ፕሮፌሰር መስፍን ለሰማያዊ ፓርቲ እራት ግብዣ የ20 ሰው ትኬቶችን እንደገዙ የፌስ ቡክ ጉዋደኞቼ ጽፈው አነበብኩ

 

Prof. Mesfin Woldemariam

ከልጅነታቸው እስከ ሽምግልናቸው ለዚች ሀገር ያላቸውን ሁሉ ሳይሰስቱ የሰጡት ፕሮፌሰር መስፍን፤ ሌላው ቀርቶ የግላቸው የሆነ መኖሪያ ቤት እንደሌላቸው የምናውቅ ስንቶቻችን እንሆን?
አዎ! ለነ አባዲ ዘሙ ድንቅ ቪላ የገነባች ሀገር ባለፉት ረጅም ዓመታት ለፕሮፌሰር መስፍን አንድ ክፍል ቤት አልሰጠቻቸውም። ለአያሌ ዓመታት የኖሩት እና አሁንም እየኖሩ ያሉት ፒያሳ በሚገኝ የኪራይ ቤቶች ህንጻ ውስጥ ተከራይተው ነው።
ይህ ስለሆነ ፕሮፌሰር ፦ “ኢትዮጰያ ሀገሬ ሞኘ ነሽ ተላላ፣
የሞተልሽ ቀርቶ፣ የገደለሽ በላ” እያሉ በቁጭት አላንጎራጎሩም። ይልቁንም በምርጫ 97 ወቅት ለወጣቶች ባደረጉት አንድ ገለጻ ላይ ፦”እቤቴ ስገባ አፍራለሁ”ሲሉ ነው የሰማሁዋቸው። የገረመኝም ይኸው ነው።
“ማደሪያ የሌላቸው በርካታ ዜጎች መንገድ ላይ ወድቀው እያየሁ ማታ እቤቴ ስገባ አፍራለሁ፣ ጎዳና የሚያድሩትን እያሰብኩ እንቅልፍ አይወስደኝም፣ አሁን የምኖርበት የኪራይ ቤት በዝቶብኛል” ነው ያሉት ፐሮፌሰር መስፍን።
ጤና እና ረጅም እድሜ ለጋሽ መስፍን!

Dereje Habtewold
ተጨማሪ ያንብቡ:  ትላንትና ጉሊሶ፣ ዛሬ ደግሞ ዳቢሳ፣ ነገና ከነገ ወዲያስ? - ከመርሐጽድቅ መኮንን አባይነህ

4 Comments

  1. Amlak endnezeh lalut yagerachenen yemerenet botta setto behon minalbat hezbachin hewot lay lewutt ennay neber ! Amlak bettena yasenbeteln Beyans kemedenager yettebqunnal hulgezae aqettacha eyetteqomun kawanabaj aselchee propaganda endehum ye ewnet shimaglae sellettefa esachewu enkuwan yesenbttuln!
    Amlak hoy melkamn gezae endeyayu aqoyelin!!!

  2. Dear author, and the rest of true children of Ethiopia.
    Please allow me to surface few lines of idea about Prof Mesfin. I know most of us Ethiopians are much better in giving lip service than taking responsive action to at least the problem we know and appreciate. I didnot know from Mesfin from close, never met him in person than reading his constructive articles, and hearing about him from others such as this author. From what i read and hear there are several 1000 citizens, mainly the youths who see this prof as raw model. But we still feel that despite he lived for his country, his country didn’t paid him for what he did for he. My idea is why not we (who shall respect the wisdom of knowledge, and contribution of a respected citzen such as Prof Mesfin) will take a responsibility on behalf of our loved mama Ethiopia and do this favor for HER—paying the reciprocity to her true son Prof Mesfin.

    I know some determined people who came together contribute from what they have and build a house and buy a car for these people whom they feel are neglected, and or deserve.

    I know many guys who have such a motive and knew to make it. For instance, Sisay Agena, Tamagn Beyene—there are several people from all around the glob.

    I will be on board! Today one can buy a nice VILA for a less than a million in a nice place in addis! I know this is not easy and small, but possible. Otherwise let us stop talking about some once’s good habit.

    • @Degefa,

      I think you got it all wrong. Prof Mesfin does not need any hand out from us. As the Article stated he feels sorry for those homeless not for himself. So, it will be a great contribution if you help to one of the Foster homes in Addis or somewhere else in the Country. You could also promot for Human right which is the passion of the Prof.

  3. ፕሮፌሰር መስፍን የሃገራችን ሃብት ናቸው። እድሜና እውቀት አንድ ላይ ስክነትን ፈጥረው ሃገራዊና ዓለም አቀፋዊ እይታቸው ሙሉዕ እንዲሆን አድርገውታል። በዚህም የተነሳ በየዘመናቱ ለሃገራችን ህዝብና አንድነት የግፈኞችን በትር ሳይፈሩ በመታገል ላይ ይገኛሉ። በኪራይ ቤት ውስጥ መኖራቸው አያስደንቀኝም። እየዘረፉና ደም እያፈሰሱ፤ አማራ ነው የጨቆነህ እንካ ቆንጨራ እረደው በማለት ኦሮሞው የወገኑን ደም እንዲያፈስ እሳትን የሚቆሰቁሱት የሰሩት ቤት ውጪው ቢያምርም ውስጡ ሰላም የለበትም። ንብረትነቱም ጊዜአዊ ነው። ካለፈው ታሪክ መማር ባንችል ነው እንጂ በፊት በግፍ የቆሙ ቤቶች ዛሬ የት አሉ? አሉ ከተባለስ ማን ይኖርባቸዋል? የሰራው ወይም ዘመድ አይደለም ጠመንጃ ያነገተ እንጂ! የፕሮፌሰር መስፍን ምርጫ ለእኔም ይስማማኛል። ፈጣሪ ሰላምና ጤና ያብዛልዎ!

Comments are closed.

Share