June 18, 2013
7 mins read

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ደጋፊዎችን ልፋት፣ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አፈር ድሜ አስጋጠው

ከግርማ ደገፋ ገዳ (ጋዜጠኛ)
ደስ ይበልህ ፌዴሬሽን!
ሁሌም ውርደት የማያጣው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን፣ ዘንድሮም እንደለመደው አሳፋሪ ቅሌት ለመላ ኢትዮጵያ የስፖርት አድናቂ አከናነበ! ይህ እጅግ አሳፋሪ ነው! ሁሉ ነገር ከአፍሪካ አንደኛ የማለት ነገር ይቀናናል። ይህስ ከአፍሪካ ስንተኛ ውርደትና ቅሌት ነው? ለአውሮፕላን፣ ለሆቴል፣ ለማሊያ፣ ለጫማ፣ ለመከላከያ እና ለመሳሰሉት ነገሮች በሙሉ የወጣው ወጭ አፈር ድሜ ጋጠ! ከሁሉም በላይ የደጋፊዎች በዋጋ የማይተመን ድጋፍና የኢትዮጵያ እግር ኳስ ስፖርት የላቀ ደረጃ ላይ ደርሶ ለማየት የመጓጓቱን ሕልም፤ የትም ቀበሩት። የፊፋን ሕግ አሳምረው በማያውቁና የተጫዋቾቻቸውን ሪከርድ መመዝገብ በማይችሉ ስግስብግ ግለሰቦች የተሞላው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን፣ የሀገራችንን ስፖርት በቁሙ ቀበረው። በደስታ ብዛት መኪና ላይ ሲፎልሉ የነበሩ ወጣቶችን የጫነ መኪና ሲገለበጥ፣ ለሞቱ ዜጎችም አንዱ ምክንያት በእግር ኳሱ የተገኘው ድል ነበር። በስንት ድካም የተገኘው ነጥብ ለቦትስዋና የሚሰጥ ከሆነ፣ ለፌዴሬሽኑ ሰዎች ዳንኪራ ሆነ ማለት ነው፤ ለደጋፊዎች ግን ለቅሶ! እንግዲህ ስፖርት አፍቃሪ ምን ይሻልሃል? ከወደ ኋላ ሆኖ ወጥሮ የሚይዘው አስራት ባልቻ እና የሚያቀብላቸው ኳሶች በሙሉ ቁም ነገር ላይ የሚደርሱለት እድለኛው አዲስ ህንጻ፣ ያ ሁሉ ትግላቸውን፤ የፌዴረሽን ጅብ በላው!
ደስ ይበልህ ፌዴሬሽን!

በዚህ ዙሪያ የመንግስት ሚድያዎች ዘገባ የሚከተለው ነው፦
ኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ምንያህል ተሾመ ሁለት ቢጫ ካርድ አይቶ ሳለ ሰኔ 1/2005 ከቦትስዋና ብሄራዊ ቡድን ጋር በተደረገው ጨዋታ መሰለፉ ስህተት እንደሆነ አመነ፡፡

ፌዴሬሽኑ ብሄራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ አቻው ጋር ከመጫወቱ በፊት ችግር ስለመፈጠሩ ፊፋ አሳውቆት እንደነበር ገልጿል፡፡

ሆኖም ይህ ችግር በቡድኑ ተጫዋቾችና በደጋፊዎች ላይ ያልተፈለገ የመንፈስ ጫና እንዳይፈጥር በመስጋት መረጃውን ይፋ ሳያደርግ ቆይቷል፡፡

ፌዴሬሽኑ በፈጠረው ችግር ዙሪያ ዛሬ ሰኔ 11/2005 ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ መሰረት ፊፋ ተጫዋቹ ሁለት ቢጫ ካርድ በማየቱ የተነሳ ከቦትስዋና ጋር በተካሄደው ጨዋታ እንዳይሰለፍ የሚገልፅ ደብዳቤ ለፌዴሬሽኑ ልኳል፡፡ ይሁንና የፌዴሬሽኑ አመራሮችና አሰልጣኝ ይህን የፊፋ ውሳኔ በመዘንጋታቸው ተጨዋቹን አሰልፈውታል፡፡

የፌዴሬሽኑ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ለችግሩ ተጠያቂ ያላቸውን ግለሰቦች ዝርዝርም ይፋ አድርጓል፡፡ በዚህ መሰረት የፌዴሬሽኑ ምክትል ፕሬዝዳንትና የብሄራዊ ቡድኑ ቡድን መሪ አቶ ብርሀኑ ከበደ፣ ዋና አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው፣ አሰልጣኝ ስዩም ከበደ፣ የቡድኑ ተጨዋች ምንያህል ተሾመ፣ የስራ አስፈፃሚ አባልናየቡድን መሪ የነበሩ አቶ አፈወርቅ አየለ እና የፌደሬሽን ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አሸናፊ እጅጉ በጥፋተኝነት ተፈርጀዋል፡፡

በፊፋ ህግ መሰረት ተገቢ ያልሆነ ተጨዋችን ማሰለፍ በጨዋታው የተገኘውን ነጥብ የሚያሳጣና ተጨማሪ የገንዘብ ቅጣትም የሚያስጥል ነው፡፡

በዚህመሰረትም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን 3 ነጥብና 6 ሺህ ስዊስ ፍራንክ እንደሚቀጣ ፊፋ ያስታወቀ ሲሆን በጉዳዩ ላይ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን እስከ ሰኔ 14/2005 ዓ/ም ምላሽ እንዲሰጥም በፃፈው ደብዳቤ አስታቋል፡፡

አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው በተፈጠረው ስህተት የተሰማቸውን ሀዘን ገልፀው ጳጉሜ 2/2005 ከማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ጋር ለሚካሄደው ጨዋታ ከወዲሁ መዘጋጀት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

በዚህ ጨዋታ አሸንፈን ወደ መጨረሻው የአለም ዋንጫ ማጣሪያ እንደምናልፍ እርግጠኛ ነኝ ብለዋል አሰልጣኙ፡፡ለዚህም የቡድኑ አባላት ዝግጁ መሆናቸውን አሰልጣኙ አረጋግጠዋል፡፡

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ፕሬዝደንት አቶ ሳህሉ ገብረወልድ በበክላቸው በአሰራር ክፍተት የተፈጠረው ችግር አሳዛኝና ሊከሰት የማይገባው ጉዳይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የፌደረሽኑ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ጥፋተኞቹ ተገቢውን ቅጣት ማግኘት እንደሚገባቸው የተስማማ መሆኑን በመግለፅ በአጭር ጊዜ ውስጥ የቅጣት ውሳኔውን ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግም አስታውቀዋል፡፡

ፌዴሬሽኑ በተፈጠረው ችግር ከፍተኛ ሀዘን እንደተሰማው ገልፆ ለኢትዮጵያ ህዝቦችም ይቅርታ ጠይቋል፡፡

13 Comments

  1. Here we go again! when we hear something good, there is always bad thing behind it…what a shame. they all need to get fired..they got the letter but they just doesn’t care? this is woyanes thinking… they all need to GO…

  2. እንዲህ የመሰለ ስሕተት እንዴት ሊፈጸም እንደ ቻለ መገመት ቀላል ነው። ኮ/ል አወል አብዱራሂም የደደቢት ክለብ መሥራችና ባለቤት ናቸው። ምን ያህል ተሾመ በየነ የደደቢት ቡድን ተጫዋች ነው። ለብሔራዊ ቡድን ከሚሰለፉት አብዛኛዎቹ ከደደቢት ነው። ኮ/ል የህወሓት አባልና ታጋይ ናቸው። ደደቢት ክለብ ማለት ገንዘብ ማለት ነው። ፌዴሬሽኑና የመንግሥት አካላት በሙስና ለመዘፈቁ ምንም ማስረጃ ማቅረብ አያሻኝም። ሯጮቻችን ለአገራቸው እንደ መሮጥ ለአረብ አገሮች የሚሮጡት ፍትሓዊ አመራረጥና ድልደላ ስለሌለ ነው። አመራሩ ላይ የተሰየሙትን ባለሥልጣኖች ስም ይመልከቱ። በፌዴሬሽኑ ሆነ በመንግሥት ዘንድ የኮ/ል ተሰሚነት እንደ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ነው የሚሉ ቢኖሩ ወይ አታላዮች ናቸው ወይም ጅሎች ናቸው። አሁን የሚደረገው ሙከራ የምንያህል ስም ስለ ተቀያየረ አሳስቶ ነው ለማሰኘት ሙከራ እየተደረገ ነው። የአገርን ያህል ክብርና የሕዝብን ሞራል ሥራቸውን በግል ጥቅም በለወጡ ሰዎች ማበላሸት ማለት ይኸው ነው። ገና ምኑ ታይቶ? እስካሁን ያልተከሰቱ ስንት አሉ? ሕዝብ ዝም ብሎ ማለፍ የለበትም። ጥያቄው እስኪመለስ በዚህ ጉዳይ በንዝህላልነት ይሁን አውቀው በደል የፈጸሙ በሕግ መቀጣት ይኖርባቸዋል።

  3. እንዴት አንድ እንኳን ጋዜጠኛ ነቄ አለለም ነበር እስካሁን? ስንቱ ኤክስፐርት ነኝ እያለ ይፎግረን የለ እንዴ?

  4. No, no, no. These guys should be fired immediately including Sewinet Bishaw as they have committed a grave and unforgivable mestake.Neither of them should participate nor lead the team in the next match.The team can play without the main and assistant coach. They must also pay the fine FIFA will impose on the Federation by witholding thier compensation. The Federation Board need to announce it’s ruling sooner than later and the public must push towards this.
    How do these guys lead the team without even knowing the FIFA match regulation. Shame and shame on the Federation leadership all which has the ultimate responsibility to prevent such neglect.

  5. If you claim being ETHIOPIAN from now on for two years don’t go to the stadium don’t participate in cheering the team I know the sound is cruel but to punish these weyan’s cadres other wise they don’t learn from their mistakes follow the event through medias that is all. we tried our best to cheer to support our national team look what has happened therefore instead of disappointing your self at the end take action with my idea and we will see the result.

  6. this is the result of woyanne.will show you clearly that the country is run by the people who don’t have any knowledge for what they work. i fill sorry for the people
    who have been celebration the all night like me.

  7. This is the work of Tigre people liberation front who hate to see the Ethiopian people smiling and celebrating a national success.

    You remember when the Ethiopian army routed shabia and was marching towards asmara, TPLF ordered the Ethiopian army to turn back and to stop the offensive. 100s of 1000s of our compatriots were massaacred in a senseless war and TPLF were cheering.

    It is the same situation here in the football. When we are nearing success, TPLF comes along and stop our progress. The woyane hate to see the Ethiopian people gathering on big crowds and singing the praises of Ethiopia. THE woyane see the rising sense of Ethiopian nationalism as a threat and would do anything possible to stop it.

  8. I feel sorry fo Ethiopian Football fans. They should deserved special prize for their support.
    They are supporting a wrong team and a bunch of IDIOTS STAFFS. THE MOST STUPID FOOTBALL COACH AND HIS STUPID STAFF MEMBERS. I see also an IRRESPONSIBLE and EGOIST player who even doesn’t remember or will not want to remember, how many times he saw yellow cards in his previous games. So, I thought these squad is smart enough and experienced to qualify for the final, well, you want to prove us the opposite. NO, Pleaese! How come, no single player could REMIND THIS RETARDED AND MORON “COACH!” Atleast, one of you players should have insised him to know the statistics of the tournaments as one of his primary jobs. Doesn’t he know the ABC of FIFA game rules? This is outragous. First learn the rule of the game then you should try to COACH others.

  9. our ” sport journalists ” calling yourself “experts””who are talking non stop on your FM programs and ETV where are you ? , deaf _mute EFF authorities and coachs . Do you know that what you did is highly questioable ? You will pay a price. .Don’t talk down.MAFERiAYA MAfIAS !

  10. የነ ይድነቃቸው ተሰማ አጥንት እሾክ ሆኖ ይውጋችሁ እናንተ በዘር የሰከራችሁ ጅቦች

  11. Birds of the same feather fly together. Nowadays, it is very simple to kill a nation and say “I am sorry for what happened”. This is what our leaders taught us. The cadres kill human being, loot the nations wealth, engulfed in corruption and during the evaluation drama They say we are sorry, we learn from our mistake….. and the boss will say “these people have accepted their mistake and the EPRDF’s aim is to teach people…. and gives them another chance to kill, loot and embezzle the nation’s wealth.
    Do these Federation leaders understand the meaning of execuse? How can you fool a nation? This shows their conclusion about Ethiopians. Remember last time when Siyum Mesfin show on ETV and told Ethiopian people about the decision made about Badme. He said “Badme has been given to Ethiopia” while he knows the actual decision, he fooled the Ethiopian People. Again, they urged Ethiopian people to rally for the decision and the poor Ethiopians demonstrated. But we remember the final result. Thanks EPRDF, you have taught us how we can lie and feel no shame.
    Shame on all those who are playing game with Ethiopians

  12. Jesus Christ ! what a bunch of losers ! The Ethiopian football federation “president himself should be resigning or Fired with all the air head staff of the federation !! They ‘forgot’ the letter from Fifa? are we a “Banana republic” already??? Fire all of them to hell !!!

  13. realy amaizing,this is Ethiopian Football faderation mistck is not Meniahile bcz Meniahile one of z best player in Ethiopian team so this person not registerd Read & yellow card, this is ferderation mistck.all Ethiopian’s please stand …………..,what do you do Ethiopian football federation ?

Comments are closed.

Asegd2
Previous Story

አስገደ ገ/ስላሴ ለህክምና አሜሪካ ገቡ

Next Story

ፓርላማው የሚኒስሮች ም/ቤት መመልከት የሚገባው ረቂቅ አዋጅ ላይ መወያየቱ ጥያቄ አስነሳ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop