አንድነት ፓርቲ ለመድረክ ምላሽ ሰጠ፤ የተደበቀውን አፍረጠረጠው

ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) የተሰጠ መግለጫ

በመሠረቱ ፓርቲያችን አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) መድረክ እንዲመሠረትና አሁን ያለበት ደረጃ እንዲደርስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደረገ ድርጅት ነው፡፡ ለመድረክ መፈጠርና መጎልበት በአደረገው ጉልህ ተሳትፎ ከፍተኛ ዋጋ የከፈለበት መሆኑን መድረክም ሆነ የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚያውቀው ጉዳይ ነው፡፡

የግምገማው ግኝቶች በየትኛውም ገጽና ቦታ የመድረክ ፕሮግራም፣ መተዳደሪያ ደንብና የስምምነት ሰነድ በመድረክ አባል ድርጅቶች በጋራና በሙሉ ስምምነት መጽደቃቸውን አላስተባበለም፡፡ አልካደምም፡፡ በተጨማሪም መድረክ እንደ አንድ የፖለቲካ ኃይል በኢትዮጵያ ሕዝብ ህሊና ውስጥ ከፍተኛ ተስፋን የፈጠረ ብቻ ሳይሆን አዲስ የጉዞና የአሠራር አቅጣጫን የቀየሰ መሆኑን ጭምር አንድነት ያውቀዋል፡፡ ያምንበታልም፡፡

መድረክ ከመቀናጀት ወደ ግንባር የተሸጋገረበት ሂደትም ብዙ ችግሮችና ድክመቶች ቢኖሩትም በአባል ድርጅቶች ሙሉ ስምምነትና ፍቃደኘነት መሆኑን አንድነት አምኖ የሚቀበለው እውነታ ነው፡፡ በመሆኑም የመድረክ ድክመቶች፣ ስህተቶችና ችግሮች በሙሉ አንድነት ፓርቲም አብሮ የሚጋራውና የሚጠየቅበት ነው፡፡ የግምገማው ዓላማ ችግሮችንና ድክመቶችን ወደ ሌሎች የመግፋት (blame-shifting) አባዜ አለመሆኑን አበክረንና አጠንክረን እንዲታወቅልን እንፈልጋለን፡፡

በአባል ድርጅቶች መካከል ስምምነት ያልተደረሱባቸው የፕሮግራምም ሆነ የህገ-ደንብ ጉዳዩችም በቀጣይ ውይይቶች ለማቀራረብ እንደሚሞከርና ይህ ካልተሳካም መድረክ የመንግሥት ሥልጣን ሲይዝ በሕዝብ ውሳኔ መፍትሔ እንዲያገኙ እንደሚደረግም ሙሉ ስምምነት ያገኘ ጉዳይ መሆኑ እውነት ነው፡፡

የመድረክ መግለጫ፣ ችግርች የሚጀምረው በመጀመሪያ ያልተካሄዱ ጉዳዩችን እንደተካሄዱ አርጎ ከማቅረቡ ላይ ነው፡፡ ሁለተኛውና መሠረታዊው ችግር ደግሞ ድርጅቶች በአንድ ወቅትና ሁኔታ ተስማምምተውና ወደው የተቀበሉት ፕሮግራምና መተዳደሪያ ደንብ ላይ ግምገማ ማካሄድ የለባቸውም የሚለው ነው፡፡ በሌላ በኩልም በአንድ ወቅትና ሁኔታ የተወሰኑ ሰነዶችን ፓርቲዎች በስምምነት ስለተቀበሉት ብቻ ሰነዶችን ትክክል ያደርጋቸዋል የሚለው ግንዛቤ ነው፡፡ ባጠቃላይ ሕይወትና በውስጡ ያሉ ክስተቶች በሙሉ የማያቋርጥ የለውጥ ሂደትና እንቅስቃሴ አካል ናቸው፡፡ በመሆኑም በማንኛውም ሥነ አመክኖ (Logic) ሰነዶች ከወቅት፣ ከጊዜና ከሁኔታዎች አኳያ (አንፃር) ይፈተሻሉ፣ ይገመገማሉ ይሻሻላሉ፣ ይለወጣሉም፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ቁጥር 52 - PDF

በመግቢያው ላይ እንደተቀመጠው የግምገማው ዓላማ የመድረክ ድክመቶች የሚስተካከሉበትና ጥንካሬዎቹ የሚጎለብቱበት ሁኔታ እንዲፈጠርና ብሎም ትግሉ የሚፈልገውን ሁለንተናዊ አቅም ለመፍጠር እንዲቻል ነው፡፡ በዚህ ረገድ የአንድነት ፓርቲ ምን ዓይነት ሚና መጫወት ይገባዋል የሚለውን ጭምር ለመፈተሽ ነው፡፡ በግምገማው ሂደትም የታዩት ነገሮች የሚከተሉት ናቸው፡፡

ሀ) ለአለፉት በርካታ ዓመታት በተቃዋሚ ጎራ አብሮ ላለመስራት ፈታኝ ሆኖ የቆየውን የኢትዮጵያ ብሔርተኘነትና ብሔር ላይ በተመሰረቱ ፓርቲዎች መካከል የነበረውን ክፍተት በተወሰነ መልኩ ማጥበቡ በአዎንታነት የሚታይ ቢሆንም፤ መድረክ ከተመሠረተ አራት ዓመት ቢያልፈውም በፕሮግራም ልዩነቶች ላይ አንድም ቀን ውይይት አለማካሄዱና ደንበቦችንም ቢሆን አብረን የቆየንባቸውን ጊዜያት ያገናዘበና ትግሉ የሚጠይቀው ደረጃ የሚመጥን ለውጥ አለማድረጉን ነው፡፡ ይህም አንዱ ዋና ምክንያት በመሆኑ መድረክ ከተመሠረተ ጀምሮ ፓርቲዎቹ የመድረክ አባል ለመሆን ያለመቻላቸው ነው፡፡

ለ) የመድረክን ሕገ-ደንብ በኢ-ዴሞክራሲያዊነት ለማስቀመጥ አስገዳጅ የሆነው አንዱ ምክንያት ፓርቲዎች የመተማመንና የአብሮ የመስራትን መንፈስ መፍጠራቸውና ከ4 ዓመት በኋላም በሙሉ ድምጽ ስምምነት ማለፍ ያለባቸው ጉዳዮች መኖራቸው ጭምር ነው፡፡ የቪቶ ሥልጣን የተሰጠውም የፓርቲዎችን ፍላጎትና ስጋቶች ለማስተናገድ ነው የሚለውም በግምገማው ተገቢ ሆኖ ባለመገኘቱ ነው፡፡ ትልቅ ቦታም ሊሰጠው ይገባ የነበረው ለሕዝብና ለአገር ፍላጎትና ስጋቶች ስለ ነበር ነው፡፡

ሐ) በግንባሩ መተዳደሪያ ደንብ መሠረት እያንዳንዱ የመድረክ አባል ፓርቲዎችና አመራሮች በአባል ድርጅቶች ላይ አፍራሽ አስተያየት ከመስጠት መቆጠብ አለባቸው የሚል ሆኖ ሳለ በተለያዩ ጊዜያት በተደጋጋሚ በአንድነት ፓርቲና በአመራሮቹ ላይ የተሰነዘሩ አፍራሽና ጎጂ አስተያየቶችን በግልጽ በማስቀመጥ ፓርቲዎችና አመራሮች ወደ ትክክለኛው አቅጣጫና መስመር ይመለሱ ዘንድ አባሎችና ሕዝቡም የራሱን ገንቢ አስተዋጽአ እንዲያደርግ ነው፡፡ ከሁሉም በጣም ቅር የሚያሰኘው የመድረክ መግለጫ አፍራሽ አስተያየቶችን ሃሳብን በነፃነት ከመግለጽ መብት ጋር ማያያዙ ነው፡፡ በምን መመዘኛ ነው፡-

ተጨማሪ ያንብቡ:  ይነበብ «ወላሂ ሁለተኛ አማራ አልሆንም» የ 6 ዓመቷ ህፃን ከወለጋ

‹‹አንድነት ዶ/ር ነጋሶን ሊቀመንበር አድርጎ ቢመርጥም የአማራ ፓርቲ ወይም የአዲስ አበባ ልሂቃን ፓርቲ መሆኑን መካድ አያስፈልግም››
‹‹የአንድነት አዝማሚያ በደቡቦች፣ በአረና እንዲሁም በኦሮሞ ላይ የበላይነትን ለማሳየት ነው››
‹‹ አንድነቶች ፌዴራሊዝምን አይወዱም ፌዴራሊዝሙን የሚጠሉት አማራሮች ናቸው››
‹‹ ከዶ/ር ነጋሶ ውጭ መሪዎቹ አማሮች ናቸው፡፡ ይህን የምለው ስለማውቀው ነው››
‹‹ ህብረ ብሔራዊ ፓርቲ ሲዳማ ወለጋ ወ.ዘ.ተ ሄዶ ድምጽ ማግኘት አይችልም››
‹‹ ኦሮሞ አማራ ክልል ሄዶ ምረጡኝ ቢል ድምጽ አያገኝም፡፡ ኦሮሞ ከሆነ
ለምን ኦሮሞ ፓርቲ አይገባም አማራው ኦሮሞ አገር ሄዶ አይመረጥም››

ይህን የተናገሩት አቶ ቡልቻ ደመቅሳ ናቸው፡፡ በሌላ በኩልም ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ በተደጋጋሚ፡-

1. የተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉን መመረጥ የሚያውቀው ኢህአዴግ ነው፡፡ የእሳቸው መመረጥ የኢህአዴግ አሻጥር ነው፡፡

2. ስንትና ስንት የዴሞክራሲ አርበኞች ባሉበትና ደጋግመው በምርጫ ያሸነፉ ሰዎች እያሉ አንድ ተወዳዳሪ ብቻ አሸንፋል መባሉ አሳፋሪ ነው ብለዋል፡፡

የደቡብ ህብረት ፓርቲ በአቀረበው የክስ ማመልከቻ፡-

አንድነቶች ‹‹በአቋራጭ ሥልጣን የሚልፈጉ የነፍጠኛ አቋም ያላቸው ናቸው›› እነዚህ አነጋገሮች አፍራሽና አጥፊ ፕሮፓጋንዳ አካል ናቸው፡፡ ከላይ በአንድነት ፓርቲ ላይ ከተሰጡ አስተያየቶች መካከል የተወሰኑቱ ‹‹ጠባብ ብሔርተኝነት›› ባህሪያት የማያመላክቱ ከሆነ ምንን ነው የሚያመላክቱት? ሌሎችንም ምሳሌዎችንና ድርጊቶችንም መጨመር ይቻል ነበር፡፡ ሁኔታው በአጭሩ ለመተው ሲባል እንጂ፡፡
መ) ግምገማው የአንድነትን ብሔራዊ ምክር ቤትን፣ የሥራ አስፈፃሚውንና በመድረክ የአንድነት ተወካዮች ሚና በትኩረት የተመለከተውና የሰሉ ሂሶችን እንደየ ተጠያቂነታቸው ደረጃ የአሳረፈባቸው እንጂ እንዲያው ችግሮችን ወደ መድረክና አባል ፓርቲዎች የወረወረ አይደለም ወደ ውጭ እንዳየ ሁሉ ወደ ውሰጥም አይቷል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  "በሰላማዊ ትግል ተስፋ የቆረጡ ዲያስፖራዎች በእኛ ላይ ፕሮፓጋንዳ እያደረጉ ነው" - ዶ/ር ነጋሶ ለራድዮ ፋና

ሠ) በመጨረሻም ግምገማው የመፍትሔ አሳቦችን በአጭር ጊዜና በረጅም ጊዜ በመከፋፈል ጠቃሚ አስተያየቶችን ሰጥቷል፡፡ በተለይም ተቀዋሚ ፓርቲዎች አሁን የሚንቀሳቀሱበት የፖለቲካ ምህዳር እጅግ ፈታኝ የሆነበት ወቅት በመሆኑ የመድብለ ፓርቲ ዴሞክራሲ በአገራችን ጠንካራ መሠረት እንዲይዝ የተቃዋሚ ኃይሎች የመጠላለፍ፣ የመጠፋፋት ፖለቲካ የትም እንደማያደርስ በመገንዘብ በመተጋገዝ በአብሮ መስራት መንፈስ አብሮ መቆም እንዳለባቸው ነው፡፡ የሚያሳየው ከአብሮ መሥራት ውጭ በአገራችን ውስጥ ለውጥ ሊመጣበት የሚችልበት እድል ዝግ እንደሆነ ነው ያመላከተው፣ ያሳየው፡፡ ማንኛውም ፓርቲ የቱንም ያህል ትልቅነኝ ቢልም፣ ትልቅ ቢሆንም ዛሬ ኢትዮጵያ ያለችበትን ውስብስብና ዘርፈ ብዙ ችግሮችን ብቻውን ሊወጣው እንደማይችል ነው የታመነበት፡፡

እውነታውና የግምገማው ዓላማና ግኝቶች ይህ ሆኖ ባለበት ሁኔታ አንድነትን በመድረክ አፍራሽነት ለመፈረጅ መሞከር ‹‹ላም ባልዋለበት ኩበት ለቀማ›› ያስመስለዋል፡፡ ይልቁንም አንድነት ለግምገማውም ሆነ በተግባር ያረጋገጠው ለመድረክ ጥንካሬ ብርታትና ወደ ፊት መራመድ እንደ ከዚህ በፊቱ ሁሉ አሁንም በትጋት እንደሚሰራ በድጋሚ ያረጋግጣል፡፡ ግምገማዎችን ማካሄድና ውስጣዊ ድክመቶች አንጥሮ በማውጣት ከዚያም ትምህርት አግኝቶና እርምት አድርጎ መራመድ ‹‹ኢህአዴግን ነው የሚጠቅመው፤ ሕዝብን ያሳዝናል›› በሚል መርህ በሽፍንፍን መጓዝ ከአገኘነው ተሞክሮ አፃር ሲታይ ከጥቅሙ ጉዳቱ ያመዝናል፡፡

በመጨረሻም ለመድረክ የምናሳስበው ቁም ነገር የተፈፀሙን የአካሄድ ስህተት ምክንያት በማድረግ የግምገማውን ይዘት አልቀበልም ማለቱ ማንንም እንደማይጠቅም በድጋሚ ተመልክቶ በይዘቱ ላይ ውይይት እንዲከፈት እንዲያደርግ በአጽኖት እንጠይቃለን፡፡ ይህ እስከሆነ ድረስ የአብሮ መስራቱና መተባበሩ ተግባር አሁንም ይቀጥላል፡፡

ሰኔ 5 ቀን 2ዐዐ5 ዓም

አዲስ አበባ

11 Comments

  1. MEDREK can now move forward with the remainder of the organizations and start consolidation of its objectives. They spent a lot of time to convince the proponents of the former feudal system that a new day is on the horizon. It was not meant to be, oil and water cannot mix. You cannot form a progressive movement with reactionary forces. You have a just cause and a very strong base to form a new Ethiopia. There should be no hesitation. There is too much waffling around. Organize your youth just like they did with Semayawi. Semayawi are off shoots of Mesfin W/Mariams Andinet wing. What we hearing is a determination to move forward. Go MEDREK!!!!

    • obo kejela,
      yehonk duldum asama nehe-Turura galla-eyandandish dedeb galla endegena mefeter alebachu sew lemehon

      • @ Sayint
        You are woyane, we all know that no one from Ethiopia gives such stupid comment in 2013, your days are short like your “visionary leader”

  2. Medrek has racist peoples who believe in only race like Bulcha demeksaksa, merara gudina and others are racist old peoples, I don’t think they will be successful unless they are believing in being Ethiopian.

    • @Babu

      Do U know what racist means? nationalist means? Can you prove by logic and evidence that the people whose names you mentioned are racists? Being Ethiopian is also racism. Why not U say Oromian?Ogadenian? Ethiopian means Amhara. Do not use “Ethiopia” as a trade mark to deceive non-Amharas.

  3. obbo/aadde sayint:

    What you have written above is only insult. It shows how much you are discouraged,depressed, disappointed, ….It benefits neither you nor others. Go and take mental treatment at Emanuel Hospital.

  4. Andnet be tariku party hono ke gileseb gar (ke Negaso ena Siye) yetewahade party new. Minalbat Negason ena Siyen endetilik ye poletika figure wesdo yetegabaw begizew le seraw sihitet medebekya ( mesrach abalatun bemabarer) endihonew new male t yichalal. Komiku sitet yane tejemere. Be etnicity yemiyamnu ene Negaso ena be unity yemiyamnut Andinetoch bemin yegara program tesmamu?(Andinetn be mafres kalhone?) Siketil zeregna ko’bun (ene Siyen) aytew ene Beyene ene Merara ene Gebru ke Andinet gar medrek nen alu. Wuha ke zeit tekelakel endemalet. Ena eskezare min seru minis feteru? Minim. Negasom ende presidentnetachew zemen kuch blew , Seyem ,scholarachewn shifan adrigew, ende woyanenetachew zemen ye woyane yesiltan atir sir eyeshenanu (marking the boundry) sinoru Seye zemedocahewn le digami esir, Negaso baytewar honew tarik degemu. Ahun andinet mewcha feligual. Silezih be 3 wer enwahad! Min ena min yiwahad ? Ye andnet amerar ende shererit dir bet eyakosheshe yinur? Woys Yitereg? Mengè bimelsut yishalal! Negeru ye hager ena ye sew hiwot baynorbet ende kartoon film moto menesat binorbet mecherehsawn mayet neber?

  5. Go semayawi…Go andente. It is waste of time to work with people who think of only their ethnicity.
    Go Yelekal..Go Girma seyifu..Go Obang Metho..HUMANITY BEFORE ETHNICITY…NO ONE IS FREE UNLESS WE ALL ARE FREE.
    We want people who are ready to solve Africa’s problem not their ethnic mender problem. Little is alwayes little(tenesh hulem tinesh new)

  6. dear editor,
    when you post comments please read carefully because it is woyane who deliberately circulate such unacceptable insults which is immoral to ethiopians. it is just to divide ethiopians across ethnic lines specially the majority ones. please read thoroughly and remove the coment written by the so called ‘Sayint”. such substandard comments may affect the Habeshas which are respected so far. After all Habesha is not to be the level for Insults but to share ideas useful to build a common understanding. freedom to express opinion does not mean being vulgar. please i request you to remove it. It hurts us.

  7. Short message for andnets …. Instead of struggling eprdf u guys are killing ur time by talking the so called medrek the collection of old gard opposition groups …. Just isolate from them then try ur best . Thatis it

  8. mederek yedekem buden new, mederek ale kemibal alemenoru yimeretal. yene seye nefesegedayu buden. delalaw beyene ena aradaw merera yeweyane telalakiwoch nachew.yeLedetu kihedetu Guwadegnoch.

Comments are closed.

Share