ታኅሣሥ 09/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ዩኒቨርስቲው የ60ኛ ዓመት ክብረ በዓሉን ሲያከብር ሕዝቡ ተቋሙን ለመደገፍ ትብበር ሊያደርግ እንደሚገባ ያስተላለፈውን መልዕክት ምክንያት በማድረግ የተለያዩ ማኅበረሰብ ክፍሎች ድጋፋቸውን እያበረከቱለት ነው። ከደጋፊዎቹ መካከል ደግሞ ወይዘሮ አፀደወይን በቀለ እና ቤተሰቦቻቸውቀዳሚዎቹ ናቸው።
በባሕር ዳር ከተማ ተወልደው ያደጉት ወይዘሮ አፀደወይን በቀለ በባሕር ዳር ከተማ የሚገኘውን እና ከእናታቸው ወይዘሮ ዝማምነሽ ወልደየሱስ በውርስ ያገኙትን ከ500 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመተውን ዙማምነሽ ታወር ለባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ በስጦታ አበርክተዋል ፡፡![411728922 748999930591267 8151955860955221168 n 411728922 748999930591267 8151955860955221168 n]()
ስጦታውን ለመስጠት ያነሳሳቸውም ባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ በጤናው ዘርፍ የሚሰጠውን አገልግሎት ለመደገፍ መኾኑን የወይዘሮ አፀደወይን ቤተሰቦች ተናግረዋል፡፡
![411921383 748999790591281 3280424816043634075 n 411921383 748999790591281 3280424816043634075 n]()
ስጦታውን የተረከቡት የባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት ፍሬው ተገኝ (ዶ.ር) ዩኒቨርስቲው ትልቅ ኀላፊነት እንዳለበት በመገንዘብ ነው ብለዋል።
ማኅበረሰቡ ያለውን ሃብት ለሕዝብ አገልግሎት ለሚሰጡ ተቋማት በማካፈል ተቋማት ሠፊ አገልግሎት እንዲሰጡ መደገፍ እንዳለበትም አሳስበዋል፡፡
![412291422 748999877257939 5302835896694733709 n 412291422 748999877257939 5302835896694733709 n]()
ከወይዘሮ አፀደወይን ቤተሰብ ትምህርት በመውሰድ ሁሉም ትብብሩን አጠንክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ፍሬው ተገኝ ጠቅሰዋል።
![412293933 748999800591280 7207302865882463409 n 412293933 748999800591280 7207302865882463409 n]()
የባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ የተሰጠውን የሕንጻ ስጦታ ለማኅበረሰብ አገልግሎት እንዲሰጥ በማሰብ የእናቶች እና ሕጻናት የሕክምና ማዕከል እንደሚኾን ገልጸዋልዋል።
ዘጋቢ:- ራሄል ደምሰው
አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን