June 4, 2014
35 mins read

በዘመናዊት ኢትዮጵያ ታሪክ ወራሪው ማን ነው? ተወራሪዎቹስ? – ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት

በዘመናዊት ኢትዮጵያ ታሪክ ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ ታላቅ የሕዝብ ቅልቅል ተካሂዷል። ከእነዚህ ምክንያቶች መካከል፦ የአህመድ ግራኝ ወረራ፣ የኦሮሞ ወረራ፣ በዘመነ መሣፍንት የነበሩት የእርስ በእርስ ጦርነቶች፣ ፈፃሜ-ዘመነ መሣፍንትን ያበሠሩት የማዕከላዊ መንግሥትን እንደገና የማዋቀር ጦርነቶች እንዲሁም ሁለቱ የኢጣሊያ ወረራዎች የሚጠቀሱ ናቸው። እነዚያ ጦርነቶች እና የእርስ በእርስ ግጭቶች ከፍተኛ ቁጥር ያለውን የሕዝብ ክፍል ሕይዎት እንዳሣጡ አይካድም። ያንንም ተከትሎ ከኑሮ አስገዳጅነት እና በአገዛዝ ኃይሎች የበላይነት የያዘው አካል በሚፈጥረው የፖለቲካ አሠላለፍ መለዋወጥ ምክንያት የአንዱ ጎሣ ወይም ነገድ አባሎች በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመጥፋት ጉዳት ደርሶባቸዋል። በዚህ ረገድ ከኢትዮጵያ ዋና ዋና ነገዶች እና ጎሣዎች መካከል፦ በምዕራብ ኢትዮጵያ ነዋሪ የነበሩት የጋፋት ነገድ በኦሮሞ ወረራ ሙሉ በሙሉ እንዲጠፉ ሆነዋል ወይም ማንነታቸውን ተገድደው ለውጠው «ኦሮሞዎች» ወይም «ዐማራዎች» ወይም በሌላ ነገድ ስም ይጠራሉ፤ የሜያ ነገድ ተወላጆች ደግሞ በግራኝ አህመድ እና በኋላም ተከትሎ በመጣው በኦሮሞዎች ወረራ ምክንያት ቁጥራቸው በእጅጉ ተመናምኖ ዛሬ በዝዋይ ኃይቅ ውስጥ በሚገኙ ደሴቶች እና አካባቢው ብቻ ተወስነው ይገኛሉ። ጥንት በባሊ (ባሌ) እና ፈጠጋር (አርሲ) ተስፋፍተው ይኖሩ የነበሩት ሐዲያዎች እና ከንባታዎች በኦሮሞዎች ወረራ ተጨፍልቀው «ኦሮሞዎች» ሲባሉ ቀሪ ወገኖቻቸው በደቡብ ምዕራብ ሸዋ በአንድ ጠባብ አካባቢ በተጨናነቀ ሁኔታ እንዲኖሩ ተገድደዋል። ከዚህ በተጨማሪም፦ አርጎባዎች፣ ቀቤናዎች፣ ወርጂዎች፣ አላባዎች፣ ሲዳማዎች፣ ወዘተርፈ በኦሮሞዎች ወረራ ምክንያት ማንነታቸውን እንዲቀይሩ ተገድደዋል፤ ከዚያም አልፎ በጅምላ ተጨፍጭፈዋል። በእናርያ ንጉሥ ግዛት ሥር የነበሩት ጃንጀሮዎች (የም) በኦሮሞ ቆሮዎች (በእነ አባ ጅፋር) በገፍ በባርነት ተፈንግለዋል። የዳውሮ እና የገሙ ሰዎች ደግሞ ግዛታቸውን በኦሮሞ ወራሪዎች ተነጥቀዋል። በመሆኑም የዘመናዊት ኢትዮጵያን የሕዝብ አሠፋፈር ጥንቅር ለውጥ ለመገንዘብ ከአህመድ ግራኝ ወረራ ጀምሮ ማዬቱ ለበለጠ ግንዛቤ ይረዳል።

ግራኝ አህመድ በኢትዮጵያ ላይ ወረራውን የጀመረው የንጉሡ የአፄ ልብነድንግል ሹም እና የደዋሮ (ምዕራብ ሐረርጌ) ገዢ ከነበረው ከአዛዥ ፋኑኤል ጋር በ፲፭፻፲፯ ዓ.ም. ባደረገው ውጊያ ነበር። ግራኝ አህመድ ዘንተራ (ደንቢያ፣ ሰሜን ጎንደር፣ ጣና ሐይቅ አጠገብ) በአፄ ገላውዲዎስ ሥር ሲዋጉ በነበሩት የፖርቱጋል ወታደሮች የጥይት አረር ተመትቶ በየካቲት ፳፯ ቀን ፲፭፻፴፭ ዓ.ም. እስኪገደል ድረስ ኢትዮጵያን ለ፲፱ ዓመታት ያህል በጦርነት አመሠቃቅሏታል፤ ዜጎቿን ኍልቆ-መሣፍርት ለሌለው ግፍ እና በደል ዳርጓቸዋል። የእርሱን የወረራ ፍፃሜ እግር በእግር ተከትለው የመጡት የኦሮሞ ወራሪዎች ደግሞ ከ፲፭፻፵ዎቹ ጀምረው ከደቡብ ከነጌሌ ቦረና አካባቢ ተነስተው ከፊታቸው የነበረውን የሌላውን ነገድ እና ጎሣ ሕዝብ ዕድሜ እና ፆታ ሣይለዩ በጅምላ እየፈጁ እስከ ትግራይ ድረስ ዘልቀዋል። ኦሮሞዎች አብዛኛውን የኢትዮጵያ ክፍል በተከታታይ ወረራዎች ለመያዝ የፈጀባቸው ጊዜ ከ፫፻ ዓመታት ይበልጣል። ስለዚህ ዛሬ ያለውን የኢትዮጵያን የሕዝብ አሠፋፈር በቅጡ ለመረዳት ያለፈውን የ፩፻፳ ያመታት ብቻ ታሪክ ሣይሆን አህመድ ግራኝ ኢትዮጵያን ከወረረበት ከ፲፭፻፲፯ ዓ.ም. ጀምሮ የነበረውን ሁኔታ መመርመር የግድ ያስፈልጋል። ሆኖም ባለፉት ፵ እና ፶ ዓመታት በኢትዮጵያ የፖለቲካ እንቅስቃሴ «መሪዎች ነን» ብለው የተነሱ ልሂቃን የኢትዮጵያን የረዥም ዘመን የታሪክ ጉዞ በ፻ ዓመታት ብቻ በመገደብ በጉንጭ አልፋ ውዝግብ ሕዝብን ሲያተራምሱ ይታያሉ። በተለይም ለዚህ ውዝግብ ቀዳሚዎቹ የትግሬ እና የኦሮሞ ልሂቃን ሲሆኑ እንደ ዋለልኝ መኮንን ዓይነቶቹ ጥራዝ ነጠቅ የዐማራ ልሂቃንም በዚህ ክበብ ውስጥ ይገኙበታል።

ታሪካቸውን በቅጡ ያልተረዱ ጥቂት፣ አክራሪ እና ዘረኛ የሆኑ የኦሮሞ ልሂቃን፣ ከጀርመናውያን የኃይማኖት ሠባኪዎቻቸው የተጋቱትን ለኢትዮጵያዊነት እና ለዐማራ ያላቸውን ጥላቻ እንደበቀቀን ደግመው፣ ደጋግመው ሲጮኹ ይሰማሉ። ለመሆኑ የዚህ አስተሣሰብ ምንጩ ከዬት ነው? በዘመነ ቅኝ አገዛዝ የአፍሪካ ቅርምት ወቅት፣ እንግሊዞች፥ «ግብፅን መቆጣጠር ማለት ቀይ ባሕርን መቆጣጠር ማለት ነው፤ ቀይ ባሕርን መቆጣጠር ማለት ደግሞ መላውን የመካከለኛውን ምሥራቅ መቆጣጠር ነው፤» ብለው በማመን ግብፅን «የገንዘብ ብድር ዕዳን» ሠበብ በማድረግ ከቱርኮች ነጥቀው ቅኝ ግዛታቸው አደረጓት። እንደዚያም ሁሉ፣ የሮማ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ሠባኪዎች «ቻይናን ስጡን እና እስያ የእኛ ትሆናለች» ብለው ሰላዮቻቸውን በኃይማኖት ሠባኪነት ሽፋን በቻይና አሠማሩ፥ ቻይናም ቀስ በቀስ በምዕራባውያን ተፅዕኖ ሥር ወደቀች። የኦነግ እና የኦሕዴድ የንስሃ አባታቸው የሆነው ጀርመናዊው ሰላይ ዩሓን ክራፍ በበኩሉ «ጋሎችን ስጡን እና መላው የመካከለኛው የአፍሪቃ ክፍል የኛ [የጀርመኖች] ይሆናል፤» በማለት ጀርመን የኦሮሞን ነገድ ተጠቅሞ ምሥራቅን እና መካከለኛውን የአፍሪቃ ክፍል በቅኝ ግዛቱ ሥር የሚያውልበትን መንገድ መጥረጉን እናያለን። ስለሆነም «የነፃ ኦሮሚያ» ዓላማ አራማጆችም «ኦሮሚያ» ከሚባለው አዲስ ወያኔ-ሠራሽ ግዛት ጀምሮ የሚያራግቡት ተግባር ሁሉ፣ በ፲፱ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን ሠፊውን የኢትዮጵያ አካል ቆርሶ ለጀርመን የቅኝ ግዛት ለማድረግ የታቀደው ሤራ በዚህ በእኛ ዘመን ታድሶ መቅረቡን መገንዘብ ያስፈልጋል።

ከዚህ በተጨማሪ ዩሓን ክራፍ፣ ጀርመን በአውሮፓ ፖለቲካ እና ኢኮኖሚ የበላይነቱን እንድትይዝ ያለውን ፍላጎት እንደሚከተለው ገልጿል፥ «“ጋሎችን” መያዝ መካከለኛው አፍሪቃን ለመቆጣጠር ከማስቻሉም ሌላ፣ በቀይ ባሕር ዳርቻ የሚገኙትን አገሮችን መያዝ ከንግድ መቆጣጠሪያነት ባሻገር፣ ጀርመን በአውሮጳ ያላትን የበላይነት ማረጋገጥ እና የጀርመንን ሥልጣኔ በዐረቦች ምድር፣ በአበሻ እና በመላው ምሥራቅ አፍሪቃ ማስፋፋት ነው። የጀርመን በምሥራቅ አፍሪቃ መስፋፋት፣ የእስልምና ኃይማኖት በዐረብ ምድር እና በአፍሪቃ ጠረፎች የሚያደርገውን መስፋፋት የሚያዳክም፣ የዐረቦችን የባሪያ ንግድ የሚቀንስ፣ እንዲሁም የምሥራቅ አፍሪቃን ሕዝብ አረመኔነት በክርስትና ሥልጣኔ መዋጋት ነው። ከአበሻ በስተደቡብ ያሉት “ጋሎች” የሠፈሩበት ቦታ ለአውሮጳውያን ሠፋሪዎች ምቹ ቦታ ነው፤» በማለት ጀርመን የኦሮሞዎችን ልብ ከኢትዮጵያዊነት ስሜት በማውጣት ምሥራቅን እና መካከለኛውን አፍሪቃ እንዴት በቁጥጥሩ ሥር ማዋል እንደሚችል «ወንጌላዊው» ክራፍ ምክሩን ለግሷል፤ ምክሩም የመከነ አይመስልም፤ ኦነግን እና መሰል ድርጅቶችን አፍርቷል። ለአብነትም ያህል ለኦነግ መመሥረት እና መጎልበት የስካንዴኔቪያን አገሮች፣ ጀርመኖች እና ሌሎችም የቅኝ ገዢነት ቅዠታቸው ያልለቀቃቸው አውሮጳውያን የሚያደርጉትን ሁሉን-አቀፍ ድጋፍ ልብ ይሏል!

በማስከተልም ዩሓን ክራፍ፣ ከሸዋ በስተደቡብ የሚኖሩት “ጋሎች” ብዛት ያላቸው መሆኑን ገልጦ፣ የእስላሞችን የመሥፋፋት ወረራ ሊመክቱ እንደሚችሉ እና የአፍሪቃ ጀርመኖች ሊሆኑ እንደሚችሉ ዕምነቱን አስረድቷል። ዩሓን ክራፍ ምሥራቅ እና መካከለኛው አፍሪቃ በጀርመን ቁጥጥር ሥር እንዲውል የነደፈው አንዱ ሥልት፣ ሚሽነሪዎችን በወንጌል ማስፋፋት ስም በአካባቢው በማሠማራት፣ የየአገሮቹ ልዩ ልዩ ነገዶች እና ጎሣዎችን ሊለያዩበት እና ሊናቆሩበት የሚችሉበትን ዘዴ ማጥናት፣ እንዲሁም ያገኟቸውን የማናቆሪያ ቀዳዳዎች ማስፋት ነበር። ለዚህም ዩሓን ክራፍ ያቀረበው ኃሣብ፦ «በደቡብ እና በምዕራብ ኢትዮጵያ የሚኖሩ የኦሮሞ ተወላጆችን ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ነገዶች በመለዬት፣ በተቃራኒው ተበታትነው ይኖሩ የነበሩትን የኦሮሞ ጎሣዎች አንድ የሚያደርግ አዲስ መጠሪያ ስም በመስጠት፣ በዚህ አዲስ ስም የሚታወቅ የአካባቢ ስም ፈጥሮ፣ ያን አካባቢ ከቀረው የኢትዮጵያ የሚገነጥል ብሔርተኛ ቡድን በጀርመን ሁለንተናዊ ርዳታ ማጠናከር፤» የሚለው ነበር። ለዚህም «“ጋላ” የሚለው ስም ሁሉንም የነገዱን አባሎች አጠቃሎ ለመጥራት አያስችልም» የሚል ምክንያት በመስጠት፣ «ኦርማኒያ» ከሚለው ስም «ኦሮሚያ» የሚል ቃል በማውጣት ጥንት “ጋላ” በመባል የሚታወቀው ነገድ በዚህ እርሱ ባወጣው አዲስ ስም እንዲጠራ እና «ኦሮሚያ» ለሚባል ክልል ነፃ መውጣት እንዲታገል በወንጌል ማስፋፋት ስም አስተማረ፣ ሰበከ። በዚህ መሠረት ዩሓን ክራፍ ራሱ «ኦሮሚያ» ብሎ የሰየመውን የኢትዮጵያ አካል መቆጣጠር ማለት፣ ምሥራቅን እና መካከለኛውን አፍሪቃ መቆጣጠር እንደሆነ በማመን የጀርመን ተስፋፊዎች ዓይናቸውን ኢትዮጵያን በማፍረስ ላይ እንዲያነጣጥሩ ምክር ለገሠ።

የዩሓን ክራፍ እና የመሠሎቹ ምክር በጀርመን ቅኝ ገዢዎች ልብ ውስጥ መስረፁ ማስረጃው ጀርመን በአፍሪቃ አኅጉር ላይ ትከተል በነበረው የቅኝ ግዛት ፖሊሲ ላይ ጉልህ አሻራ አኑሯል። በዚህ ረገድ እስከ ፩ኛው የዓለም ጦርነት ድረስ ጀርመኖች ከምሥራቅ አፍሪቃ፥ ታንዛኒያን፣ ሩዋንዳን እና ብሩንዲን፤ ከምዕራብ አፍሪቃ ቶጎን፣ ከፊል ጋናን እና ካሜሩንን፤ ከደቡባዊ አፍሪቃ ደግሞ ናሚቢያን በቅኝ ግዛትነት በያዙበት ወቅት ከእንግሊዞች፣ ፈረንሣዮች እና ጣሊያኖች በከፋ ሁኔታ ያካሄዱት የከፋፍለህ-ግዛው የቅኝ አገዛዝ አካሄድ አይረሣም። ከሁሉም መዘንጋት የሌለበት አብይ ነጥብ፥ በ፲፱፻፹፮ ዓም በሩዋንዳ በሁቱዎች እና በቱትሲዎች መካከል የደረሠው የዘር ዕልቂት እና በብሩንዲም በየጊዜው በዘር ልዩነት ምክንያት የሚደረገው መተላለቅ ሠንኮፉ በጀርመን ቅኝ ገዢዎች የተተከለ እና በኋላም ጀርመኖቹን በተኩት ቤልጂጎች ዳብሮ በዘመናችን ደግሞ በፈረንሣዮች የተተበተበ የተንኮል ድር ድምር ውጤት መሆኑን ነው። በእኛም አገር በኢትዮጵያ፣ ላለፉት በርካታ ዓመታት በዩሓን ክራፍ መሠሎቹ አመለካከት ተኮትኩተው ያደጉ የኦሮሞ ልሂቃን የሚያቀነቅኑት አስተሣሰብ አለ። ይኼውም፥ የያዙትን የኢትዮጵያዊነት ማንነት ለማስጠበቅ ሣይሆን ለማጣት በሚያስገድድ መልክ በራሣቸው ላይ ዘመቻ ከፍተው፣ ለሌሎች ኢትዮጵያውያን ቀርቶ ለራሳቸው ሊሰሙት የማይፈቅዱትን ጩኸት ሲያሰሙ ይደመጣሉ።

ለመሆኑ ጥቂት የኦሮሞ ልሂቃን ነገዳቸውን “ጋላ”፣ ቋንቋቸውን “ጋልኛ” የሚለውን ዐማሮች እንደሰጡዋቸው አድርገው የሚያቀርቡት ታሪካዊ መሠረት አለው? በመሠረቱ “ጋላ” እና “ጋልኛ” የሚሉትን ስሞች ዐማራው አላወጣቸውም። እንዲያውም የኦሮሞን ታሪክ በስፋት እና በጥልቀት ያጠኑ ሰዎች እንደሚያስገነዝቡት “ጋላ” ማለት እስላምም፣ ክርስቲያንም ያልሆነ ማለት እንደሆነ ያብራራሉ። የቃሉም ምንጭ ሶማሊኛ እንደሆነ ያስገነዝባሉ። በሌላ በኩል “ጋላ” ማለት ግመል ማለት ነው የሚሉም አሉ። ሌሎች ደግሞ “ጋላ” የሚለው ቃል «ገላ» ከሚለው የኦሮሚኛ ግሥ የወጣ መሆኑን እና ትርጉሙም «ወደ ቤታችን መሄድ ፈለግን፣ ወደ ቤታችን ሄድን ወይም ገባን» ማለት እንደሆነ ያስረዳሉ። ይህም ትርጉም ኦሮሞዎች በሶማሌና በባንቱ ጎሣዎች ተገፍተው፣ ከነበሩበት ከምሥራቅ አፍሪቃ የሕንድ ውቅያኖስ ዳርቻዎች ፈልሰው ወደ ደቡብምሥራቅ ኢትዮጵያ ግዛት፥ ወደ ባሌ፣ የተጠጉበትን ዘመን በማውሣት፣ በሰላም ተረጋግተው የሚኖሩበትን ሥፍራ ፈልገው ማግኘታቸውን የሚያመለክት ስያሜ እንደሆነ ብዙዎች በትርጉሙ ይማማሉ። ስለዚህ ጥቂት ዘረኛ የኦሮሞ ልሂቃን «“ጋላ” የሚለውን የስድብ ስያሜ የሰጠን ዐማራው ነው፤» የሚሉት የራሣቸው የማንነት ቀውስ ያስከተለባቸው ግራ መጋባት ከመሆን ውጭ ሌላ አሣማኝ ምክንያት የላቸውም። «ዐማራ ይህንን መጠሪያ ሰጠን» የሚሉትም ውንጀላ ፍፁም መሠረተ-ቢስ ሐሰት ነው። በአንፃሩ «ኦሮሞ» እና «ኦሮሚያ» ለሚሉት መጠሪያዎች የታወቀ ፈጣሪ አላቸው፦ እርሱም አፍቃሬ ቅኝ ገዢዎች የነበረው ጀርመናዊው ዩሓን ክራፍ ነው።

ዩሓን ክራፍ «ጋላ» የሚለውን ቃል ለመቀየር ያነሣሣውን ኃሣብ ሲያስተነትን፦ «ጋላ» የሚለውን ቃል ሲተረጉም «ስደተኛ» ማለት እንደሆነ እና ይህም መጠሪያ በዐረቦች እና በ«አበሾች» የተሰጠ እንደሆነ ይገልፃል። በአንጻሩ እርሱ የፈጠረው «ኦርማ» ወይም «ኦሮማ» ማለት ትርጉሙ «ጎበዝ» ማለት እንደሆነ ያምናል። በእርሱ አባባል «ጋሎች» ለራሣቸው እና ለሚኖሩበት አካባባቢ አጠቃላይ የወል መጠሪያ ስለሌላቸው «ኦርማኒያ» ተብለው እንዲጠሩ ኃሣብ አቅርቧል። ሆኖም ይህንን የዩሓን ክራፍን ኃሣብ የእርሱ-ቢጤ የሆኑ የዘመኑ ሚሽነሪዎች እና ተመራማሪዎች እንኳን አልተቀበሉትም። ለምሣሌም ያህል፦ ኢትዮጵያን ያጠኑ እንደ ዶክተር ቻርለስ ቴ ቢክ ያሉ የመልከዐምድር ተመራማሪዎች፣ ለኦሮሞዎች «ጋላ» የሚለውን ስም የሰጡዋቸው ዐረቦች እና «አበሾች» አለመሆናቸውን እና ስሙ ከራሣቸው ቋንቋ የተገኘ እንደሆነ ይሞግታሉ። ይሁን እንጂ፣ ዕውነቱን ትተው ውሸቱን፣ ሠፊውን ጠልተው ጠባቡን፣ የሚያኮራውን ንቀው የሚያቀልለውን፣ የሚያስከብረውን አውግዘው የሚያዋርደውን፣ የመረጡት ጥቂት «ተማርን ያሉ» የኦሮሞ ልሂቃን፣ የዩሓን ክራፍን ስብከት አምነው ተቀብለው፣ ዐማራን እና ኢትዮጵያን ከምድረ-ገፅ በማጥፋት፣ «ኦሮሚያ» የተባለ አዲስ አገር በመመሥረት እንቅስቃሴ ላይ ከተሠማሩ ከግማሽ ምዕተ-ዓመት በላይ አድርገዋል። ወራሪ የሆኑትን ኦሮሞዎችን እንደ ተወራሪ በመቁጠር፣ ወያኔም ዮሓን ክራፍ የሰጠውን የአካባቢ መጠሪያ በማፅደቅ፣ ዐማሮችን እና ሌሎችን ኢትዮጵያውያን ከአፅመ-ርስታቸው በማባረር፣ «ኦሮሚያ» የሚል አዲስ ግዛት ፈጥሮላቸዋል።

«እንግዳ ሲሰነብት፣ ባለቤት የሆነ ይመስለዋል፤» የሚሉት አባባል አለ። እንግዶቹ እና ወራሪዎቹ ኦሮሞዎች፣ የነባሮቹን የኢትዮጵያ ነገዶች እና ጎሣዎች ግዛቶች በወረራ ይዘው፣ የገደሉትን ገድለው፣ የሠለቡትን ሠልበው፣ ጡት ቆርጠው ሲያበቁ፣ ተበዳዮቹ «ይህ በደል ተፈፀመብን» ሣይሉ፣ እንዲያውም እነርሱ «ተበደልን» ብለው በወረራ የያዙትን አገር እንገንጥል ይላሉ፣ ነባሮቹን ኢትዮጵያዊ ነገዶች እና ጎሣዎች ያፈናቅላሉ። እነርሱው ነባር የአካባቢ ስሞችን ለውጠው እና በነገዳቸው ስም ቀይረው መያዛቸው እየታወቀ፣ «ዐማራው ስማችን እንድንቀይር አስገደደን፤ ቋንቋችንን፣ ባህላችንን እና የየአካባቢ ስሞችን ለወጠብን» እያሉ ስም ሲያጠፉ ይሰማሉ። ሃቁ ግን የአካባቢ ስሞችን በመለወጥና በራሱ ነገድ ስም በመጥራት የሚታወቀው የኦሮሞ ወራሪ ኃይል ነው። የታሪክ ሠነዶችን ማጣቀስ ካስፈለገም፥ በ፲፮፻ኛው ክፍለ ዘመን ኢትዮጵያን ከጎበኙት እና በአገሪቱም ተቀምጠው የሕዝቡን የአኗኗር ልማድ እና ዘይቤ በቅርበት እያጠኑ የታሪክ መድበሎችን ካበረከቱልን የአውሮፓ ሊቃውንት መካከል ፔድሮ ደ-ኮቪልኻም፣ አባ ፍራንሴስኮ አልቫሬዝ እና ሌሎችም የፖርቱጋል ዜጎች አያሌ ጠቃሚ የታሪክ ማስረጃዎችን ትተውልን አልፈዋል። እንዲሁም አህመድ ግራኝን ተከትሎ የዘመተው፣ እርሱ ባደረጋቸው ወረራዎች ሁሉ የቅርብ ተሣታፊ የነበረው የመናዊው ሺሃብ አድ-ዲን አህመድ ቢን አብድልቃድር ቢን ሣሌም ቢን ዑትማን፣ «ፉቱህ አል-ሓበሻ» በተባለው የታሪክ ድርሣኑ የዚያን ዘመን የኢትዮጵያን የሕዝብ አሠፋፈር ቅጥ በዝርዝር መዝግቦት ይገኛል። በእነዚያ ጽሑፎች ውስጥ «ጋላ» ወይም ኦሮሞ የሚባል ነገድ ዛሬ «ኦሮሚያ» ተብሎ በተከለለው አብዛኛው የኢትዮጵያ ግዛት ስለመኖሩ በአንዱም ጭራሽ አልተጠቀሰም። ስለዚህ የዛሬው ዘመን የኦሮሞ ልሂቃን የጥንት አባቶቻቸው በወረራ የያዙትን ግዛት እንደ አፅመ-ርስት ቆጥረውት ሌላውን ኢትዮጵያዊ ሲያፈናቅሉ ሃግ ሊባሉ ይገባቸዋል። ከኦሮሞ ወረራ በፊት ዛሬ ወለጋ፣ አርሲ፣ ወሎ፣ ኢሉባቡር፣ ወረኢሉ፣ ወረሂመኖ፣ ወዘተርፈ በመባል የሚታወቁት የቦታ (የአካባቢ) ስሞች የሚታወቁት እና የሚጠሩት በሌሎች ስሞች ነበር። የሚከተለውን ሠንጠረዥ እንዲሁም አባሪ ካርታዎችን ፩ እና ፪ ልብ እንበል።

ከኦሮሞ ወረራ በፊት ዛሬ ወለጋ፣ አርሲ፣ ወሎ፣ ኢሉባቡር፣ ወረኢሉ፣ ወረሂመኖ፣ ወዘተርፈ በመባል የሚታወቁት የቦታ (የአካባቢ) ስሞች
ተ/ቁነባር ስምበኦሮሞዎች የተሰጠው ስምየትኞቹን አካባቢዎች እንደሚገልጽበአካባቢው ነዋሪ የነበሩ ነገድና ጎሳዎች
1ቢዛሞቄለምምዕራብ ወለጋጋፋት፣ ዐማራ፣ ሽናሻ፣ ቤንሻንጉል፣ አንፊሎ፣ ሌሎች፣ እንዲሁም የጠፉ ነገዶች እና ጎሣዎች
2ዳሞትሌቃምሥራቅ ወለጋጋፋት፣ ዐማራ፣ ሌሎች፣ እንዲሁም የጠፉ ነገዶች እና ጎሣዎች
3እናርያኢሉ አባቦራኢሉባቦርዐማራ፣ ከፊቾ፣ ሌሎች፣ እንዲሁም የጠፉ ነገዶች እና ጎሣዎች
4ገሙጂማጂማየም (ጃንጀሮ)፣ ገሙ፣ ዳውሮ (ኩሎ)፣ ሌሎች፣ እንዲሁም የጠፉ ነገዶች እና ጎሣዎች
5ገንዝጅባት እና ሜጫምዕራብ ሸዋጋፋት፣ ዐማራ፣ ሌሎች፣ እንዲሁም የጠፉ ነገዶች እና ጎሣዎች
6ግራርያሰላሌሰሜን ሸዋጋፋት፣ ዐማራ፣ ሌሎች፣ እንዲሁም የጠፉ ነገዶች እና ጎሣዎች
7እንደጥናእንጦጦ፣ ጉለሌ፣ የካአዲስ አበባ ዙሪያሜያ፣ ዐማራ፣ ሌሎች፣ እንዲሁም የጠፉ ነገዶች እና ጎሣዎች
8ኦ(ወ)ይጃየረር እና ከረዩምሥራቅ ሸሜያ፣ ሐዲያ፣ ዐማራ፣ ከምባታ፣ ሲዳማ፣ ሌሎች፣ እንዲሁም የጠፉ ነገዶች እና ጎሣዎች
9ፈጠጋርአርሲአርሲሐዲያ፣ ከንባታ፣ ሜያ፣ ዐማራ፣ አዳል (አፋር)፣ ሲዳማ፣ ሌሎች፣ እንዲሁም የጠፉ ነገዶች እና ጎሣዎች
10ደዋሮጭሮምዕራብ ሐረርጌሐዲያ፣ ከምባታ፣ ዐማራ፤ ሌሎች፣ እንዲሁም የጠፉ ነገዶች እና ጎሣዎች
11ላኮመልዛወሎደቡብ ወሎዐማራ፤ አዳል (አፋር)፣ አገው፣ ሌሎች፣ እንዲሁም የጠፉ ነገዶች እና ጎሣዎች
12ቤተ-ጊዮርጊስወረኢሉወረኢሉዐማራ
13ቤተ-ዐማራወረሂመኖወረሂመኖዐማራ
14አንጎትራያሰሜን ወሎዐማራ፣ አገው፣ አዳል (አፋር)
15ባሊባሌባሌሐዲያ፣ ከንባታ፣ ሜያ፣ ዐማራ፣ ሲዳማ፣ ሌሎች፣ እንዲሁም የጠፉ ነገዶች እና ጎሣዎች

ስለዚህ በአሁኑ ወቅት አዲስ አበባን «ፊንፊኔ»፣ ናዝሬትን «አዳማ»፣ ደብረዘይትን «ቢሾፍቱ በሉ» እያሉ ለማስገደድ ለሚሞክሩት ዘመነኞች እኛም፥ ወለጋን ቢዛሞ እና ዳሞት፣ ኢሉባቡርን እናርያ፣ ወሎን ላኮመልዛ፣ አርሲን ፈጠጋር፣ ሐረርጌን ደዋሮ፣ ወዘተርፈ ብለን በጥንቱ ስማቸው የምንጠራ መሆናችንን እንዲያውቁት እንሻለን። ወደፊት ካላረፉም በእንግድነት ከኖሩበት አገር «ውጡ» የምንል መሆኑን ሊያውቁት ይገባል። የኦሮሞ ቀለም-ቀመስ ትውልድ ዐማራን በአውራ ጠላትነት ፈርጆ፣ ክንዱን አስተባብሮ ሊያጠፋው ሲነሣ፣ ዐማራው በተቃራኒው እጁን አጣጥፎ ተቀምጦ ይጠብቀናል ብለው ካሠቡ በእጅጉ ተሣስተዋል። በመሆኑም ለማንኛችንም የሚበጀው እኛ ኢትዮጵያውያን በጠቅላላ አንዳችን ለሌላችን ቀና መተሳሰቡ እንጂ፣ ፍጭው ፈንግጭው ከሆነ ዬትም አንደርስም። እንዲያውም ከኖረው መልካም ባህላችን ውስጥ የቀረንን አብሮ እና ተቻችሎ የመኖር መልካም ባህላችንን እንኳን ለማጣት እንገደዳለን። ስለሆነም ከዚህ ተነስተን «ወደፊት እንዴት እንጓዝ?» የሚለውን ጥያቄ አንስቶ በጋራ በሚደረስበት ውሣኔ የተሻለች ኢትዮጵያን በመገንባቱ ላይ ማተኮሩ ዐዋቂነት ብቻ ሣይሆን ብልኅነትም ነው። በየትኛውም መልኩ የትናንት ኢትዮጵያን ካነሣን፣ በዳዩ «ተበደልኩ» ባዩ፣ ወራሪውም «ተወረርኩ» የሚለው የኦሮሞው ልሂቅ መሆኑ ሊታወቅ ይገባል።

ሞረሽ ወገኔ በተለይ በአሁኑ ወቅት ራሱን በኢትዮጵያዊነት ጭንብል ውስጥ ሸፋፍኖ፣ ለጥፋቱ ሁሉ የሩቅ ተመልካች ሆኖ ለሚታዘበው የተማረው የዐማራ ተወላጅ የሚያስተላልፈው ግልፅ መልዕክት አለ፦ ወገናችን ከምድረ-ገፅ እየጠፋ ዝምታው እስከመቼ ነው? «ትውልድ ትውልድን ተክቶ ያልፋል፣ ታሪክም ይመዘገባል» ተብሏልና ዛሬ ለወገኖቻችን ካልደረስን ነገ እያንዳንዳችን የትውልድም፣ የታሪክም ተጠያቂ ከመሆን እንደማንድን መካድ አይቻልም። ስለዚህ በወገኖቻችን በዐማራው ነገድ ተወላጆች ላይ በትግሬ-ወያኔ እና በተባባሪዎቻቸው ላይ የሚደርሰው ሠቆቃ ከዚህ በላይ በዝምታ እና በቸልተኝነት ሊተው ከማይችልበት ምዕራፍ ላይ መድረሱን ተገንዝቦ ለወገን ጥሪ ተጨባጭ የተግባር ምላሽ መስጠት ያስፈልጋል።

ዐማራን ከፈፅሞ ጥፋት እንታደግ!

ፈለገ-አሥራት የትውልዳችን ቃልኪዳን ነው!

ኢትዮጵያ በታማኝ ልጆቿ መስዋዕትነት እና ትግል ለዘለዓለም ፀንታ ትኖራለች!

በዘመናዊት ኢትዮጵያ ታሪክ ወራሪው ማን ነው? ተወራሪዎቹስ? – ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት ( PDF)

 

ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት

42 Comments

  1. Finally Moresh has shown they started reading one of the many Oromo recorded histories; But sadly they chose to ready the wrong twisted way. Am sorry about that. Those Moresh guys are never happy until they see all Ethiopian people call themselves Amhara. Or forget about their identities. While respect for other nations is never found in their dictionary. The Habesha once again proved it is the voice of extrimist Amharas. Had the habesha been neutral Ethiopian, they couldnt have published this hateful and degrading article. And take heart, they only serve the amhara extrimists, not Ogadeni, or Oromo, or Sidama, or….. or any different extrimists from Ethiopia. Only amahara extrimists!!

    • @Bonni
      Instead of writting something crap, just show us how the above article is incorrect by bringing fact and logic.

      • You are bulshit. What kind of fact and logic do you need better than this?

        • @Walelign
          Cool down…why u become hot when you can’t to defend the article? Peanut head!!!

  2. We Oromian Aware of you any time. he can say what so ever but we never stop our goal because of him. any way thank you to make Alert OROMIAN PPL. we are stand bye to defend our OROMUMMAA !! OROMIA WILL BE FREE !!

    • morsh means anti oromo,tigray,sidama,somali…overall anti ethiopian.morsh amhara means ignorance,backwardness,famine.we learned from past time.no more ethiopia without oromos,tigres,southern nations,somali!thanks to the strugle of eprdf!

    • Thank you for this nice article. The true must be told!!! Only true set us free at the end!!!

    • naji,

      Please bring justification, or scholars critics than bla bla. Please your side is true. If OROMO were there even in the map ??? Please support your critics with evidence

  3. Moreh begins the work that gave the group instant notoriety (infamy) by saying: “We have understood the history of Ethiopia intellectually.” The group spends just a couple of pages rewriting Ethiopian history proving conclusively that such is not the case.
    When one makes a major claim, such as saying that the Oromos have invaded Amharas land, then one should be able to provide historical facts, sources, statistics, archeological evidences etc., to be able to back up one’s claim. Because without such evidence, the claim has no merit.
    It isn’t simply that Moreshs version of Ethiopian History turned out to be wrong in some of the particulars, but rather that they were so completely wrong that they will NEVER resolve the current regionalism mentality and the distractive seed that has been sawn by TPLF gangs. Moresh, however, unrepentantly continues to beat the drum of TPLF invented division as well as hostility between the two populace further in the name of protecting poor Amharas. How foolish, misguided and irresponsible Moresh is! My best advice or strategy? You better work on creating alliance and partnership between the Amharas and Oromos in order to eliminate minority TPLF instead of destabilizing them.
    One more point, according to close observants and my Gondere friends, the demography of Gondar is changing alarmingly to Tigre right now. Am I right? Not Oromos but Tigres are invading and dislocating indigenous Gonderes from their ancestorial land and homes by one or another means. Oroms are not the one who are in the verge of transferring part of Gonder to Sudan. TPLF (Tigres) are on the one tirelessly working hard of transfer part of Gondar to Sudan. Is not this so sad? Why not Moresh propagate to the sons of Theodros to show their heroism and secure such indigenous and historic land instead of diverting Amharas attention to a more complicated issue? My hope is that on its next history class Moresh will preach us how Amahas were the indigenous people in Sidamo, Ogaden, Borena or Wolaita.

  4. This is trash and far from the truth. Amhara is everywhere as per this useless essay before the “oromo came and removed them and others from Illu_Aba-Bora, Jima, Kelem Leqa etc” . Doro ye kotuun la-wurd bila ye bibituan talech”. This fabrication of lie will produce nothing, but will help the others to claim the entire Wollo where the millions of Oromo were Amaharanized by force in the name of Christianity.

  5. morsh means anti oromo,tigray,sidama,somali…overall anti ethiopian.morsh amhara means ignorance,backwardness,famine.we learned from past time.no more ethiopia without oromos,tigres,southern nations,somali!thanks to the strugle of eprdf!

  6. Moresh is revealing its true color from day to day. They should change their name to anti Oromo. If you observe clearly they write more about fabricated stories about Oromo than for the well being of amhara. I don’t really get what they aim to achieve. When people accuse minilik of doing atrocities, their defence is to immediately claim that the Oromos did the same thing(like breast cutting). This is a very racist organization which is anti Ethiopia. When I say Ethiopia I am not envisioning the same Ethiopia like Moresh Ethiopia(same language, same religion, same culture). I am talking about Ethiopia where people of all race, religion get the same value and respect and have all full rights. Today’s world has no place for racists like moresh.

  7. Thanks Moresh Wogene for posting this valuable document. You helped us a lot to know about the tricks of our colonialists through the cover of missionaries. You clearly stated nicely, if we want to discuss with modern Ethiopia, we need to start with the invasion of Giragn Mohamed. The stupid the so called elite of shabia, woyane & Oromo were trying to fabricate false history as to accomplished their colonialist agenda. One thing should be considered, the current move and plan of the Oromo extremists will never and ever happen in Ethiopia but they may loose what they get mistakenly instead. The other point is as our innocent fathers and mothers did, we need to accept the concept of living together in peace and love. Through war, trade, slave trade, religion and other reason, the current Ethiopian people are intermingled each other and this time, very difficult even to distinguish our people. For me, their is no pure Oromo, Amhara, Tigre, Gurage, Hadiya, Halaba…So, please the so called extremist elites come to your own thinking, how long are you vomiting the ideas of our Eropian enemies. Your evil thinking will heart and suffer your children and grand children. Ethiopia will stretches her hands into God.

  8. Telling the truth to those who have been bending on instigating violence between the two big tribe is a good listen, if they are willing to take it. We, Amharas, have taken more than enough suffering because of our ethnic background not only in Ethiopia but also in neighboring country like Kenya- a place where I am now living. Former Prime Minister of Kenya, Raila Odinga, said ” Ethnic is a biological accident’ when he spoke with BBC have you say special program presenter from Ghana in June 2009. we shouldn’t subjected to suffering because of our ethnic background.

  9. @Boonii and naji
    But they do not understand anything like animal. Woyane at this moment ride them,killed them, imprisoned them but they are talking about 100 yrs back. look the stupidity of them. Any ways this is the fact wether you some of ormo extrimists accept or not. you emigrated to Ethiopia and if you cant accpet our offer ,u better leave Ethiopia to somehere else. We need one Ethiopia, I am proud of Ethiopianism.ወደ ኢትዮጵያ መጣችሁባት እንጂ ኣልመጣችባችሁም። ልክ ማወቅ በጣም ይጠቅማል። OLF is killing him self for many years due to lack of critical thinker people with in and please take a lesson from your scrach and try to things differently. do not think like 4th centery moneky. Accept the fact and try to belive One Ethiopia

  10. Dear Boonii,

    It is correct to say we have to read all old and new documents and triangulate facts! I agree with you in that case. But are not believing the fact about the great massive migration of oromo people to its current place in the some 500 years ago? I know several young people who are very much astonished with the bad dids of minilik but never regrate about what happened during oromo migration. Sew call it werera (invasion) i rather call it were (migration) but remain to be corrected. As some call minilik’s movement expansion, and some call invasion—for me it is not these words which matter, but to accept the full history of our country. It is unfair to promote recent facts while denouncing the old. History is history. nothing less and nothing more! Let us accept all our ethnic groups (mainly oromo, amhara and tigre) has caused massive mistakes, but also massive goods, and let us join and build on the good once! Otherwise, we have few options, but looming bloodshed right in front of us.

  11. Thank you Moresh.

    You have armed us with historical facts. It is a wake up call to all Amharas. This is the true history written without any fabrication. The OALFites are merely fabricating false history about themselves and the Amhara. If they want to write their history why they do start from the end of the 19th Century, where Emperor Menelik II started reunifying Ethiopia, which was destabilised by the invasion of Mohamed Ibn Ibrahim Al Gazi (Mohamed Gragn) and the Oromo?

    You Oromos, your forefathers invaded Ethiopia by massacring the inhabitants in Ethiopia. They forced the inhabitants to change their tribe through their Mogassa tradition. The inhabitants of Fatagar now Arsi), Sodo, Damot Enrea, Bizamo, Gafat, Wollo, etc, changed their tribe by coercion and that is the secret behind the explosion of the population of the Oromo people. Those who refused to change their tribe into Oromo were annihilated. Bothe the annihilation of a tribe and forcing them to change their tribe is a pure act of genocide.

    And this act of barbarism and genocide is still being committed by their grand children to this minute. Unfortunately it them who clamour that the Amhara has committed genocide against them, what a white lie!

    We the Amharas believe, even though you are invaders and committed untold atrocities against the rest of Ethiopians, especially the Amhars, , you are Ethiopians and let us live together. If you do not accept our heartfelt call and chose to pursue your act of genocide, well go ahead, we are waiting for you!

  12. We have heard about this Moresh’s anecdote thousand times. It won’t change the facts on the ground. How come Moresh forgot to mention that the Abyssinians(Amhara & Tigray) migrated to Africa from Yemen. You claim that you are NOT African. I was just laughing when Moresh id trying to put Amharas in all regions…..kkkkk….they forgot to include the Ogaden and the rest of the Southern part. Wushet bedegagem ewnet lihon ayechelem Ato Tekle Beshawu…yeleqis Amarignawotin beyashashelu yeqelal, hulum sewu endegebawu.

  13. Mosresh Wogene chair man, Tekle Yeshaw copying old history and try to threaten Oromo and its freedom like his ancestor did century years back. When all people of Ethiopia are trying to narrow their differences and aiming at the core enemy, which is Woyane, Mr. Tekle is flaming the condition by digging old history and try to spoil the relation among the the Whole Ethiopian people. Mr. Tekle crossed the red line when he officially insult the Oromo people many time giving interviews about Oromo people. I will come up with full piece of note next time about you in detail and how you should stop insulting Oromo people. For a while do not mess with us.

  14. Trash guy with big glasses. Is there no rich MORESH member that can change that ugly glasses of Debtera Tekele Yeshaw that he can read not only church and war lord wanna be kings story, but more world history written about Kush Ethiopia and Oromia?

    If there is any logic in this fool guy garbage, he would know how 40 million people exist in one place of the horn of Africa, with one language and under one system of GADA. Did Oromo came by airplane, cruise ship etc. Anyhow we know the IQ of these people, it is rat thing, I mean rat mind.

  15. THANK YOU MORESH WOGENE

    It is a Wake up Call to all Amharas The is the true histore written without ony
    fabreication

  16. Thank you moresh wogene

    it is a Wake up Call to all Amaharas the is the true history written witheaut an fabrication

  17. The truth bites.this story is not witten by Tesfaye Gebreab,it is written by European and Arab explorers,what are you liers barking about,prove that article wrong based on facts.other wise,just swallow it.stop dirty mouthing.talking about.you Oromo extremists led by that merecenary Jawar are mothers of hate.look you history which is well documented on international arena,you guys massacred thousands of innocent and defenseless Amaras in a very barbaric way since your masters Woyanes rule our country.you can not bring a single incident Amara perpetrated or comite crime on others.you guys are hate mongerers,you talk about murder and distraction all the time.how un civilized and back ward is that.

  18. Look the way those hate full Oromos are reacting,it is amazing,look how much venom they are carrying in side them.they live in the Stone Age erra.very sad.

  19. ሰላም የተከበራችሁ አስተያየት ሰጭዎች የሁላችሁንም አስተያያት በጥሞና አንብቤዋለሁ በተቃውሞው ጎራ የተሰለፋችሁት ወገኖቼ በጣም የምታሳዝኑ ናችሁ ሐቅ ወይም እውነት የማይዋጥላችሁ። የሞረሽ ወገኔ ሊቀመንበር አቶ ተክሌ ያሻው እድሜ ልኩን እውነትን እንደተናገረ ከዚህ የደረሰ «ብርቅ ኢትዮጵያዊ» ነው። ቃሉንም ተቀብለን እንድትማሩ የምንችለውን እንጥራለን በህወሃት አሽከርነታችሁ ለመቀጠል ከመረጣችሁ ደግሞ «መንገዱን ጨርቅ ያድርግላችሁ» ደረ-ገጹንም ከሳችኋል በጣም አልቀበጣችሁም እንዴ? አድብ ግዙ! የህወሃትን እድሜ እንዲረዝም ለማድረግ የምታደናቅፉን እናንተው ናችሁና በሀገርና ———–ዋዛ የለም።

  20. Thank u moresh for revealing thier true color if they don’t want peace we can be like them we can not tolerate thier hate towards us any more it is to much if they don’t want to live peacefully we have to show them who we are.The last 40 years they have been dancing on us with out shame now we have to engage them.

  21. Thank you again Moresh Wegene for bringing up to the surface the fact that those so called ‘’ fake intellects’’ have been trying to cover!!! Now some idiots becoming hot reading of this article and writing full of insult. You are showing us how your peanut head can’t produce more than what you are doing now. Your emotion and fictions will not take you anywhere!!! Use your mind!

  22. kkkkkkkkkkk Ato Shawel, except Oromo and Tigre and Ogadenia, everybody was their, What a racist person you are? Then where can you send us now? Show we ask you for a visa where you hide somewhere in Europe?

    Ant batmar yeshal neber, you better be a farmers Mr. Tekele.

  23. Thank you moresh.
    This article should have been published long time ago.
    this teaches the younger generation how to look Ethiopian history beyond the 100 year tag.The oromo elites stuck with100 year history, because if they go beyond that history tells the fact that most central Ethiopia including present day addis abeba was inhabited by amharas and the likes.
    The fact that weyanes keep repeating the same thing to keep the balance of power.
    Dr Tecola Hagos was saying the thing in another article even if it is not as elaborate as this one.
    pls invite other historians to say something in our shared history.the younger ones need to know.

  24. May I ask what the purpose of this article is?
    Are you asking the Amharas to wage a war against the Oromos? I dont the double standard these bunch of “Moresh” foLks are playing. They are trying to achieve two conflicting objectives at the same time.

    in one hand they claim Minilik unified Ethiopia blah blah and the unity of of the country is not up for discussion (fair enough). in the other hand they claim they were victims of agression and they will defend what is theirs by removing the Oromos who they claim to originate from Madagascar.
    I am puzzled with waht their real objective is. When you declare a war on others, dont expect the other party to wait for you with roses. You guys are adding to fuel to the existing tension instead of extinguishing it.

    I am just venting and I know none of them will dare to answer my questions. I am a proud Oromo and have down to earth and good Amhara friends. We never had issues living together.

    If our elites are not able to bring a solution to the problems they themselves have created (referring to elites from both sides), they would rather shut up and leave us alone. Dont use us as your scapegoats to quench your thirst of power and money.

    enough said…

  25. one more thing to those of you writing derogatory comments here, please do yourself favor by going to school and educate yourself on how to co-exist with all your differences in the 21st century. I am referring to bothe side of the aisle here.
    Hatered has never been a solution to any of our problems and will never be. If you claim to be civilized (what most of you claim here) please act like one.

  26. hi

    Most of our problems in Ethiopia can be solved if we try to understand why some people with different views from ours about the country behave. Let us put ourselves in another persons shoes and try to understand what Ethiopia really means to each one of us and try to work a solution together. An amhara person doesn’t fully understand what it is like to be an Oromo in Ethiopia. If this amhara person is born an Oromo will he really be satisfied with the current version of his Ethiopiawinet? I highly doubt it. The same thing goes around and for other citizens of the country as well.

    We as Ethiopians don’t have a culture of openness even within our family. We don’t really know one another and we are biased and rarely rely on facts. As citizens of the same country we must start to know each other and give value to one another. We are going no where as long as we focus on opposing each other and finding faults. When we think of Ethiopia we should think about all her citizens.
    When a person from my group insults people from another group if I defend this person just because he belongs to my group, where is my love and respect for my country? My loyalty is really to my group even if I try to sugar code it in the name of Ethiopia.
    Every body has different version of Ethiopia. If we want to create a common version of the country and national sentiment different groups should respect each other, sit down, debate, compromise and then create a common Ethiopia which is inclusive and be really loved and cherished by all its citizens. Opposing someones views all the time is very easy and bears no fruit. It has no use even for the group we belong to let alone for diverse Ethiopia

  27. according to the article amhara was living everywhere. when I read these kind of texts i am now really suspecting that even the “aba bahrey” might be a fictional conspiracy. How would Oromo language be more than 75% or more similar to Sidama, Hadiya, Konso etc when the Oromo people are strangers to the area. Why wouldn’t amharic has no relation with the languages of the south if (as the writiter of this article) amhara has been living indeginously in all the mentioned areas.

  28. Most of the notion in the statement is taken from the april 2012 article published
    by Ethiopian Review and written by Telahun Ashenafe under the title “Who is Amhara”. Even the wording at the beginning and in most of the sentences and
    concluding remarks are what Mr. or Dr. T.Ashenafe pointed out. Moresh added
    a new concept regarding how the name Oromo and Oromia came about, and I
    would like to commend Moresh for explaining clearly the misguided OLF story.
    However, there is another outlook about how OLF and its intellectuals created
    it from. In Latin, Spanish and Italian “Oro” means Gold and “Mia” means Mine.
    “mo” is an expressive word even in English means “Plenty or More,etc.”
    Therefore, “Oromo means My Gold” and “Oromo means Plenty of Gold,etc.”
    OLF simply borrowed it from European Languages. What a shame attempting
    to make the black population group “White” and “European not African”. What
    more lies can we take from this extremist, anti Ethiopian, anti African group
    that created an artificial and baseless story? the answer is nothing. Moresh
    needs to continue exposing more lies OLF is spreading in order to discredit
    it.

  29. kkk this man dont know that we sidama peopel and oromo afar hadiya somali agewi saho kimati etc are cushtic people we are the people who mention on the bible are you telling us that oromo came from some where kkkkkk that is funy

  30. Ethiopian medias should disseminate such narratives as they do about the Nefetegna system.

  31. BRAVO MORESH for finally speaking the truth about the invasion of Oromos and their GENOCIDAL history they committed on the people of ENARYA, DAMOT and GAFAT and this history is not written by AMHARAS it is rather written by foreigners like ABA BAHRAIN, ALVAREZ etc …

    OLFites would go crazy and mad reading their true history of GENOCIDE and origin and as they always believe repeating FALSE would be true and they now believe their false and fictions history kkkkkk

    Oromos have no any historical or material evidence to prove their existence before the 16 century however the now extinct people due to the GENOCIDE of OROMOS such as ENARYA, DAMOT, GAFAT, DAWRO and AMHARAS were their and their existence was even written by these foreign historians

    Oromo invaders killed hundreds of thousands of AMHARAS and if one has to demand an apology they are the one who should ask an apology for the GENOCIDE THEY COMMITTED ON AMAHRAS and other Ethiopians who were completely annihilated by their barbaric invasion and assimilation

    If there is an issue of land or territory we AMHARAS also have a right to reclaim our land forcefully taken by OROMO INVADERS 400 years ago and we have a right to reclaim our land like JEWISH people they claimed their land after 1000 years and we AMAHRAS can also claim our land like ISRALELITES the land forcefully taken by OROMO INVADERS 400 YEARS AGO and THAT IS OUR RIGHT and AMHARA PEOPLE SILENCE IS NOT OUT OF FEAR It was for the seek of peaceful coexistence if OLF OROMOS could not understand this we are brave people who knows how to fight

  32. OLF OROMOS the usual tactic calling MORESH as anti Oromo will not work this time, you have been irritating and insulting anyone who dares to tell you your barbaric invasion claims the lives of millions of Ethiopians to forcefully occupy the present day of OROMIYA 400 years ago ….

    whenever you hear your true history you cry oh this is written by AMAHRA DEBTERAS kkkkk now MORESH show you HISTORICAL FACTS WRITTEN BY FOREIGN HISTORIANS you poisonous OLF OROMOS can not do anything except crying the old song DEBTERA bla bla call FRANCISCO ALVAREZ debtera kkkk

    if OLF Oromos can not live in the land they forcefully occupy after killing Hundreds of thousands of Amharas and committed Genocide on the people of ENARYA, DAMOT, and GAFAT, Amhara people will reclaim their land and Amhara people are fade up of being a punch bug for OLF Hate preachers and we are ready to defend our to reclaim our land and we Amahras know how to fight…we are not like OLF Oromos who surrendered 40,000 soldiers and we are not like OLF Oromos who can not even liberate one Mountain after 50 years of struggle

Comments are closed.

Previous Story

ፕሮፌሰር መስፍን ለሰማያዊ ፓርቲ እራት ግብዣ የ20 ሰው ትኬቶችን እንደገዙ የፌስ ቡክ ጉዋደኞቼ ጽፈው አነበብኩ

Next Story

“በቅሎ አባትህ ማነው ቢሉት ፈረስ አጎቴ ነው አለ” የኢህአዴግ የሃያ ሶስት ዓመት ጉዞ – ከሙሼ ሰሙ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop