ጋዜጠኛ አለምነህ ዋሴ የቁንጅና ፈቃድ ቢሮ ሃላፊ

ፋሲል አ.

የአለምነህ ዋሴን አስተያየት ለማድመጥ እዚህ ይጫኑ

ቤቴልሄም አበራ(ቤቲ)

ሰሞኑን ቤቴልሄም አበራ(ቤቲ) የተባለች ወጣት ኢትዮጵያዊት በቢግ ብራዘር አፍሪካ  ትእይንት (show) ላይ ከሴራሊዮኑ ቦልት ጋር ፈጸመችው ስለተባለው ወሲብ በተለየዩ  ማህበራዊ ድረ-ገጾች እና መገናኛ ብዙሃን የሚሰጠው አስተያየት እንደቀጠለ ነው::በዚህ የቢግ ብራዘር ትእይንት ላይ ከዚህ በፊት በተደረጉ ውድድሮች ላይ የተለያዩ ጥንዶች እንደዚህ አይነት የወሲብ ድርጊት መፈጸማቸው የተዘገበ ሲሆን ይህ የቢግ ብራዘር ትእይንት በባህሪው ለእንደዚህ አይነት ድርጊቶች የተጋለጠ ለመሆኑ ከዚህ ቀደምም ሆነ አሁን የተደረጉት ድርጊቶች በቂ ማሳያ ናቸው :: ይህ እንዳለን ሆኖ  ቤቲ ፈጸመችው ለተባለው ድርጊት ብዙ ኢትዮጵያኖች በተለያዩ  ድረ ገጾች ”አዋረደችን” አሰደበችን” ምነው ባትሄድ ቢቀርባት ኖሮ “እና የመሳሰሉትን የተቃውሞ  አስተያየቶች እየሰጡ ሲሆን ከነዚህም አስተያየቶች አንዱ ታዋቂው ጋዜጠኛ አለምነህ ዋሴ በሬድዮ የሰጠውን አስተያየትም ተከታትዬው ነበር::

ጋዜጠኛ አለምነህ ዋሴ እንደጋዜጠኛ ሳይሆን እንደ ተጋባዥ እንግዳ ከሌላ ጋዜጠኛ የሚቀርብለትን ጥያቄዎች እየመለሰ በቀረበው በዚህ ፕሮግራም ላይ አለምነህ አስተያየቱን ሲጀምር በዚህ ቢግ ብራዘር አፍሪካ ትእይንት ላይ ከሌሎች የአፍሪካ  ሃገሮች የሚመጡት ተወዳዳሪዎች በሃገራቸው ታዋቂነት ያላቸው የቲቪ ሾው አዘጋጆች፣ አርቲስቶች ወይንም በሞያቸው ዝናን ያተረፉ ታዋቂ ሰዎች (celebrities)  ሲሆኑ ከእኛ ግን የሚወስዱት እኔ የማላውቃቸው ሰዎች ናቸው ( ለማለት የፈለገው በሞያቸው በህዝብ ዘንድ ታዋቂ ያልሆኑትን ለማለት ነው) ሲል የቢግ ብራዘርን አዘጋጆችን ይወቅሳል::

እንግዲህ እኔን እንደገባኝ ከቤቲ ይልቅ የሃገራችን ታዋቂ አርቲስቶች (celebrities )  ቢሄዱ ኖሮ  ይሻል ነበር ምናልባትም አንዋረድም ነበር ብንዋረድም ውርደቱ የጋራ  ይሆን ነበር ሲል ይገልጻል::ይገርማል በመጀመሪያ  ደረጃ የቢግ ብራዘር አዘጋጆች ከአንድ ሃገር ታዋቂ አርቲስትም ይምረጡ መደበኛ ኖርማል ሰው ያ የተመረጠው ግለሰብ ወደ ውድድሩ ከመግባቱ በፊት የውድድሩን ህግጋቶች ከማጥናቱም በተጨማሪ በግሉ ደግሞ እንዴት ማሸነፍ እንዳለበት የአቅሙን ዝግጅት አድርጎ የሚገባ ሲሆን በተጨማሪም ወደ ውድድሩ ከገባም በኋላ በውድድሩ ውስጥ በሚፈጠሩ የተለያዩ አጋጣሚዎች እራሱን እያስተካከለና እያዋሃደ የሚሄድበት ሲሆን የሸመደደውን ወይም ያጠናውን የሚያንበለብልበት መድረክ ሳይሆን ከሁኔታዎች ጋር የራሱን የግል ስብእና፣ ስሜትና አስተሳሰብ የሚያንጸባርቅበት ትእይንት በመሆኑ ተወዳዳሪው አርቲስት ይሁን ወታደር፣ ፖለቲከኛ ይሁን መምህር፣ ድንገት በሚፈጠሩ አጋጣሚዎች የሚመልሰው ( የሚወስነው) ግብረ መልስ (reaction )  እንደየሰው የውስጥ ስብእና፣ ልምድ፣ አስተሳሰብና  ውስጣዊ ጥንካሬ የሚለያይ እንጂ አርቲስት ስለሆነ ትክክለኛ ውሳኔዎችን ያስተላልፋል ሌላው ሰው ግን ሊከብደው ይችላል ብሎ ሙሉ በሙሉ  መደምደም ይከብዳል::

ተጨማሪ ያንብቡ:  በጣም መነበብ ያለበት እውነት ነው! (ዶክተር ግርማ ዳዲ ጋዲሳ)

ሌላው አለምነህ ከዚሁ ጋር አያይዞ  የገለጸው ነገር የምናከብራቸው አርቲስቶች ወደ ውድድሩ ቢሄዱ ያስደስቱናል! ያኮሩናል! የሚፈጽሙትም ነውር ነገር ካለ አብረን ችግሩን እንቀበላለን ሲል ይገልጻል:: ወይ አለምነህ ታዲያ ቤቲስ ይህንን ድርጊት ባትፈጽምና ብታሸንፍ ኖሮ  ታስደስተን! ታኮራን! የለም እንዴ? እንዲሁም ያው ልክ አንተ እንዳልከው ነውር ነገር ካለም ያው ችግሩ የጋራ ይሆናል ማለት ነው ስለዚህ አብረን መቀበል የለብንም እንዴ ? ነው ወይስ ቢያኮሩንም ቢያሳፍሩንም አርቲስቶች ብቻ ናቸው መሄድ ያለባቸው እያልከን ነው?

ቀደም ሲል አርቲስት ወደ ውድድሩ ተልኮ  ቢሆን ኖሮና  ነውርም ካለ አብረን እንቀበለዋለን ሲል የነበረው አለምነህ ቤቲ መምህርት ናት በመሆኑም ትልቁ የሚሰቀጥጠው ነገር ልጆቻችንን ወዴት ነው የምንልከው? ሲል የተምታታ  ስጋቱን ይገልጻል:: እንዴ ደግሞ ነውር የአርቲስትና የመምህር የሚባል ልዩነት አለው እንዴ ጋዜጠኛ አለምነህ? ልጆቻችን ትምህርት እና ስነ ምግባር የሚማሩት ት/ቤት ብቻ ነው እንዴ? በዲቪዲው በሲዲው የአርቲስቶቻችን ስራ በየቤታችን እየገባ አይደለም እንዴ? አርቲስትስ አንድን ጤናማ  ማህበረሰብ ለመቅረጽ ከፍተኛ ሚና  እንዳለው አልሰማህ ይሆን?

የጋዜጠኛውና የአለምነህ ውይይት ሲቀጥል ጠያቂው ጋዜጠኛው ጥያቄ  መሰል አስተያየቱን በማስከተል ቤቲ ይህን ውድድር ካሸነፈች ወደ ሆሊውድ መሄድና የራሷን የጉዞና አስጎብኝ ድርጅት መክፈት እንደምትፈልግ ገልጻለች  በማለት ካብራራ በኋላ ቤቲ ወደ ሆሊውድ ከሄደችማ  ሌላ ነገር ነው ማለት ነው ሲል ቤቲ ወደ ሆሊውድ ሄዳ ሌላ ተመሳሳይ የሆነ ነገር መፈጸሟ አይቀርም የሚል ቃና ያለው አስተያየት ሲሰጥ ሁሉ ይደመጣል:: በእውነት በጣም የሚያሳዝን አስተያየት ነው:: በአንድ ውድድር ላይ በመዘናጋት መጠኑን የዘለለ ድርጊት የፈጸመች መምህርት እህታችን ( ለኔ ወሲብ መፈጸሟ ሙሉ በሙሉ እንደ ወንጀኛ  የሚያስቆጥራት ሳይሆን በመዘናጋት ትንሽ መጠኑን ያለፈና ባታደርገው ሁላችንም የምንመርጠው ድርጊት ነው) ምንም ማረጋጫ ሳይኖር ወደፊት በማንኛውም ጊዜና  የትም ቦታ  ይህንኑ የምታደርግ ተደርጎ  በሚድያ ከአንድ ጋዜጠኛ አስተያየት መስማት  እጅግ ያማል::

ተጨማሪ ያንብቡ:  እንኳን ለአዲሱ ዓመት አደረሰህ! - ከፕ/ር መስፍን ወልደ-ማርያም

አለምነህ አስተያየቱን በመቀጠል ቤቲ ይህንን ድርጊት የፈጸመችበት የተለያዩ  በጣም ብዙ አሳሳችና አዘናጊ ምክንያቶች ሊኖሩ ስለሚችሉ ብዙም ሊፈረድባት እንደማይገባ ይገልጽና  መልሶ  ደግሞ  ቤቲ ለፍቅር ብላ ቢሆን እንደዚህ ያደረገችው እኔ አንገቴን ለቢላ  እሰጥላት ነበር ግን አይደለም ለገንዘብ ብላ ነው ይህን ሁሉ ያደረገችው ብሎ በአንድ ጊዜ ሁለት የሚጋጩና  ባልተረጋገጠ መላምት ላይ የተመሰረቱ አስተያየቶችን ያስደምጠናል::

አለምነህ በማጠቃለያው ቤቲ ውድድሩን አቋርጣ እንድትመለስም ይመክራል:: ይገርማል የውድድሩን ህግና  ስርአት ያላፋለሰች እና ምናልባትም ጠንክራ በውድድሩ ውስጥ ከቆየች የማሸነፍ ተስፋ ሊኖራት የሚችልን ተወዳዳሪ እኔ ማየት የማልፈልገውን ነገር በማድረጓ  ከውድድሩ መውጣት አለባት ብሎ  መፍረድ ምን አይነት ፍርድ እንደሆነ  ለአድማጭ እተወዋለሁ:: ሲሆን ሲሆን ስህተቶቿን እያስተካከለች ለማሸነፍ እንድትጣጣር መገፋፋት ይገባል እንጂ ወደ ኋላ  እንድታፈገፍግና  እንድትሸማቀቅ ማድረግ ተገቢ አይመስለኝም:: የሄደችውስ ከተሳካ አሸንፋ ለመመለስ እንጂ በትንሽ መዘናጋት በተፈጠረ ጉዳይ ተስፋ ቆርጣ ለመመለስ ነው እንዴ? አለምነህ ንግግሩን ሲያሳርግ ደግሞ ኢትዮጵያውያን ቆንጆዎች ናቸው ሲባል እንደ ቤቲ ማለት አይደለም ሲል የቤቲን ቁንጅና ከኢትዮጵያውያን ቁንጅና ለመለያየትም ጥረት ሲያደርግ ይታያል:: ያንተ ያለህ ጆሮ  መቼም አይሰማው የለም:: አይ አለምነህ የኢትዮጵያውያን ቁንጅና እንደ ቤቲ ካልሆነ ታድያ እንደማን ነው? እንዳንተ ይሆን? ለመሆኑ አንተ ያልጣመህን ወይንም ያልተመቸህን ነገር ያደረገ ሁሉ ኢትዮጵያዊ ቁንጅናው ይገፈፋል ማለት ነው? ለካስ ከጋዜጠኝነትህም በተጨማሪ ቁንጅና ሰጭና  ነሺም ሆነሃል? ቤቲማ ልቅም ያለች ኢትዮጵያዊት ቆንጆ  ናት በተለያዩ  ምክንያቶች በመዘናጋት በአንድ ውድድር ላይ ትንሽ መጠኑን ያለፈ ድርጊት የፈጸመ ግለሰብ ቁንጅናው ይነጠቃል የሚል ህግ ካለ እራሱ አልምነህ ያስረዳን::

ተጨማሪ ያንብቡ:  ላም ባልዋለበት ኩበት ለቀማ :: ህወሃት ጎጠኝነትን ብትኮንን የመለስ ዜናዊ አጽም ይወቅሳታል።

ጋዜጠኛ አለምነህ ለመሆኑ ኢትዮጵያ የተዋረደችው በቤቲ የአጋጣሚ መጠኑ ያለፈ ድርጊት ነው እንዴ? ፍጹም በሆነ የአስተዳደር ብልሹነት፣ ፍትሃዊ ባልሆነ የሃብት ክፍፍልና  አምባገነናዊ አገዛዝ በሃገራቸው የመኖር ተስፋ አጥተው በሱዳን እና በ ሊብያ በረሃ የማንም አረብና ጥቁር መጫወቻ  ሰለሆኑት እህቶቻችን ምነው ዝም አልክ? አለም ደቻሳ በኢትዮ. ኢምባሲ በር ላይ በአረቦች ስትደበደብና ስትጎተት ለዚህ ሁሉ የዳረገንን የአስተዳደር ብልሹነት መሆኑን እያወቅክ ምነው ልሳንህን ያዘው? ዛሬ በአዲስ አበባ እና በተለያዩ ከተሞች የውጭ ዜጋ የሆነ ጥቁር ይሁን ነጭ እንዲሁም  ካገሬውም ሰው ቢሆን ትንሽ ገንዘብ ለማግኘት ለስጦታ እንደተዘጋጀ የገበያ እቃ ራሳቸውን አሳምረውና ተሽቀርቅረው ሰለሚቀርቡት በሺዎች ለሚቆጠሩ የእህቶቻችን ጉዳይስ  ዜናው አልደረሰህ ይሆን?   እዛው አፍንጫህ ስር በአለቆችህ ቀጭን ትእዛዝ ጋዜጣ ላይ ሃሳባቸውን ስለገለጹ ብቻ  በአሸባሪነት ተከሰው ወህኒ ስለተወረወሩት ስለ እነ እስክንድር ነጋ ፣ ርእዮት እና ሰለብዙ የግፍ እስረኞች ጉዳይስ ትንሸ  አቆጠቁጥህም?  ከእነዚህና  ከመሳሠሉት በላይስ ሃገራዊ ውርደት አለ?

ለቤቲ ቤተሰቦች፣ ጓደኞች፣ ዘመዶችና ለመለው ህብረተሰባችን በሙሉ

ቤቲ አንዲት ኢትዮጵያዊ እህታችን በሃገራችን ያለውን ባህላዊ፣ ማህበረሰባዊ እና ስነልቦናዊ ጫናዎችን ተቋቁማ በዚህ መድረክ ላይ በመሳተፏ አድናቆት ይገባታል:: በመዘናጋት ትንሽ መጠኑ ከፍ ያለና ባታደርገው ሁላችንም የምንመርጠው ነገር ግን ሁሌም እኛ ባሰብነው ብቻ  ሳይሆን ባላሰብነው መንገድ ነገሮች ተከስተው ቤቲ ይህንን ነገር ብታደርግም ምንም ማለት ያልሆነና  ቀጣይ ቆይታዋ የተሳካ  ሆኖላት ጥሩ ውጤት እንድታመጣ ሁላችንም ከሆኗ ልንሆንላት ይገባል:: ወደድንም ጠላንም ቤቲ የኛው እህት፣ የኛው ልጃችን ናት:: እንደስህተትም ከተቆጠረባት የሚሰራ ሰው ይሳሳታልና ስህተቷን አስተካክላ ነገ  የተሻለ ስብእና እንዲኖራት ሁላችንም ከሆኗ እንሁን:: ስሜቷን ከሚጎዱ መንፈሷን ከሚረብሹ ድርጊቶች ተቆጥበን በሰላም ተቀብለን የቀድሞ ህይወቷን ምንም ባለመሳቀቅ እንድትቀጥል እንርዳት እላለሁ ::

 

አመሰግናለሁ::

 

የምልህ አለኝ የሚለኝ ካለ ይሄው መገኛዬ…. fasil_ayal@yahoo.com

 

 

24 Comments

  1. I think the issue is a closed one .There is no need to dwell again and again on trivial
    issue as it is exclusively a personal affair. Leave Betty alone . Rather it is better to discuss in earnest the issue on how we can bring down those woyane thugs and tyrants like Alemneh wase and other opportunist self -styled journalists including those bunch of mercenary artists .

  2. ደግ አደረገች። እሰይ ቤቲ ደግ አደረግሽ። ”ከእናንተ መካከል ሃጢያት የሌለበት አስቀድሞ በድንጋይ ይውገራት” ነበር ያለው ጌታ?!ወሬኞች!!!

  3. ቤቲን ለማሞካሸት የግድ ሌላ ሰውን ማዋረድ አይገባም
    አለምነህም ቢሆን የራሱን አስተያየት ነው የተናገረው። ዝም ብለህ እንዴት ቤቲ ኢትዮጵያን እንዳላስቀየመች ብታስረዳን ይመረጥ ነበር

  4. yehe seletane new kalachu ,,yemechachu

    ende ,,awo betyegnan becha sayhon ye Ethiopian Sem be metfo Gonu asteretalech !!!
    yasafral!!yemegermew konjo setoch lemen ,,,,.,,,,,,??????
    asafari new abo !!!

  5. truwe tazebahwale ,,,ye alwe nager ye tematat ena anaduwe ka anduwe ye meiyagceh nw . sasebawe dagemo siysamwe men honagey nw sayle ye meikare ayemaselegenm .. bitty batsast truwe nbr gn hona kahona bhola weda hoal yemeiymalse nager yelam yelek edatshenf eradeteo almwa endiysak maderg enjy makniytuwem ,le erasuwem lasebachwem alma ,,,la ahgre tetekamalech ena .Shtate bihonem ngru Wye gn bakate batedegfuwatem tewate erasuw tewatwe .

  6. ለግልሙትና ክብር ለመስጠት መረባረባችሁ ያስገርማል። በቲቪ ላይ ከማታውቀው ወንድ ጋር በአደባባይ ራስዋን ማስነወሯ ምን ክብር አለበት? የአገሩ ይቅር። ገንዘብና ለመታወቅ ፍለጋ ባይሆን ኖሮ ምናልባት ወንድ ጠፍቶ ቸግሯታል ይባል ይሆናል። በነገራችን ላይ ይኸ በዓለም ዙሪያ ትልቅ ንግድ ነው። የንግድ ዕቃዎቹም ሁልጊዜ ሴቶች ናቸው። ይሸጣሉ ይለወጣሉ። በቅድሚያ ግን ሥልጣኔ ለማስመሰል ቃለ መጠይቅ፣ ውድድር፣ ሽልማት፣ ወዘተ ይባላል። የአገራችን ወጣቶች በአንድነት ተነሥተው ዕድል ፈንታቸውን ካላስከበሩ በስተቀር ቀስ በቀስ ሊወድሙ ነው። የሥራ ዕድል የለም። ትምህርቱ ቅጥ ያጣ ነው። ተምሮ ደክሞ ለዐረብና ለደቡብ ሱዳን ግርድና መግባት ብቻ ሆኗል። አገር ይህን ለማች ይባላል። የልማቱን ፍሬ ግን የሚቃመሱ ጥቂቶች ናቸው። በዚህ ላይ መሪዎች የአገሪቷን ንብረት እየመዘበሩ ነው። ኮንዶሚኒየም እናድልሃለን እያሉ 10 ዓመት ያንገላቱታል። ወጣቶች ቀስ በቀስ በሞራልና በአካል ሞተው እየረገፉ ነው። ሴቶችና ወጣቶች በምድራቸው ምርጫ ስላጡ ኬላ እየተሻገሩ ራሳቸውን ሽጠው የኑሮን ጣእም ለመቅመስ ይታገላሉ። ሩቅ ሳይሄዱ የአዲስ አበባን ከተማ ማየት ይበቃል። ከተማዋ ሰዶም ሆናለች። የአገር መሪዎች ቀን ቀን አገሪቷን ይመዘብራሉ፤ ማታ ማታ ወጣት ሴቶችን ያባልጋሉ። እንደማንኛውም ወጣት ጂንስና ስኒከር መልበስ ሲያምረው ወይ ይሠርቃል ወይም ራሱን ይሸጣል። ወይም ይሰደዳል። በመጠበቅ ምን ለውጥ መጣ። ምርጫ በደረሰ ቁጥር ይህን እናደርጋለን፣ ይህን እናመጣለን ሲባል ይኸው ሃያ ዓመት አለፈ። ወጣቱ እንዳለፈው ትውልድ ተነሥቶ መብቱን ማስከበር ይኖርበታል። የባለ ሥልጣናት ቤተሰቦችና ልጆች እንደ ማንም ሰው አይደሉ? አገርስ የነርሱ ብቻ ነው ማን አለ? ልጆቻቸው ዓይነተኛ ትምህርት ሲማሩ ሥራ ሲይዙ ሲያገቡ ልጆች ሲወልዱ ለሕክምና ውጭ ሲላኩ ንግድ ሥራ እፈለጉበት ሄደው ሲሰሩ ቤት ሲያሰሩ ሌላው ምን አነሰውና ነው ከዚህ ሊቋደስ የተከለከለው? ወጣት መነሳትና ሕገ መንግሥት በሚያዝለት መሠረት መብቱን መናጠቅ አለበት። አማራጩ ቀስ በቀስ መሞት ነው።

  7. ስማ እንደማስበው ላንድ አንድ ዌብሳይቶች ጽሁፎችን እልካለው በጣም (busy) ነኝ ብለህ ለምጎርር ነው እንጂ አለምነህ ዋሴ እንደዚ አላለም ወይም ሊል አልፍለገም:: እኔ ጽሁፉን አልጨርስኩትም ልክ እንደጀምርኩት የው ያቆምኩት ለምን ከላይ እንደጽፈኩልህ ለምጎርር እንዲምችህ ነው:: ያንተህ አይነቶች ናችው ያልተባለ ተባለ ብለው ሰውን የሚያደነቁሩ:: ለማንኛውም ይህውላችሁ ሊንኩ::www.diretube.com/big-brother-africa/journalist-alemeneh-wase-disgusted-by-betty-on-bba-video_ea2cfebc4.html

  8. ስማ ለእህትህም ቢግ ብራዘር አፍሪካ ላይ ባይሆንካን በኢትዮ ታለንት ሾው ላይ እንድታቀርብ ምከራት::

  9. Wow someone took time to criticize Alemeneh for commenting the indecent sexual act or sex committed by a matured school teacher named BETTY, for setting a bad precedent for millions of young Ethiopian girls. I am even surprised by the author FASIL not even saying a word against BETY, People against Alemneh are concerned for the millions of young girls and the social consequence of performing sex in public rather Stupid people like this diaspora FASSIL worry about sexual freedom. My advise to EThIOPIAN DISPORA bring knowledge and skill and promote development like diasporas from GHANA, INDIA not prostitution to our country please ETHIOPIAN DISPORA refrain from promoting prostitution and live sex

    • አቶ ሰለሞን ዕድሜ ከጤና ይስጥልኝ….ግብፅ በዓባይ ወንዝ ከተፎካካሪ ፓርቲ ጋር ትሰራለች፣ትመክራለች፣ ትደራጃለች፣ ትታጠቃለች፣የእኛ ቤት አለቅላቂዎች ደንቆሮዋች ዲያስፖራዎች የቺ ከሰው አፍ የቀለባትን ወሬ እንደትልቅ ዕውቀት አድርገውት ይሞላፈጡብናል።ኢህአዴግ ልብ አለው ደጋፊ እነደሌለው ያውቃል። ፈጥነው ቻይና ቂጥ ተለጠፉ፣ደጋፊ ሳይሆን ተደጋፈ ካድሬና ሆድአደር ካድሬ የተሞላው የሙስና ማህበር አባለት ያቀፈው ወያኔ ገብቷቸዋል፤ተስፋ ቆርጠው አቁፋዳቸውን ሽክፈው ሮጡ፡ ለምን ስለአንድንት፣ ኅህብረት፣አብሮ ባጋራ ለሀገር መቆምን ይምከሩ? ዓላማቸው ሁሉ አባልቶ ብቻ መብላት ስለነበር ያቀረቧቸው ዲያስፖራዎች ለወሬ እንጂ ለቁም ነገር አይሆኑም። በዚሁ ድረገፅ አቶ ያሬድ አይቼህ የተባለ ባለጌም ሀገርና ህዝብን በቤቲ ሥም ገብቶ በጥፍሩ ቆሞ ሲሳደብ፣ሲዘልፍና፣ሲያዋርደን ሕዝባችንን ሲያንቋሽሽ…ባፉ ሲፀዳዳ ነበር አንብቡት።” ለመሆኑ የግለሰቧ ቂጥ እንዲህ ከአባይ ግድብ በላይ እንዴት ትኩረት ተሰጠው? እነኝህ ናቸው ኢትዮጵያን ለማጥፋት ያቆበቆቡ ፈረንጅ ያሳደጋቸው ‘ፍናፍንቶች’ ሸዋ ጠተንቀቅ በለው!!ለመሆኑ የዚህ ፊልም አውጭና አባዥ ማነው?

      “አላምነህ ዋሴ የቁንጅና ፈቃድ ቢሮ ሃላፊ'”? ያሬድ አይቼህ እና ፋሲልአሩ የቆነጃጅንት አሻሻጭ ‘ ኪራይ ሰብሳቢ’ ‘ደላላ’ ‘ተጫራች’ ሆነው ነው ሚቀሳፍቱትና የሚቆሉት? ለመሆኑ ቤቲ ለሀገራችን’ አልጋ ላይ ማዕድን ስታስቆፍር ነው ወይንስ ከሴራሊዮን ነዳጅ ስታስቀዳ “ነው የሚያሳው? ይህ ሁሉ አጅቧት፣ አድንቋት፣ አጨብጭቡላት፣ድንኳን ወጥሩላት፣ባንዲራ ኢዛችሁ ተቀበሏት፣ለቤተሰቦቿ አባባ ላኩ፣ጋሪ ይጫን፣ ከበሮ ይጎሸም፣ ሰላማዊ የድጋፍ ሰልፍ ውጡ፣ እየተባለ የሚሻፍዱት? “ቤቲ ስትረካ ለካስ ብዙ ሰው ጠተምቷል’ በለው!! ሀገራችን ኢትዮጵያ የባህልና ቋንቋ ሀይቅ፣ ብዙ ሃይማኖትና የሰው ዘርና የምርጥ የህል ዘር መገኛ ናት! ይህንን ለመበከልም ይሁን ለማጥፋት የተሠማሩ የሚደግፉ ሁሉ ዘራቸው ይመተር! ጥቁር ውሻ ይውለዱ!በለው! ከሀገረ ካናዳ

  10. U think u are civilized u so naive may be u from that kind of family but u don’t have to defened it it is not ur fault having said that betty should get fired from teaching and apply different job which she is good at it like this one there is place for her in addis chechenia where this kind of behavior practice broadly.

  11. Fasil, please if u have personal problem with Alemneh, you can have your own battle field with him. But here is not for the single person ‘Betty’ rather Ethiopia as a whole that is transmitted live to the world. Do you remember the famine in 1983/4 that was transmitted live to the world which then named Ethiopia as famine and hunger stricken country for the single spot of the report? Now world assumes all other girls of Ethiopia as cheap and bitch. Look this way also, there is no substance in your critics.

  12. Mr YARED and FASIL ,what a disgraced and morally buncrapted guys, It is really sad to see DIASPORAS Ethiopians like you trying to promote indecent and immoral things, instead of skill and knowledge of course everybody can give what he has Mr YARED and Mr FASIL have nothing they can teach for their society except Prostitution and ZEMUT,

    Mr YARED it is an open secret that you are A HOMOSEXUAL and a lot of people in your community know that and it is really sad to see you here promoting bilgina and you are already worthless however you should not work hard to make our society worthless like you we know next time you will come to this forum to defend HOMOSEXUALITY as a right, MR YARED you are sick and you need to see a psychatrist

  13. ይህን መጥፎ ድርጊት ምንም እንዳልተሰራ ለማስመሰል እና ለወደፊትም የማበረታታት ያህል፥ ቤቲን መደገፍ ምን ይሉታል? ጋዜጠኛውን መተቸት ይቻላል ግን በዚህ ጉዳይ አይመስለኝም።አለምነህ ኢትዮጵያዊ ጭዋነት የተሞላበት አስተያየት ተናግሯል፣ ለዚህም ሊመሰገን ይገባል።

  14. i have a big problem here .can she have a right what ever she want to do more than any thing that is her vagina her body herself. she has un touchable right to do best for her. the other people have a right too ,that is DO NOT WATCH THE SHOW period .leave her alone .

  15. yebetin lemeshefan lelasewen tefatag mederagi asefalagi adelem batadergew teru neber gin adergawalech selezih yemidersebaten neger hulu mechale yesuwa derasha new asedabi nech ehen demo mamen alebate le birr bela ehen madergi tagebi adelem !

  16. What is your problem there? It’s none of your business. She is not representing your damn country there. Bunch of good-for- nothings. Make your country free of those bush people before you put your nose in someone’s business. What the hell does this Alemneh or who ever know about Bethy.. silly bush people.

  17. What happ en to my people leave her alone we act like we never have saix
    bate be strong you are not the #1 person to do this its your time u yang and gorgeous don’t stop doing what is most important things for u

  18. ye almnewasen kale milelsn zare new yayewut bergix hulum yerasun asteyayet new yemisxew. yemnsexew asteyayet mizanawi bihon ymerxal silezi yesehun asteyayet baninkef tiru new.

Comments are closed.

Share