May 11, 2014
1 min read

የሚኒሶታው ደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ ምርጫ ተጠናቀቀ

በርከት ያላችሁ የዘ-ሐበሻ አንባቢያን ዛሬ በጉጉት እየተጠበቀ ያለውን የሚኒሶታውን ደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ ቀጣይ ሁኔታን የሚወስነውን ምርጫ በተመለከተ ‘ውጤቱ ምን ሆነ?’ ስትሉ በስልክ፣ በኢሜል እና በተለያዩ መገናኛ ዘዴዎች በጠየቃችሁን መሠረት የቤተክርስቲያኑ አሁን ያለበት ሁኔታን እነሆ።

በፍርድ ቤት በታዘዘው መሠረት ወደ ሃገር ቤቱ ሲኖዶስ እንጠቃለል የሚለውም፤ እንደነበርነው በገለልተኛነት እንቆይ የሚለውም ወገን በድምጽ ብልጫ የቤተክርቲያኑን ሁኔታ ለመወሰን ድምጽ ሲሰጡ ውለዋል። ወደ 5 ፒኤም አካባቢም የድምጽ መስጠቱ ሂደት ተጠናቋል። የፍርድ ቤት ዳኛና ከሁለቱም ወገኖች የተወከሉ ሰዎች ባሉበት የድምጽ ቆጠራው እየተካሄደ ነው።

የድምጽ ቆጠራው ውጤት ዛሬ ማምሻውን ይለቀቅ፤ አይለቀቅ ዘ-ሐበሻ ያወቀችው ነገር ባይኖርም ውጤቱን እንደሰማን ለአንባቢዎቻችን እናቀርባለን።

በምርጫው ውስጥ ከተሳተፉ ወገኖች ለማረጋገጥ እንደቻልነው በሁለቱም ወገኖች የቆሙ ካህናት በየተቃራኒው ወገን ተቃውሞ ሲሰማባቸው ነበር።

30170
Previous Story

የዞን ዘጠኝና የታሳሪ ጋዜጠኞች ጠበቃ አቶ አምሃ ለቢቢኤን ራድዮ ተናገሩ

Next Story

ዓባይ እንደዋዛ–“ኢትዮጵያ ሃገሬ ናት፤ ዜግነቴ ኢትዮጵያዊ ነው” ክፍል ሶስት (ከአክሎግ ቢራራ (ዶ/ር)

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop