ተደናቁሮ ለማደናቆር የመረጠ ሰርአት ማነው? – ሊቁ እጅጉ

በ 21ኛ ክፍለ ዘመንሰ ድንቁርና የተፈረደባት አገር ማነች ? (ሎሚ-ተራ ተራ)

በ እርግጠኝነት በቅርቡ በዚህ በአሜሪካን አገር ተወዳጀ በሆነው  ጀፐርዲ (Jeopardy!, ) ተብሎ በሚታወቀው እርሦም ይሞክሩት የጥያቄና መልሰ ውድድር  በጥያቄነት መቀረቡ አይቀሬ ነው ተብሎ የሚገመተውን የጥያቄ አርእሰት ነው ይዤላችሁ የቀረብኩት፡፡

አዎ በ እርግጥ ይዞታው አሰቂኝ ቢመሰልም እውነታውን በአንክሮ ለተመለከተው ማንኛውም ዜጋ ግን ከልብ ያሳዝናል ያሰቆጫልም። ተደናቁሮ ለማደናቆር የመረጠው የወያኔ ሰርአት ግን  ማንም ከልካይ በሌለው ሁኔታ ትውልዱን ለ24 አመት በማፈንና  አዕምሮውን እንኳን በእወቀት እንዳየሰፋ ታዋቂና አዋቂ ናቸው ትውልዱን ሀብት ባይሰጡትም እውቀት ያሰገበዩታል ተብለው የሚታመንባቸውን የ ዩንቨርሲቲ አሰተማሪ ፐሮፌሰሮችን ያለምንም አፈረት እውቀትን ለምን አሰፋፋችሁ ? አደናቁሩ አልናችሁ እንጂ ህዘቡ አይኑ ተገልጦ  የእኛን አፍራሽነትና የዘረኝነት ፖሎቲካ አራማጅነት እንዲረዳ በእውቀት አጥምቁ መች አልናችሁ ? የሚሉ ይመሰል ባደባባይ አይናቸውን በጨው አጥበው ማባረሩን ተያይዘውታል ። ይሔ ታዲያ ምን ሰም ሊሰጠው እና ምን ሊባል እንደሚችል በ እውነቱ አሰቸጋሪ ነው ? እርግማን አይመሰላችሁም ? አሁን ዶ/ር ጌታቸውን ማባረር ምን ይባላል?

“እርሳቸው ግን አሁን ገና ኢትዮጵያዊ ሆንኩ ፣ምከንያቱም ኢትዮጵያዊ  መሆን ማለት መብቴ የሚረገጥ ማለት ነውና ” በሚል  የወያኔ ሰርአት ኢትዬጲያዊነትን ምን አክል እንደሚጠላና አላማውና እቅዱ ሁሉ አገር ማፈረሰና ማጥፋት እንደሆነ እንደፍልሰፍና መሁርነታችው በፍልሰፍና ቃል  በጥሩ ሁኔታ ገልጸውታል። ጥያቄው ግን  ያፈጠጠ ሰርአት አልበኝነት እሰከመቼ በዚህ እብሪተኝነት መቀጠል ይችላል ተብሎ ይታመናል ነው ? ሕዝብሰ ይኸንን አይነት አይን ያፈጠጠ ማን አለብኝነት  ሰርአት እሰከመቼ ተሸክሞ ይዘልቃል ? በቃኝ ! በቃኝ አሁንሰ መረረኝ ብሎ አሸቀንጥሮ ለመጣል አቅም ያጣበት ምክነያት  ምን ይሆን ? በእርግጥ ወያኔ በጥናቱ ባሰላው የማደናቆር እቅድ ሕዝቡ ተደናቁሯል ማለት ነው?  ከሆነሰ የእኛ በ ውጭ የምንኖረው አልተደናቆርንም የምንለው ወያኔ አደናቁሮታል ያልነውን ሕዘባችንን የመታደግ ግዴታችንን እንዴት መወጣት እንችላለን ትላላችሁ ? እር ይታሰብበት ጎበዝ እኛንም አደናቆሩን እንበል እንዴ ? አይገባም እንንቃ ሕዘባችንንም እንታደገው ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ያማራ የሕልውና ችግር ሁለቱ ምንጮችና ዘላቂ መፍትሔው

አልታይህ አለኝ አይኔን ጉም ሸፍኖት
አልገለጥ አለኝ እሰትራፖ ይዞት
አይን የሚሸፍን አይን የሚጋርድ
አዲሰ በሸታ ነው “ወያኔ” መሆኑን ሕዘቤ ሆይ ተረዱት
*
ምንድነው ብላችሁ ጥያቄም አቅርቡ
ምላሹን የሚሰጥ ባይኖርም በቅርቡ
ጥያቄም ጠይቁ ለ አቦይ ሰብሀት
ፊት መሪ ለሆነው ለድንቁርና እሳት
ጥያቄም አቅርቡ ለ አቦይ ጸሀይ
ጮቤ ለሚረግጠው በ ሕዘቡ ሰቃይ

*
ዳይሰፖራም ጠይቅ አንተም ተጋርደሀል መደናቆር ይብቃ
በ አንደነት እንቁም የወያኔ ጭፍራ ሴራው እንዲያበቃ።
እንቢኝ በይ ሴቲቱ እንቢኝ በል ወጣቱ እንቢኝ በል ወገኔ
በርቀት መልሰው አጠገብህ ሳይደርሰ የወያኔን ኩነኔ።

በቸር ይግተምን ። አሰተያየት ቢኖሮት በዚህ መላክ ይችላሉ ኢሜል ፤- mwl200825@yahoo.com
ኢትዮጲያ ለዘላለም ትኖራለች !!

 

1 Comment

Comments are closed.

Share