ስለዐባይ መገደብ ጉዳይ እኔም የምለው አለኝ ( ከቃል-ኪዳን ይበልጣል)

The Nile River has become a point of contention between Egypt and Ethiopia.
( ቃል-ኪዳን ይበልጣል)
ሰሞኑን ኢትዮጵያውያንን አነጋጋሪ ሆኖ ያለው የዐባይ መገደብ ጉዳይ ነው፡፡ አንዳንድ ወገኖች ሁኔታውን ከቀኝ ከግራ፣ከፊት ከኋላ ሳያዩ ከመለስ ዜናዊ ድንክዮች ባላነስ መንገድ መገደቡ ትክክልና ተገቢ እንደሆነ ሲጸፉና ሲናገሩ ይሰማል፡፡ ይህ ሊደንቀን አይገባም፡፡ የነዚህ ዓይነት ሰዎች አቋም አንድም ግድቡ ስለሚኖረው ኢኮኖሚያዊ፣ፖለቲካዊ፣ማኅበራዊና በህላዊ ጉዳዮች ባይተዋሮች ናቸው፡፡ ሁለትም “እናቴን ያገባ ሁሉም አባቴ” ነው በሚል እሳቤ ወያኔን ኢትዮጵያዊ መንግሥት አድርገው የተቀበሉ ናቸው፡፡ ሦስትም የስደት ኑሮ ከብዷቸው ከወያኔ ጋር መግባቢያ መሰላል እየሠሩ ናቸው፡፡ ይህን ያልተገነዘቡና የወያኔን የቆረጣ የትግል ሥልት ያልተረዱ ወገኖች ለምን በዚህ ወቅትና ሰዓት የዐባይ መገደብ ጉዳይ አጀንዳ ሆኖ ቀረበ? ብለው ሳይጠይቁና ዕውነታውን ሳይረዱ፣ ዐባይ መገደቡን መደገፍ አለብን ይላሉ፡፡
በሀሳብና በአመለካከት ደረጃ ዐባይ መገደብ የለበትም የሚል ኢትዮጵያዊ ይኖራል ተብሎ አይገመትም፡፡ ጥያቄ የሚነሳው ዕውን ወያኔ ለኢትዮጵያ አንድነት፣ለሕዝቡ ሉዐላዊነት፣ብሔራዊ ጥቅምና ብልጽግና የቆመ ነው? ይህን ግንባታ ለመገንባት የተነሳሳው የኢትዮጵያን ሕዝብ በዐባይ ተጠቃሚ ለማድረግ አስቦ ነው? ወይስ ከኋላው ሌላ ምክንያቶች አሉ? የኢትጵዮጵያን የባሕር በር ፈቅዶ የሰጠ፣የኢትዮ-ኤርትራን ጦርነት ድል በአልጀርስ ስምምነት አሳልፎ የሰጠ፣የአገሪቱን ምዕራባዊ ዳርቻ 1600 ኪሎሜትር ርዝመት፣50 ኪሎ ሜትር ጥልቀት ለሱዳን አሳልፎ የሰጠ፣ከ7 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በላይ ለቱርክ፣ለሳውዲ ዐረቢያ፣ለቻይና፣ወዘተ ባለሀብቶች ለሄክታር በአንድ ዶላር ሂሳብ ለ99 ዓመታት የሸጠ፣የአገሪቱን ታሪክና አንድነት የካደ፣የመነጣጠያ ሕገ-መንግሥት ያዘጋጀ፣ባገሪቱ ካሉ ከፍተኛ ቁጥር ካላቸው ነገዶች መካል አንዱ የሆነውን የዐማራ ነገድ የዘር ማጽዳትና የዘር ማጥፋት ወንጀል የፈጸመ አካል ዐባይን በመገደብ እንዴት ኢትዮጵያን ተጠቃሚ ያደርጋል ብሎ ማሰብና ማመን ይቻላል ? በአሁኑ ወቅት ወያኔ እየደረሰበት ያለውን የሕዝብ ተቃውሞ አቋም ለማብረድ የአቅጣጫ ማስለወጫ አጀንዳ አለመሆኑን በእርግጠኝነት እናውቃለን ወይ ? ወደ ውሳኔ ከመድረሳችን በፊት ለእነዚህ ጥያቄዎች ተገቢ መልስ ማግኘት ያለብን ይመስለኛል፡፡
በሁለተኛ ደረጃ ዐባይ ይገደብ አይገደብ ከሚለው መደምደሚያ ከመደረሱ በፊት ለሚከተሉት መሠረታዊ ጥያቄዎች አዎንታዊ መልሶች ማግኘት ያለብን ይመስለኛል፡፡ እነዚህም፡-
1. ኢትዮጵያ ተብላ ለዘመናት በዓለም ካርታ የምትታወቅ አገር ዛሬ በድሮ ወርድና ቁመቷ አለች?
2. የአንድን አገር ምላተ ሕዝብ ተሳትፎ የሚጠይቅን ተግባር ለማከናወን በቅድሚያ ከዕቅድ ዝግጅ እስከ አፈጻጸም ሕዝቡ መሳተፍ የለበትም ?
3. የሕዝቡን ቁሳዊና ኅሊናዊ ሀብት በሚፈለገው ደረጃ ለማግኘት ሕዝቡ የኔ የሚለው የመንግሥት አደረጃጀትና አመራር አለ ብሎ ያምናል?
4. ዐባይን ለመገደብ የታሰበው በዕውነት ለልማት ታስቦ ነው? ወይስ የሰሜን አፍሪካ ሕዝብ አመጽ ወደ ኢትዮጵያ እንዳይሸጋገር የአመለካከት ለውጥ ለመፍጠር ነው?
5. ዐባይ ይገደብ ከተባለስ መገደብ ያለበት ቦታ የት ቢሆን ነው ለሕዝቡ ዕከል ተጠቃሚ፣ለግድቡ ደህንነት አስተማማኝ የሚሆነው?
6. ዐባይን ያህል ግዙፍ ግድብ ከመገደብ መካከለኛና ዝቅተኛ ግድቦችን መገደብ የበለጠ ውጤታማ መሆን አይቻልም ነበር ወይ?
7. የጣና በለስን ፕሮጀክት ዘርፎና አውድሞ ቤንሻንጉል ጉምዝ ላይ ከሱዳን ደንበር የቅርብ ርቀት ላይ ይህን ያህል ግዙፍ ግድብ ለመገደብ የታሰበው ዕውነት የኢትዮጵያን ሕዝብ ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሌሎች አማራጭ ቦታዎቸ ጠፍተው ነው ? ወይስ በግንባታው ሊጎዳ የተፈለገ አካባቢ አለ?
8. ከለጋሽ እና አበዳሪ መንግሥታና ድርጅቶች በኢትዮጵያ ሕዝብ ስም ያገኘውን ብድርና ዕርታ በሙስና የወያኔ አባሎችን ተጠቃሚ ያደረገ አመራር መሆኑ እየታወቀ ለግድቡ ሥራ ከሕዝብ የሚሰበሰበው ገንዘብ ለተባለለት ዓላማ ስለመዋሉ ምን ዋስትና አለ?
9. የዐባይ ገባር ወንዞች በአመዛኙ ከጎጃም፣ከጎንደር፣ከሰሜን ሸዋ እና ከወሎ የሚነሱ ናቸው፡፡ ግድቡ እንዲሠራ የተፈለገው ከእነዚህ ክልሎች ብዙ እርቆ ነው፡፡ በግድቡ መሠራት ምክንያት እነዚህ የዐባይ ገባር ወንዞች ባለመብት የሆኑ አካባቢዎች በገባር ወንዞቹ ላይ የመጠቀም መብታቸውን አይከልልም ወይ?
ለእነዚህና መሰል ጥያቄዎች ተገቢ መልስ ሳንሰጥ፣ ዐባይ ይገደብ ወይም አይገደብ ብለን አቋም መያዝ ተገቢም ትክክልም አይመስለኝም፡፡ ለእነዚህ ጥያቄዎች አጥጋቢ መልስ ሳንሰጥ በስሜት ዐባይ ይገደብ ብንል ሁለት መሠረታዊ ስሕተቶችን እንሠራለን፡፡ አንድ ለወያኔ ዕድሜ ማራዘሚያ እንሆናለን፡፡ ከኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ድጋፍ ትምህርት መቅሰም ያለብን ይመስለኛል፡፡ በወያኔ አመራር የኢትጵዮያ ብሔራዊ ጥቅምና የሕዝቡ መብት ይጠበቃል ብሎ ማሰብ ሸንበቆ ያፈራል ብሎ እንደማመን ይቆጠራል፡፡ ሁለት የተቃውሞው ጎራ ይከፋፍላል፡፡ በዚህም ተጠቃሚው ወያኔ ይሆናል፡፡
በሌላ በኩል የዐባይ መገደብ አለመገደብ የተቃዋሚው አጀንዳ ሊሆን አይገባም፡፡ የመገደቡም ሆነ ያለመገደቡ አጀንዳ የወያኔ ነው፡፡ ተቃዋሚው ድምፅ ሊሰጥ፣ሐሳብ ሊያቀርብ በማይችልበት ሁኔታ ውስጥ መኖሩ እየታወቀ፣ በጠላት አጀንዳ ውስጥ ገብቶ የራሴ የሚለውን መጣል ተገቢም ትክክልም አይሆንም፡፡ ለምን በወያኔ አጀንዳ ራስችን እንጠምዳለን?
ተቃዋሚ ሲባል የመጀመሪያ ተግባሩ የሚቃወመው አካል የሚሠራቸውን አገርና ሕዝብ ጠቀም ያልሆኑ ተግባሮች በመረጃ ማጋለጥ ነው፡፡ የዐባይ መገደብ በተቃዋሚው አመለካከት ተገቢ ከሆነ የጀመረው አካል ይግፋበት፡፡ አንድ መንግሥት ነኝ ያለ አካል መሥራት የሚገባውን ሥራ መሥራቱ እንደ ልዩ ተአምር መታየት የለበትም፡፡ የተቃዋሚው ትኩረት መሆን ያለበት የሚሠሩ ሥራዎች በትክክል አገርና ሕዝብ ጠቀም መሆናቸውን በማረጋገጥ፣ጎጅ የሆኑትን ተግባሮች ማውገዝ ነው፡፡ ሲያቅድ ፣ሲጠነስስ ሕዝብ እንዲመክርበት ያላደረገ፣ሕይዎት የሚያስጠይቅ ጉዳይ ሲገጥመው ድረሱልኝ ሲል ፣ጥና ጠሪ መሆን ከተቃዋሚ የሚጠበቅ አይመስለኝም፡፡ መሆን ያለበት የሚቃወመው አካል ችግር ሲገባ፣ለችግሩ መውጫ አማራጭ ሐሳብ ይዞ ሕዝብ እንዲከተለው ማነሳሳት ነው፡፡
ቸር ይግጠመን!

ተጨማሪ ያንብቡ:  የሙሶሊኒና የቫቲካኑ ፖፕ ፓየስ 11ኛ ፋሺሽታዊ ሕብረት ሐቅ የቀድሞ አምባሳደር፤ ዘውዴ ረታ፤ ቫቲካንን ከኃላፊነት ነጻ ለማድረግ ስላደረጉት ሙከራ

20 Comments

  1. Ato Tekile ere eyetestewale !!!!

    lebelwat yasebuwaten Amora yeluwatal Jigra endayhon !!

    yelelawenem Hasab yakberu enji !

  2. Egypt sematu bemin mengad endmematu beyfa be television negrawnal Ena aydenkanim Ethiopia always ready.

  3. indeed these questions must answered to debate whether the dam should be built or not. Thanks

  4. you said it all, if we trust weyane we all going down to the drain please people stop being emotional and think why weyane try to build this big dam with out having even half of the money? they tried their best for us to fight each other by ethnic religon they couldn’t succeed therefore they have to put the whole country in war so they can exit easily from ETHIOPIA and live the comfortable life abroad with the money they stole already.

  5. This Amahra elite unless everything done by themselves and hold power in 4 kilo, they carry out 1969 old poltics of zero sum. For them Ethiopia is from Gonder to Addis Ababa. Excluding the opnion of other people Tigray, Oromo people, Somale people, Sidama people, and Welayita people. Moreovere they have looked down Benshangul people as the part of Ethiopia and opposes development in this forgotten nation during the Amahra reign of Hailslasse and Derg . But Personally I hate ethinics politics. Ethiopa is not from Gonder to Addis Ababa. You can oppose Weyane on dimocratization process, but Donot use Abay to come to power and and learn from your mistake as using your slogan one country, one language,one religion

  6. You diasporas playing zero sum poletics. What is the benefits of opposing every thing? We Ethiopian (those who live in country) suffered by woyane, but we need road, education and health institution…. Who ever did it he is well come. However, we can not stop asking poletical right.

  7. Abay aygedeb bemilew ajenda alismam. Yihin tsuhuf yatsafe sew endemigebagn ye Abay lemin Benishangul tegeneba yemil andmita yalew enji minm hagerawi simet bewustu yelele cifin tilacha new. Ende ethiopiyawi honek kasebk weyane ena Abay minm ayigenagn weyane lezelalem aynorm Abay gidib gin letiwild hulu new. Zim bileh chifin atihun.

  8. the most rustic boy,Kalkidan ybeltal,go to the hell,u have to learn from past mistakes,Ethiopia has been devastating by drought,ignorance,deaths etc during the Amhara Regime,now it is time to getup together bro,God bless u.

  9. what Dear Ayalsew Dessie said is correct and his article was well researched and he looked from different angles not one sided. after I read his article I convinced . we oppose woyane until the end but we will not loose this golden opportunity.for every thing there is a time and season.if its possible Media like ESAT and Zehabesha should arrange for the debate about the Nile dam.

  10. u stonehead don’t u think that benishangul is part of homeland,the dam can built where ever if it has benefit arguing about it’s site indicates your narrow,spoiled & tribal mind.shame on u.

    • Hello dear i did’t feel any thing by ur vomt still my concern is u can oppose weyane’s policy and it’s stupid politics but u never can’t oppose national development. Still many people are crying for power by opposing every things which have been done by leading party.

  11. I agree with Tazabi in which those who live inside Ethiopia need basic needs such as education, health care and electricity even in a difficult political environment. But, the problem is those who live overseas give priority to only their political end in which to condemn all things the present government does without considering the actual benefits of a particular issue. The failure of the ethiopian opposition to understand that dictatotrial and oppressive regimes can proceed and implement economic activities which might benefits the people and the country undermine their support from the people in which directly benefit from these projects. South korea with military regime previously, Singapore with one party oppressive regime and china with the communist government advanced significant economic achievements in the last thirty years. Based on this, our opposition groups and individuls should consider their opposition by examining each particular issue and consider the interests of people back home. By. Opposing the dam we are saying to the people back home you can live with darkness, you can live without electtricity to cook your food or you can stop building new manufacturing sectors until we are free from this oppressive woyane government. Instead of doing this, We can still oppose the failure of this government by highlighting the failure of its policies regarding advancing democracy, imprisoning journalists and it’s failure in keeping the interests of all ethiopians. Please don’t oppose in the sake of opposing everything without prior consideration of a particular issue. life should continue for ethiopians even in the difficult kind of circumstances until they get the government they want and need.

  12. ከፀሀፊዉጋር፡የምስማማበት፡ጉዳይኢህአዴግ፡የግድቡን፡ግንባታ፡ለፖለቲካዊትርፍ፡ማጋበሻነት፡ሊጠቀመዉ፡መድፈሩ፡ጥቂቶች፡መር፡አመራሩን፡ሊከላከልበት፡አንባገነናዊስርአቱንእድሜ፡ማራዘሚያነት፡ኢፍትሀዊ፡ሀብት፡ክፍፍሉንሙስናዉን፡ሊሸፍንበት፡በሀይማኖት፡ጣልቃበመግባቱ፡የተነሳበትን፡ተቋዉሞ፡ሊያበርድበት፡ተቃዋሚዎችን፡በጠላትነት፡ሊፈርጅበት_አንድነገርማለት፡ቢቻል፡አባይ፡ከሚያስፈልገን፡በላይ፡ነፃነታችንን፡እንፈልገዋለን፡

  13. I agreed 100% with your ideas.I also want to say that the war never erupted between the two countries.It is a poltical game or what we learned from the past history of woyane and if the situation aggravated and jeoparadise to the woyane central government.The woyane will accept the Egyptian interest with out a pre-condition.Like the previous treaties that had signed between Sudan and Ethiopia and Ethiopia and Eritrea.The woyane government easily hand over the vast amount of land to Sudantha historically and legaly belongs to Ethiopia . the Badme had given to Eritrea under the so-called Algers agreement.from my point of view ,I dont trust the woyane government. I think ,this condition for Ethiopian opposition poltical Parties, it is a wasting time to bring an end woyane,on the other hand,to the existing woyane government ,It is a buying time to strength his poltical power and position and also ,it is a means to crackdown the opposition poltical parties.

  14. We’r tired of the dirty propaganda of paper tigers, diaspora politicians! Who gonna trust you after seeing how cowards you are during 1997? Btw the location of the dam was well researched and put on the paper long before the time of EPRDF. Get your facts right before embarrassing yourself

Comments are closed.

Share