡ ማድረግ ኣለበት እላለው።
(ከዚህ ቀደም ከጉራ ፈረዳ የተፈናቀሉ አማሮች፡ ፎቶ ፋይል)
ዜጎቻችን በስደት ሳውዲ ዓረብያ፣ የመን፣ ደቡብ ኣፍሪካ፣ ሊብያ፣ ደቡብ ሱዳንና ቤሩት የመሳሰሉ ሃገራት፤ በቀይ ባህር፣ ሜድትራንያን ባህር፣ በሲናይና ሰሃራ በረሃዎች እየደረሰባቸው ያለው መቅዘፍት ሳይበቃ በገዛ ሃገራቸው ይህን የመሰለ ሰቅጣጭ ጭፍጨፋ ሊደርስባቸው ኣይገባም።

ሃገራችን 15 ማልዮን በኣስከፊ ረሃብ በያዘበትና ሂወቱ እያጣበት ባለበት ግዜ ይህን መሰል ወንጀል መፈፀሙ የሚዘገንን ብቻ ሳይሆን የሚያሳፍር ወንጀል ነው።

ብኣዴንም እወክለዋለውና ኣስተዳድረዋለው የሚለው ህዝብ ኣስከፊ ወንጀለ እየተፈፀመበት እያየ የሰው መሰውያ እንደለመደ ጣኦት ምንም ሳይል ደማቅ በዓል እያሳለፈ መሆኑ ያስገርማል።
የኢህኣዴግ መንግስትም እንደዚህ ዓይነቶች ወንጀሎች የሚፈፅሙ ወንጀለኞች ይዞ ለፍርድ የማያቀርብ ከሆነ ኣስፍኘዋለው የሚለው ሰላም ከመደፍረሱ በላይ የወንጀሉ ተባባሪና ቁጥር ኣንድ ተጠያቂ ያደርገዋል።
መንግስት ወንጀለኞች ባስቸኳይ ለህግ ያቅርብልን !

ተጨማሪ ያንብቡ:  እኔን እሰሩኝ! ልጆቼን ልቀቁ ! - ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ አቡነ አብርሃም

3 Comments

  1. Kkkkkk keldegnaneh bakih man honena aschefchafiw maskom alebet eyalik yemitkeldew
    Tigre mehonun adelem ethiopiawi lelaw alem yawkal ye ethiopia hizb aydelem sew(hizb)
    yedur ensisa atgdelu tebilenal bilew aygelum.
    lemangnawm ene amidom gudgudun betam arkachu kofrchwtal yasebachiwtn bicha laymolaw yichilal enantem tezegaju

    Tekawami mustachw hizbn lematalel yemitadergut enkskasi $$$$$$$$

  2. Amhara people will be exterminated by its deadliest enemies like Tigres , Eritreans and OLF Oromos unless they organize themselves

Comments are closed.

Share