June 19, 2013
4 mins read

ፓርላማው የሚኒስሮች ም/ቤት መመልከት የሚገባው ረቂቅ አዋጅ ላይ መወያየቱ ጥያቄ አስነሳ

– የአካባቢና የደን ሚኒስቴር ሊቋቋም ነው
– የሁለት ሚኒስቴር መ/ቤቶች ስያሜ ይሻሻላል

በፍሬው አበበ

የሕዝብ ተወካዮች ምክርቤት በውክልና ለሚኒስትሮች ም/ቤት የሰጠውን ሥልጣን ሥር የሚወድቀውን ረቂቅ አዋጅ እንዲያጸድቅ መቅረቡ ጥያቄ አስነሳ።
ፓርላማው በትላንት ውሎው የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ታጥፎ “የአካባቢና ደን ሚኒስቴር” የተባለ አዲስ ሚኒስትር መ/ቤት እንዲቋቋም፣ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴርን “የከተማ ልማት፣የቤቶችና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር”፣ ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር “የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር”፣ በሚል ስያሜው እንዲቀየሩ የአስፈጻሚ አካላትን ሥልጣንና ተግባር ለመወሰን በተዘጋጀውን ረቂቅ አዋጅ ማሻሻያ ውስጥ ቀርቦለት ተወያይቶበታል።
የአንድነት ፓርቲ ተመራጭ የሆኑት አቶ ግርማ ሰይፉ ባቀረቡት አስተያየት የአስፈጻሚ አካላትን ሥልጣንና ተግባር ለመወሰን የወጣውን አዋጅ ቁጥር 691/2003 አንቀጽ 34 የፓርላማው ሥልጣን ለሚኒስትሮች ም/ቤት እንዲተላለፍ በአብላጫ ድምጽ መወሰኑን አስታውሰው የፌዴራል አስፈጻሚ አካላትን እንደገና ማደራጀትን በተመለከተ ይህ አንቀጽ “የሚኒስትሮች ም/ቤት አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው ደንብ በማውጣት፣ ማንኛውም አስፈጻሚ አካል እንዲታጠፍ፣ ከሌላ ጋር እንዲዋሃድ ወይም እንዲከፋፈል በማድረግ፣ ተጠሪነቱ ወይም ሥልጣንና ተግባሩ እንዲለወጥ በማድረግ ወይም አዲስ አስፈጻሚ አካል እንዲቋቋም በማድረግ የፌዴራል አስፈጻሚ አካላትን እንደገና የማደራጀት ሥልጣንና በዚህ አዋጅ ተሰጥቶታል” በሚል መደንገጉን በማስታወስ ይህን አዋጅ የማጽደቅ ሥልጣን አለአግባብ ወደሚኒስትሮች ም/ቤት የተዛወረ ቢሆንም ህግ በመሆኑ ይህ ም/ቤት አዋጁን ለማጽደቅ ሥልጣን አለው ወይ የሚል ጥያቄ አዘል አስተያየት አቅርበዋል።
ዶ/ር አሸብር ወ/ጊዮርጊስ በበኩላቸው በተለይ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር የሚለው ስያሜ ወደ ከተማ ልማት፣ የቤቶችና የኮንስትራክሽን ሚኒስቴር የተቀየረበት አግባብ ግልጽ እንዳልሆነላቸው ተናግረዋል። “ኮንስትራክሽን” የሚለው ቃል ቤቶችንም እንደሚመለት የጠቀሱት ዶ/ሩ ማብራሪያው ላይ ገጠሩንም ለማካተት መታሰቡን መመልከቱን አስታውሰው ይህ ከሆነ መባል ያለበት የከተማና የገጠር ልማት የኮንስትራክሽን ሚኒስቴር ነው ብለዋል።
የአደረጃጀት ለውጥ በዚህ ወቅት ማድረግ ለምን አስፈለገ የሚሉ ጥያቄ አዘል አስተያየቶችና ከዕድገትና ትራንሰፎሜሽን ዕቅዱን ለማሳካት አደረጃጀቶች ከላይ እስከታች ተዋቅረው ርብርብ በሚደረግበት በዚህ ወቅት አዲስ አደረጃጀት መምጣቱ ሥራውን ሊጎዳው አይችልም ወይ የሚሉ ሥጋቶች በም/ቤት አባላት ተንጸባርቀዋል።

ምንጭ ሰንደቅ ጋዜጣ

1 Comment

  1. ” GULECHA BIQEYER WOT AYATAFTEM” you can’t develop the country by changing names after names,this shows the so called parliament doesn’t have a better things to do.

Comments are closed.

Previous Story

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ደጋፊዎችን ልፋት፣ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አፈር ድሜ አስጋጠው

Next Story

የጁነዲን ሳዶ ባለቤት ወ/ሮ ሀቢባ መሐመድን ጨምሮ የ32ቱ ሰዎች ክስ ለሕዝብ ክፍት እንዲሆን ጠበቆቹ ጠየቁ

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop