የዞን 9 ጦማሪያኑ እና ጋዜጠኞቹ በድጋሚ ተቀጠሩ

ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ በፌስቡክ ገጹ እንደዘገበው በእነ ሶሊያና ሽመልስ የክስ መዝገብ በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው በቂሊንጦ እስር ቤት የሚገኙት የዞን 9 ጦማሪያና ጋዜጠኞች በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት ዛሬ ቀርበው ተጨማሪ የጊዜ ቀጠሮ ተሰጣቸው፡፡

አቃቤ ሕግ በተከሻሾች ላይ ያቀረበው የኦዲዮ ሲዲ ማስረጃ እንዲደርሳቸው ባቀረቡት ጥያቄ ላይ ችሎቱ ብይኑን ስላልጨረሰ ለመጋቢት 15 ቀን 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

ጋዜጠኛው እንዳለው ሁሉም ተከሳሾች ከችሎት መጀመር በፊት እስር በእርስ ተቀራርበው እያወጉ እና ፈገግ ሲሉ ተስተውለዋል

ተጨማሪ ያንብቡ:  የአማራ ክልል አዲስ ርእስ መስተዳደር አገኘ
Share