በኢትዮጵያዊያ የመሳፍንት ዘመን አጭር ታሪክ

ከታክሎ ተሾመ ( አውስትራሊያ)

መምህር ገብረኪዳን ደስታ “ለVOA” ለሰጡት መልስ የግል አስተያየት

ከኢትዮጵያ ረጅም ታሪክ ሳንገባ ለዚህ ጽሁፍ መነሻ እንዲያመች ትንሽ ቀንጨብ ማድረግ አስፈላጊ ነው። በ1529 – 1543 ዓ.ም ኢማም አህመድ የተባለው የአፋር ተወላጅ በሐረር አካባቢ የሚገኙ ደጋፊዎቹን በማስተባበር በመላው ኢትዮጵያ የእስላም መንግሥት ለመመስረት ከፍተኛ ጦርነት አድርጓል። በጦርነቱ ምክንያት በእሰልሞናዊ ገዥዎችና በክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች ላይ ብዙ እልቂት ደረሰ። በዚህ የተነሳ የያሬድ መንፈሳዊ ኪነት እድገት ሳያሳይ በቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢ ብቻ ተወስኖ ቀረ።

ነገ ርግን ከኢማም መሃመድ ጥፋት በኋላ የሰለሞናዊ ሥርወ-መንግሥት የቀድሞ ግዛቶቹን አስመለሰ። ቢሆንም በተደረጉ የእርስ በርስ ጦርነቶች የኃይል ክፍተት የተነሳ ከደቡብ እስከ ምስራቅ ድረሰ የኦሮሞዎች ወረራ ተስፋፋ። የኦሮሞ ወራሪዎች ገዳ በሚባል ስርዓት ሉባ በሚባሉ የጦር አበጋዞች አማካኝነት ጋሻና ጦር ይዘው የአዳልን የአካባቢ ነገሥታት እየወጉ፤ ነዋሪውን እያስለቀቁ በራሳቸው ቋንቋና ባሕል ለማዋሃድ ከፍተኛ ጦርነት አካሂደዋል።

እሮሞዎች ያደርጉት ጦርነት ራሳቸውን ችለው መንግሥት አይመስርቱ እንጂ በደቡብ መሀል አገር የሚገኙ እሮሞዎች፤ ገራጌዎች፤ ከምባታዎች፤ ሃዲያዎች፤ ሲዳማና ሌሎችም ብሄር-ብሄረስቦች ተቀላቅለው ግዛታቸውን ለማስፋት ሞክረው ነበር።

በጦርነቶች ምክንያት በአንድ አካባቢ ይኖሩ የነበሩ ሕዝቦች እየፈለሱ ከሌሎች ጋር በመቀያየጥ አዲስ የአኗኗል ዘቤዎችን በመለማመድ በአሸናፊዎች ተጽኖ ሥር የመውደቅ እጣ ደርሶባቸዋል። በተለይ በምስራቅ አፋር፤ ሱማሌና እሮሞዎች ጐልቶ ይታይ ነበር።

በዘመነ መሳፍንት በኦሮሞ መሪዎች አማካኝነት ይደረጉ የነበሩ ጦርነቶች ከላይ በተጠቀሱት አካባቢዎች ብቻ የተወሰነ አልነበረም። በሽዋ ከነበሩ መንግሥታት ጋር በመመሳሰል አጼ ሱሰንዮስ የተባሉ እሮሞዎችን ይዘው ከጐንደር ነገሥታት ጋር ተዋግተው ጐንደር መንግሥት መስርተው ነበር። በየጊዜው የሚደረጉ የሥልጣን ፉክክሮች የኃይል ሚዛናቸው እያየለ ሲመጣ ዛጉዌዎች የሃይማኖትንና የአገር አመራርን ለሰለሞናዊ ሰርወ-መንግሥት አስተላፉ። በዚህ ጊዜ በሰሜን በኩል አማራና ትግሬ የበላይነት እንዳላቸው በሌሎች ዘንድ ጥርጣሬን እንዳስከተለ ይገመታል።

ከላይ የተጠቀሰውን አጋጣሚ በመጠቀም ቱርክ በሰሜን ኢትዮጵያ የሚገኙ የአካባቢ የጐሳ መሪዎችን በጥቅማጥቅም እየደለለች በ1557 ምጽዋን ተቆጣጠረች። እንዲሁ ግብጽ የሱዳን ወደብ የነበረውን ዘይላን ያዘች። ከዛም እስከ ቀይ ባሕር ድረስ ለመስፋፋት ሞክራለች። በ19ኛው ከፍለ ዘመን ጣሊንና እንግሊዝም ቅኝ ግዛታቸውን ለማስፋፋት ከፍተኛ እንቅስቃሴ ስላደረጉ አገሪቱ በውጭና በእርስ በርስ ጦርነት ተወጠረች።

በዘመነ መሳፍንት የግዛት ዘመን የአገሪቱ ማዕከላዊ መንግሥት እየተዳከመ ሲመጣ የትግራይ ገዥ የነበሩ ራስ ሚካኤል ስሁል የተባሉ ኢዮአስ 1ኛን በ1769 ከሥልጣን አውርደው አስገደሏቸው። እንዲሁ አጼ ዮሃንስ 2ኛ አጼ ተክለሃይማኖት 2ኛን ሲሾሙ ለዘመነ መሳፍንት የመጀመሪያው ክስተት ሆነ።
የተካሄደው የእርስ በርስ የሥልጣን ሽኩቻ በተራዘመ ቁጥር ግብጽ አጋጣሚውን በመጠቀም 1874 ዓ.ም ሀረርን ተቆጣጥራ ነበር። በ1875 ዓ.ም በሰሜን በኩል ጣሊያኖች ከፍተኛ የመስፋፋት ወረራ አደረጉ። ይሁን እንጂ በአጼ ዮሃንስ አራተኛ የግዛት ዘመን ሥመ ጥሩው አሉላ አባ ነጋ ባደረጉት የተቀነባበረ ጦርነት በ1887 ዓ.ም ዶጋሌ ላይ ጣሊያን መሸነፏ አልቀረም። በተመሳሳይ ሁኔታ እንዲሁ ጉራአ አካባቢ ግብጽ የላከቸው ጦር በኢትዮጵያ አልበገር ባይነት ድባቅ ተመታች።

በኢትዮጵያ የተማከለ መንግሥት ለመመስረትም ሆነ የበላይነትን ለማሳየት ብዙ ጊዜ የእርስ በርስ ጦርነቶች መካሄዳቸውን ከፍ ሲል አውስተናል። ይህ ሁኔታ ባለበት አጼ ቴዎድሮስ 2ኛ በጐንደር በኩል ሥማቸውና ኃይላቸው ጐልቶ ወጣ። ነገር ግን በአገሪቱ የተማከለ መንግሥት ለመመስረት ከፍተኛ ተጋድሎ በሚያደርጉበት ወቅት የቤተክርስቲያን ሹማምትም ሆኑ አንዳንዶች ሥልጣናቸውን ላለማስነጠቅ ውስጥ ውስጡን በአጼ ቴዎድሮስ ላይ መዶለት ጀመሩ። ከዚህ አድማ ባልተናነሰ ሁኔታ የየጁ ኦሮሞ የሽዋ፤ የጐጃም መሳፍንቶች በጐንደር በኩል የሥልጣን ተፎካካሪ የሆኑ አጼ ቴድሮስን ለመውጋት ተነሱባቸው።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ከሕዝብ ጉያ ሳታወጣ- ሰለባህን አትቅጣ - አሳዬ ደርቤ

የሰሜኑ የትግሬው በዝብዝ ካሣ (አጼ ዮሃንስ 4ኛ) ሥጣል ከቴዎድሮስ እጅ ነጥቀው ብቸኛ ንጉሥ ለመሆን ከፍተኛ ፍላጎት ስለነበራቸው የመሣሪያ እርዳታ አገኛለሁ በሚል ከኢንግሊዝ ጋር ተስማሙ። ይሁን እንጅ አጼ ቴዎድሮስ የውጭ ባዕድ ወራሪ ኃይል አገሪቱን እንዳይደፍራት ኃይላቸውን በማጠናከር ብዙ ጊዜ ተዋግተዋል።

ነገር ግን አገር በቀል ባንዳዎች ለእንግዝሊዝ ጦር መረጃ እያቀበሉ የአጼ ቴዎድሮስ ኃይል እንዲሳሳ ማድረጋቸው አልቀረም። ለዚህ ማስረጃ አጼ ዮሃንስ አራተኛን ከእንግሊዝ ጋር ባደረጉት ውል የናፒየርን ጦር ወደ መቅደላ መምራታቸው ነው። በመጨረሻም አጼ ቴዎድሮስ የሚደርስባቸውን ተቃውሞ እየተጋፈጡ ከ1855 1868 በንግሥና ቆይተው መቅደላ ላይ ከኢንግሊዞች ጋር በተከፈተው ጦርነት ለጠላት እጅ መስጠትን እንደነውር ቆጥረው የራሳቸውን ሽጉጥ ጠጥተው ለአገራቸውና ለሕዝባቸው መስዋዕት መሆናቸውን ታሪክ መዝግቦታል።

ከአጼ ቴዎድሮስ በኋላ አጼ ዮሃንስ 4ኛ ኃይላቸው በማጠናከር ከተቀናቃኞቻቸው ጋር ከፍተኛ ውጊያ አድርገዋል። በእንግሊዝ መንግሥት ተባባሪነት የአጼ ዮሃንስ አራተኛ ኃይል ጐልቶ ሊወጣ ቻለ። ይሁን እንጂ የአካባቢ ገዥዎችን ከማስተባበር ባለፈ አገሪቱን በተማከለ መልክ ማስተዳደር አለመቻላቸውን ከታሪክ መረዳት አያዳግትም። በሰሜን ጀግናው አሉላ አባ ነጋ የጣሊያንን ወረራ እየተጋፈጡ ባለበት የአጼ ዮሃንስ ኃይል እምብዛም እንዳልታከለበት የብዙዎች ግምት ነው።

አጼ ዮሃንስ አገራቸውን ለባዕድ ወራሪ አሳልፈው ላለመስጠት መተማ ላይ ከድርቡሾች ጋር ሲዋጉ ሕይወታቸው ልፏል። አንገታቸው ተቆርጦ ካርቱም መሄዱ እውነት ነው። በዚህ ሁኔታ አጼ ዮሃንስ አራተኛ 1872–1889 ድረሰ ሥልጣን ላይ መቆየታቸው የማይታበል የታሪክ ሃቅ ነው።

አጼ ዮሃንስ አራተኛ ኢትዮጵያን በተማከለ መልክ ለማስተዳድር ጥረት በማድረጋቸው ለኢትዮጵያ ባለውለታ ናቸው። ነገር ግን በግዛት ዘመናቸው ሕዝብ አብሯቸው ተሰልፎ እያለ በእስልምና ተከታዮች ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ማሳደር ጀመሩ። አጼ ዮሃንስ አራተኛ የአስተዳደር ጉድለት ወይም ብቃት ስላልነበራቸው በእስልምና ተከታይ ሕዝብ በኩል ሊያገኙ ይችሉ የነበረው ድጋፍ አጡ። ጠቅለል ባለ መልኩ አጼ ዮሃንስ አራተኛ በታሪክ መልካም ሥም ቢኖራቸውም አጼ ቴውድሮስ በባዕድ ወራሪ እንዲጠቁ ማድረግ ባልተገባቸው ነበር። በዚህ የተነሳ ይመስላል ብዙ ጊዜ የአጼ ዮሃንስ መንግሥት በባዕዳን የተገነባ እንደነበር የተለያዩ የታሪክ ፀኃፊዎች ዘግበውታል።

በልማት በኩል ያደረጉት አስተዋጽዖ ጐልቶ አልታየም። የእስልምናን ሃይማኖት ጠቅለው ወደ ክርስትና ሃይማኖት ለማስፋፋት ከፍተኛ ሥራ ሰርተዋል። ቢሆንም ከጥቅሙ ጉዳቱ እያመዘነ የሃይማኖት ልዩነት በፈጠረው ክፍተት የሰው ሕይወትና ንብረት ከማለቁም ባሻገር የእስላምና የክርስቲያን አንድነት እንዳይጠነክር የአጼ ዮሃንስ አራተኛ አስተዳደር ምክንያት ሆኗል።

ባጠቃላይ በዛ ዓለም ባልሰለጠነት፤ አገሪቱ በእርስ በርስ የሥልጣን ሽኩቻ እየታመሰች ባለበት አገራቸውን ለድርቡሽ አሳልሆፎ ላለመስጠት ያደረጉት ጀግንነት ለመላ ኢትዮጵያ ዋስትና ነበር ማለት ይቻላል።

ከዝርዝር ጉዳዩ ከመግባቴ በፊት በመጀመሪያ ደረጃ መምህር ገብረ ኪዳን ደስታ ጊዜያቸውን ወስደው የአገር ታሪክ በመፃፋቸው ላንደቃቸው እወዳለሁ። ከዚህ በፊት የተፃፉም ሆነ ያልተፃፉ በታሪክነት እንዲቀመጡ ችሎታ ያላቸው የመፃፍ አገራዊ አደራ አለባቸው። እርግጥ ነው ሰው የማይገሰስ ሰብአዊ መብቱን በመጠቀም መፃፍና መናገር እንደሚችል አምናለሁ። ነገር ግን የአገርና የሕዝብ ታሪክ በዘፈቀደና ክልልን ያማከለ ከሆነ ለትውልዱም ሆነ ለአገር ከጥቅሙ ጉዳቱ ያመዝናል። ከመምህር ገብረ ኪዳን አንደበት ማድመጥ እንደተቻለው ችግራቸው ከአጼ ምኒሊክ ጋር የተያያዘ ነው። ይህን ካልኩ ዘንዳ ወደ መነሻየ ላምራ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  እኔ እማልሰጣችሁ ፣ እናንተ እማትወስዱት….

መምህር ገብረኪዳን ደስታ በቅርቡ ስለአጼ ዮሃንስ አራተኛ ገድል የሚያሳይ መጽሕፍ መፃፋቸው ይታወሳል። ይህን መነሻ በማድረግ የአሜሪካ ሬዲዮ አማርኛ ዝግጅት የትግራይ ቃላቀባይ አቶ ገብራይ ገብሩ የአጼ ዮሃንስን ገድል የሚያወሳ መጽሕፍ መፃፍ ለምን አስፈለገ የሚል ጥያቄ አቅርቦላቸው ማዳመጥ ችያለሁ።

የመምህር ገብረ ኪዳን ደስታ መልስ፟፦ሌሎች ስለአካባቢያቸው ሲጽፉ እኔም ስለአካባቢየ እጽፋለሁ፤ አጼ ዮሃንስ ለኢትዮጵያ ጥሩ ሰርተዋል፤ ነገር ግን እስከ ዛሬ ድረስ ታሪክ የተባለው ለአንድ ውስን ሰርዓ-ተማኅበር ብቻ በማጠንጠን አንድ አቅጣጫ ይዟል፤ ለማቃናት የሚተጋ ሰው አላጋጠመኝም፤ በአጼ ዮሃንስ ላይ የተሳሳተውን ዘገባ ለማስተካከል ነው አሉ። ጋዜጠኛው ገብራይ ገብሩ አክሎ ለዚህ ምን ማሰረጃ አለዎች የሚል ጥያቄ አቀረበላቸው።
የደራሲ ገብረ ኪዳን መልስ ፦ ስለመረጃ ከትግራይ ሕዝብ በላይ ምንጭ የሚሆነኝ ሌላ ሕዝብ የለም የሚል ነበር።

መምህር ገብረ ኪዳን ማብራሪያቸውን ሰፋ በማድረግ አጼ ምኒሊክ የሽዋ ሰው ብቻ ስለነበሩ ሰሜኑን ክፍል እንደ ኢትዮጵያ አይመለከቱትም፤ ለኮሎኒያሊዝም ምክንያት ናቸው ወዘተ በማለት ደጋግመው ነግረውናል።

አዎ አጼ ምኒሊክ የሸዋ ሰው መሆናቸው አይካድም፤ በዚህ ሁላችን ልዩነት ያለን አይመስለኝም፤ እሽ እንስማማ። ችግሩ ግን የሽዋ ሰው ብቻ ስለነበሩ ሰሜኑን ክፍል እንደ ኢትዮጵያ አይመለከቱትም የሚለውን አምኖ ለመቀበል ህሊናየ አልደፈረም። አባቶቻችና የታሪክ መዛግብት እንደሚያስረዱን ከሆነ አጼ ምኒሊክ የመላ ኢትዮጵያ አካል መሆናቸውን ነው ታሪክ የነገረን።

በዘመኑ መሳፍንታት ሲነሱ መጀመሪያ የአካባቢያቸውን ሕዝብ ይሁንታ ለማግኘት ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ነው። የአጼ ዮሃንስን፤ የአጼ ቴዎድሮስም የኃይል አደረጃጀት እንዲሁ በአካባቢ ላይ የተገነባ ነበር። የአጼ ምኒሊክም አደረጃጀት ከዚህ የተለይ አይደለም። በዚህ ዓይነት መነሻቸውን አውቀው እያሰፉ ሌላውን አካባቢ ማስተዳደር ችለዋል።

አጼ ምኒሊክ ከአጼ ዮሃንስ ለየት የሚያደርጋቸው ነገር ቢኖር አጼ ምኒሊክ አንድ ነገር ከማድረጋቸው በፍፊት አቅምና ችሎታቸውን የማመዛዝን ችሎታ ነበራቸው። በወቅቱ አጼ ዮሃንስ ከእንግሊዝ ባገኙት መሣሪያ የተጠናከሩ ስለነበር ለብቻ ከመዋጋት ይልቅ ኃይል ካለው ጋር በመሆኑ አገሪቱን ማስተዳደር ይቻላል በሚል አጼ ምኒሊክ ከትግሬ ከተወለዱት ከአጼ ዮሃንስ ጋር ወዳጅነት መፍጠር ብቻ ሳይሆ እስከ መጋባት ደርሰዋል። ታዲያ ከሸዋ እስከ ትግራይ ድርሰ ዘር ሳይለዩ በጋብቻ ከተሳሰሩ የሽዋ ብቻ ነበሩ ለማለት አያስደፍርም። ታሪኩ እንደታሪክ ይቀመጥ ከተባለ የጠባብነት ስሜት ያልነበራቸው ምኒሊክ ብቻ ነበሩ ማለት ይቻላል።
የኢትዮጵያን ሉዓዊነት ለማስከበር የተማከለ መንግሥት ለመፍጠር የተለያዩ አካባቢዎችን አንድ እያደረጉ እቅዳቸውን ወደ ተግባር ለመለወጥ እየተንቀሳቀሱ እያለ ከመሳፍንቶች የእርስ በርስ ጦርነት በከፋ መልኩ የጣሊያን መንግሥት ኢትዮጵያን ለመቀራመት ወረራ ጀመረ። ይሁን እንጅ በአጼ ምኒሊክ ድፍረትና በእትጌ ጣይቱ ብልህነት በ1896 የአድዋን ድል ተጐናጸፉ። ነገር ግን የአገሪቱ ማዕከላዊ መንግሥት በመላላቱ የተነሳ ቀረጥ ወይም ታክስ የሚከፍለው የሰው ቁጥር ቀነሰ። የገቢ ምንጭ በቀነሰበት ሁኔታ እስከ መጨረሻው ከጣሊያን ጋር ጦርነት ቢገጥሙ ውድቀት ሊደርስባቸው እንደሚችል በመገመት ለጊዜው ኤርትራን ከጣሊያን እጅ ማስወጣት አልቻሉም።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ኢትዮጵያ የዕንቆቅልሽ ምድር - ዳግማዊ ጉዱ ካሣ

ለዚህ ዋናው ምክንያት የኢኮኖሚ አቅም ማነስና በሰሜ ኢትዮጵያ አገር በቀሎች ከጠላት ጋር በመወገናቸው ወደ ፊት ቢገሰግሱ ድል ሳይሆን የያዙትን እንደሚያጡ ከግምት በመሳገባት ነው።
የዚህ አይነት የጦርነት እስትራቴጅ በዚህ በ21 ክፍለ ዘመንም ቢሆን አንድ መንግሥት ለውጊያ ሲነሳ መጀመሪያ የጦር ኃይሉን የኢኮኖሚ አቅሙ በማገናዘብ ነው ። ታዲያ የአጼ ምኒሊክ ጥፋት ተምኑ ላይ ነው ብሎ መጠየቅ ተገቢ ነው። ይሁን እንጅ አጼ ምኒሊክ ቀስ በቀስ የመሳፍንት ገዥዎችን ወደ አንድ በማምጣት ለማዋሀድና አገሪቱ ከውጭ ወራሪ ጦርነት ተላቃ የቴክኖሎጅ እድገት እንድታሳይ ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል። የተለያዩ የእምነት ተከታዮች የእርስ በርስ ውጊያን አስቀርተው ወደ አንድ እንዲመጡ አድርገዋል።

አጼ ምኒሊክ በ19ኛው ክፍለ ዘመን የዛሬው ምሁር ያላሳየውን የተራማጅነት ባሕሪ እንደነበራቸው አሳተው አልፈዋል። በአገሪቱ ሰላም የሰፈነ በአጼ ዮሃንስ ዘመን ሳይሆን በአጼ ምኒሊክ የግዛት ዘመን ስለመሆኑ ታሪክ ነጋሪ አያስፈልግም። ድሃው ሰርቶ የመኖር መብቱ ተከብሮ፤ ግብር እንኳን መክፈል ያልቻሉ እርዳታ እየተሰጣቸው በሰላም የኖሩበትን ዘመን ፈጠረዋል። የአግሪቱን የሥልጣኔ ጉዳና ለማፋጠን ገጠሬውን ከከቴሜው፤ የውጩን ከኢትዮጵያ ጋር ለማገናኘት የባቡር መስመር፤ የስልክ አገልግሎት እንዲስፋፋ የመጀመሪያ የእድገት በር ከፋች አጼ ምኒሊክ ናቸው።

በአጼ ዮሃንስ ዘመን ጣሊያን በቀይ ባሕር ሲስፋፋ ነበር። አጼ ምኒሊክ ግን የባድ ወራሪን መስፋፋት ዘመቻ ለመደምሰስ ባደረጉት ጦርነት አድዋ ላይ ድል መቀዳጀታቸው ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ የጥቁር ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ አጼ ምኒልክ ብቻ ናቸው። የአገሪቱን የእርስ በርስ ጦርነት አስወግደው አዲስ አበባን ቆርቁረው ዛሬ ለአፍሪካ አንድነት ጽሕፈት ቤት በር የከፈቱ ምኒሊክ ብቻ ናቸው።

ኢትዮጵያን በሕግ የሚተዳደር ሕዝብ ፈጥረዋል። ዓለም ባልሰለጠነበት በእርስ በርስ ጦርነት ወቅት አጼ ምኒሊክ ሥልጣ ከአንዱ ወሌላው በሰላም እንዲሸጋገር ለመጀመሪያ ጊዜ የዴምክራርሲን ይትባህል አሳይተው አልፈዋል።

ደራሲው ከአንደበታቸው ሲናገሩ እንደተደመጠው ከሆነ በጐጥ ዙሪያ የተሸበቡ መሆናቸውን አሳይቷል።
በጣም አዛዛኝ ሆኖ ያገኘሁት ደግሞ መላውን ኢትዮጵያ በማግለል ምስክሬና የታሪኩ ምንጭ የትግራይ ሕዝብ ብቻ ነው ማለታቸው የደራሲነታቸውን ማንነት በሚገባ አሳይቷል። ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የህወሐትን የድል ቀን ትግራይ ውስጥ ሲያከብሩ እንኳ ከወርቅ ሕዝብ ተወለድኩ ያሉትን ቃል ያጠናከረ መጽሕፍ መስሎ ታይቶኛል።

ኢትዮጵያ ከመሳፍንት እስከ አሁን ድረሰ ሕዝቦች ተዋደው ተፋቅረው ዘር ሳይለዩ ተጋብተው ተዋልደው አገራችን አቆይተው አስረክበውናል። በመሆኑም ይህ ትውልድም ሆነ ቀጣዩ ትውልድ አንድ በሆነች አገሩ እንዲኮራ ኢትዮጵያዊነትን የሚያጠነክር የታሪክ መጽሀፍ እንደሚፈልግ አያጠያይቅም።

በመጨረሻ፦መምህር ገብረኪዳን ደስታ በቃለመጥይቁ ላይ የተሳሳትኩት ካለ እታረማለሁ ማለታቸው ኢትዮጵያዊነትን ያሳያል። በመሆኑም መምህር ገብረኪዳን በታሪክነት ያቀረቡትን መጽሀፍ ለአገርና ለሕዝብ አፍራሽ መሆኑን ልብ እንዲሉት ተመልሰው እንዲያነቡትና የሚስተካከለውን በእርምት መልክ ቢያወጡት በሕዝብ ዘንድ ሊኖረዎት የሚገባው ተቀባይነት ቦታ ይኖረዋል። ነገር ግን ወግቶ ይማርህ ከሆነ በታሪክ ማስወቀሱ አይቀርም።

አንባቢያን በዚህ ዙሪያ የተሳሳትኩት ወይም የጐደለ ካለ ለመታረም ዝግጁ ነኝ።

ሁሉም ቀናውን እንዲያሰብ የእግዚአብርሄር ረዴት ይደርብን።

11 Comments

  1. I think the Oromo who took power at Gondar was Ras Ali , who took power after the end of the dynasty of Aste Tsersedingil the I: the grand father of Aste Fasil in which their dynasty ended after the reign of Aste Fasil – One of the main reason Aste Tewdros took up arm was due to the reign of the Yeju Oromo at Gondar. And Aste Tewodros defeated Ras Ali and become king of kings of Ethiopia. Gebrekidan is not a historian rather an empty head tigre that snores to much

    • G/Kidan is a hero! He to took the initiative to make the correction to hearsay story which is considered by few as Ethiopian history. Those who even not able to write one paragraph is rudely insulting G/kidan exposing their ignorance. keep up the good work G/Kidan. don’t give up. You are an example for others and more will travel your way in getting re-written the corrupted so called Ethiopian history!

  2. Tegrean elits ethnocenterisim is a curse in their blood. We can’t help it. Let us forget them and do what we got to do, save Ethiopia and win our diginity back…HUMANITY BEFORE ETHNICITY…..NO ONE IS FREE UNLESS WE ALL ARE FREE.

    Lets invest our time and energy on things we can change.
    Long live Ethiopia

  3. Taklo,

    Do you know the difference between an opinion and historical facts. Why do you try to twist facts to fill in your imaginary history? Are we not still out of this kind of jargon?

  4. Ato Teklu Teshomme

    Yet yeneberk gimatam neh … Afeh yegemal … Bante bet eko counter attack maregeh new … gin aladerekim … Tarikin achemalkeh akerebkew enji … Zim beye segemet malet new Amaran yematwekil werada neger neh … Tamagn beyene yeshalenal …. Minilik Was a Murderer he enslaved the oromo people by giving a name “Galla” … Minm enquan Amara behonim hakun menager gin wurdet adelem

    • @Mesfin: Denkem Amara:
      You like it be but you don’t get it man. be urself. Amara never open a mouth to insult others. Insulting is typical from weyane bandas.

  5. Ato Takelo, you condemn G/kidan for his focus on Atse Yohannes and his writing source of Iinformation. I’m agreed about the source of information he quoted. But what about your article? You did the same with what G/kidan is doing. That is you try to magnify your similar man Atse Menilik(I respect the emperor) by quoting intangible evidences. in the contrary you tries to the possible way to degrade and attack Atse Yohannes. The most terrible thing you mentioned is that what Atse Yohannes did on our Muslim Ethiopians, on the opposite you try Atse Menelik was doing good for Muslims. If you understand Atse Yohannes was not staying a long in power. Since, Yohannes was very religious and kind his palace was administered by Debtera Ekubit who was sent by Menilik to sabotage him and Alula. This Debtera was trying to murder Ras Alula by creating different kind of lies to Atse Yohannes. I think every body knows this story. It’s written by the known editor Mamo Wudneh on the history of Atse Yohannes. It was not the duty of Atse Yohannes to fight face to face with Derbush Mahdists in Metema. But before Yohannes goes to Metema, he asked his palace secretary Ekubit to tell him the outcome, going to the war front or remaining in his palace. Ekubit told him that if he goes to the war if died he will go to heaven, if not no heaven at all. Besides this, Atse Yohannes’s war lords and Mequanints were strongly opposed the journey of him to the war front. At last Atse Yohannes decided to go. The best tangible thing how Debtera Ekubit exposed was one day a letter was sent to Atse Yohannes by Ras Gobena in initiating to work with him and quitting Menelik . But Ekubit return the letter to Menelik to jail Ras Gobena with out the knowledge of Yohannes. What I want to say is I don’t want to say what the Amara rulers did on Muslims because that is not a big issue in the Zemene Mesafnt. What we need is we have to write a balance story of our past history. There are good and bad things that our Emperors doing. They already passed by doing what they can do to their country. Their past history should be a great lesson to us. I’m very interested with the interview of Dr. Shumet Sisay. That is a balanced story.If we are writing our past history we shouldn’t sided with our clan or tribe. That is not a story but politics. God bless Ethiopia.

  6. Let us look from insight starting from the very beginning since seaul Michael
    Tiginsts are always against ethiopiawenet. Particularly tigrian(agames) elite
    has determined to be ati-ethiopia, anti-unity their blood are already contaminated by
    hate crime. they have been in the state of inferiority complex .they never get out of this there is no treatment. There is nothing b/n Tigre(agame) and great ethiopiawinet.

    • You idiot, do you know the history of the proud Agame people? Before you write you have to have a knowledge of that topic. I’m sure you are poor about the story of the Agame people. Simply insulting with out any knowledge of an innocent society is a crime. The capital of Agame Auraja is called Adigrat. Agame is the place where ancient Mequanints and respected war lords was fborn. Ras Sebagadis the known war lord is from this place. If you want to know more read the story of Ras Sebagadis in Ethiopian History. He was a very educated Ethiopian who was ruled until the Red Sea. He had a good knowledge about the importance of the Red Sea to Ethiopia. Since, Agames are the true Ethiopians, they refused Weyane to carry his bandit flag and told him the green, yellow, and red color flag is their ancestor’s flag they use it for ever. Then, to revenge, Weyane gives a new name called Misraqawi Zone by mixing it with Bizet and Wuqro. Now, Agame is dissolved but the people have an association of Agame like Edir or Equb. Agazi-Alumni is also part of it.

  7. The Shiftian Aba Bzbaza Kassa was’nt good for one unity Ethiopia but an ego one.

Comments are closed.

Share