ከካህኑና ከሌዋዊው ደጉ ሳምራዊ የሰብአዊነት መገለጫ ሆነ፣ 

ከደረጀ ተፈራ፣

እንደሚታወቀው የአማራ ህዝብ ከግማሽ ክ/ዘ በላይ በኦነግ፣ በህወሃት፣ በኢህአዴግ አሁን ደግሞ በብልፅግና መንግስት ተቆጥሮ የማያልቅ መከራና በደል ደርሶበታል። ሽመልስ አብዲሳ ሰበርነው ያለውን የአማራ ህዝብ ኦነግ ሸኔ እያሳደደ ይገድላል፣ የሃገሪቱ የስልጣን መንበር ላይ የሚገኘው ጠ/ሚ አብይ አህመድ እንደ መንግስት ህዝቡን ከጥቃት ከመከላከል ይልቅ በአማራ መቃብር ላይ ዛፍ እንተክላለን እያለ ያላግጣል። ከአራት ኪሎ እስከ ጫካ ድረስ እየተናበቡ የአማራን ህዝብ ከምድረ ገፅ ለማጥፋት እየተረባረቡ ይገኛሉ።

አብይ አህመድ በአማራ ህዝብ ላይ ያለው ጥላቻ ካሳዳጊው ከመለስ ዜናዊ ቢበልጥ እንጂ አያንስም። አማራ እንዳይደራጅ አድርጎ፣ መሪዎቹን ገድሎ፣ አሸባሪውን ኦነግ በለውጥ ስም ከአስመራ ወደ ሃገር ውስጥ አስገብቶ፣ ባንክና የመሳሪያ መጋዘን ዘርፎ እንዲደራጅ በማመቻቸት ላለፉት አምስት አመታት በአማራ ህዝብ ላይ የዘር ፍጅት እንዲፈጸም አድርጓል።
የወያኔን እና የኦነግን የጥላቻ ትርክት እንደ ዳዊት ሲደግም ያደገው አብይ አህመድ ባለፉት የስልጣን ዘመኑ በአማራ ህዝብ ላይ ባዘነበው የበቀል በትር መርካት ባለመቻሉ፣ መንግስቱ ኃ/ማርያም ንጉሱን ገድሎ ቢሮው ውስጥ አስቆፍሮ እንደቀበራቸው፣ አብይም በተራው በኦነግ ሸኔና በኦሮሚያ መንግስት የተጨፈጨፉ አማራዎችን መቃብራቸው ላይ ዛፍ እንተክላለን በማለት ለአማራ ህዝብ ምንም ዓይነት ርህራሄ የሌለው ክፉ በቀለኛ መሆኑን በአንደበቱ ተናግሯል፣ እርካብና መንበር ብሎ በፃፈው መፅሃፍም እንዴት ጠላቴ ብሎ የፈረጀውን ሰው እንደሚታጠቃ ጽፏል።

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የደግነት እና የሰብአዊነት ምሳሌ ተደርጎ  የተገለፀ የአንድ የሳምራዊ ሰው ታሪክ በሉቃ 10፥ ከ25 – 37 ላይ ተጽፎ እናገኛል። በአንድ ወቅት አንድ ሳምራዊ ሰዉ ከኢየሩሳሌም ወደ ኢያሪኮ  ሲጓዝ በመንገድ ላይ ወንበዴዎች አገኝተውት ገንዘቡን ዘረፉት፤ ልብሱንም ገፈፉት፣ በህይወት እና በሞት መሃል ደብድበዉ በሜዳ ላይ ጥለውት ሄዱ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ብልፅግና ሆይ ራስህን ከሰቀልክበት ጉም በጊዜ አውርድ፣ ነገ ሌላ ቀን ነውና!! [መስፍን ማሞ ተሰማ] 

በዚያ መንገድ አንድ ካህን ሲሔድ የወደቀውን ሰው ቢያየውም፤ ምንም ሳይረዳዉ አልፎት ሔደ፡፡ ከካህኑ ቀጥሎም አንድ ከሌዊ ወገን የሆነ ሰው በዚያ መንገድ ሲጓዝ በወንበዴዎች ተደብድቦ የወደቀዉን ሰዉ ቢያየውም እርሱም ሳይረዳዉ ዝም ብሎ ጥሎት ሄደ።

ነገር ግን አንድ ሳምራዊ በዚያች መንገድ ሲያልፍ፤ አይቶም አዘነለት፤ ልቡም ስለራራ በሰብአዊነት የቆሰለውን ሰው ቁስል ጠራርጎ፣ ቁስሉም እንዲያደርቅለት ወይን አደረገለት፤ እንዲያለሰልስለትም ዘይት አፈሰሰለት፡፡ ሩህሩህ ሰው በዚህም ሳያበቃ ቁስለኛውን ደግፎ እንግዳ ማረፊያ ቤት ከፍሎ አስቀመጠው። የቤቱ አከራይንም በመጥራት ወጪህን ሁሉ እከፍልሃለሁ ይህንን ሰው አስታምልኝ በማለት የተደበደበውን ሰው አደራ ሰጥቶ ወደ ሌላ ስፍራ ሄደ፡፡

እንግዲህ እግዚአብሔርን አመልካለሁ፣ አገለግላለሁ ከሚለው ከካህኑ እና ህግ አውቃለሁ ከሚለው ከሌዋዊዉ  ይልቅ እምነቱን በምግባር ያሳየ፣ ሰብአዊነት የተሰማው፣ በወንበዴዎች ተደብድቦ ለወደቀዉ ምስኪን ሰው የደረሰለት ደጉ የሰብአዊነት ምሳሌ የሆነው ሳምራዊው መንገደኛ ነው።

ስለዚህ በዘመናችን በአማራ ህዝብ ላይ የሚፈፀም፣ እንግልት፣ በደል፣ ወረራ፣ ግድያ፣ ዝርፊያ፣ ከተማ ማውደም፣ ህዝብን ማፈናቀል፣ የዘር ማፅዳት እና ጭፍጨፋ ባጠቃላይ በሰብአዊ ፍጡር ላይ የሚፈፀምን ወንጀል አይቶና ሰምቶ የማይቆረቆር፣ በአማራ ህዝብ ላይ እየተፈፀመ የሚገኝ አረማዊ ድርጊትን አቃሎ የሚመለከት፣ የሚያድበሰብስ፣ በራስ ላይ ወይም በቅርብ ቤተሰቡ ላይ ሊፈፀም የማይፈልገውን አስነዋሪና ጨካኝ ኢሰብአዊ ድርጊት ሲፈፀም እያየና እየሰማ በምንቸገረኝነት ወይም በሌላ ምክንያት በግፉአን ሞትና መከራን አንዳላየ የሚሆን ወይም የሚያላግጥና የሚያቃልል ቅድም ሆነ ሼክ ወይም የትኛውም ዜጋ ሁሉ ከዚህ በላይ የተገለፀው የካህኑና የሌዋዊው ምሳሌ ለእነሱም የተነገረ መሆኑ መረዳት ይገባዋል።

በውዳሴ ከንቱ ተሸንፋችሁ አረመኔ ገዢዎችን ለማስደሰት ወይም ለማባበል ስትሉ የተገፋውን እና የተበደለው የአማራ ህዝብ እንደ መስዋዕት በግ ማቅረብ የምትፈልጉ፣ በግል ጥቅምና ክብር ለተሸነፋችሁ ከንቱዎች ይህ መልዕክት ይድረድልኝ።

ግንበኞች የናቁት ድንጋይ እርሱ የማዕዘን ራስ ሆነ፤ እንደተባለው ታንክ፣ መድፍ እና ድሮን ከታጠቁ የአረመኔው የአብይ መንግሥት ወታደሮች ይልቅ የማዕዘን ራስ የሆኑት ለተገፋ ህዝባቸው የቆሙት የአማራ ፋኖዎች ናቸው። የህዝቡ መከታ ከሆነው ፋኖ ከሚባል የማዕዘን ድንጋይ ጋር የሚጋጩ ሁሉ ይቀጠቀጣል።
ድል ለፋኖ!
ድል ለተገፋው የአማራ ህዝብ!
ከደረጀ ተፈራ

5 Comments

  1. ሀ) የሃይማኖት ተቋማት የእረኝነት ሳይሆን የለየለት ምንደኝነት ሰለባ ከሆኑ ዓመታት ተቆጠሩ!

    ለ) እንዲህ አይነት ከጨካኝ (ከገዳይና አስገዳይ) የፖለቲካ ሥርዓት ካድሬዎች (ባለሥልጣናት) መካከል ተቀምጦ እና ከእነርሱ ባልተናነሰ ግልብና አደገኛ ስሜት እየተናጠ አገር ማለት ሰው እንዳልሆነ ሁሉ የገዳዮችን የጦር ሃይል ተዳፈራችሁ በሚል እረኛው ነኝ የሚለውን ህዝብ የሚያጎሳቁል አባት ተብየ አኳኋን የሚነግረን የገጠመንና እየገጠመን ያለውን ውድቀት አስከፊነት ነው!

    ሐ) እነዚህን አይነቶች አሳፋሪና ወራዳ አባቶች ተብየወች ከቻሉ ንፅሃ ገብተው ይቅርታ እንዲጠይቁ ካልሆን ግን የጨበጡትን መስቀል አርክሰውታልና ቢያንስ ባለመሳለም እውነተኛ አማኝነትን ማሳየት የግድ ነው!

    ሐ) አዎ! የአድርባይነት ክፉ ልክፍትን/ሰብእናን በሃይማኖታዊ አልባስ እና በንዋየ ቅድሳት ሸፍኖ (ተኩላነትን በበግ ለምድ ለብዶ/ሸፍኖ) መከረኛውን ህዝብ የማታለሉን አስቀያሚ ሰብእና ፈፅሞ ማስቀረት ባይቻልም ከቁጥጥር ውጭ ሆኖ በቋፍ ላይ ያለውን ትውልድ ጨርሶ ከማበላሸቱ በፊት መገታት አለበት!!

  2. From Zemedkun’s telegram page

    “…ብፁዕ አቡነ ኤርሚያስንም ሆነ ቅዱስ ሲኖዶሱን ያጠፉ ሲመስለን፣ የመጠየቅ፣ የመተቸት፣ የመጨቃጨቅ፣ የመሟገት መብት አለን። አባት ከልጁ ጋር እንደሚጨቃጨቅ ማለት ነው። ከዚያ በዘለለ ግን የጳጳስን ስብዕና አውርዶ፣ ፈጥፍጦ፣ እያዋረደ፣ በካርቶን ሥዕል፣ መስቀሉን እንደያዙ ዘቅዝቆ መስደብ ዐማራዊም፣ ኦርቶዶክሳዊም ጠባይ አይደለም።

    የዐማራ ከፍታው የታወቀ ነው። ሞራሉ፣ ስብዕናው ሁሉ እጅግ ከፍ ያለ ነው። እናም ከወረዱት ጋር አንወርድም። ያውም የዋቀ ጉራቻ የኦነግ አክቲቪስቶችን መንገድ ተከትሎም አይሄድም። ጠይቁ፣ ውቀሱ፣ ጻፉ፣ ተቹ፣ ማብራሪያም ስጡ ነገር ግን ብፁዕ አቡነ እገሌ፣ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ እገሌ ብሎ ከነማዕረጋቸው ነው መጠየቅ። እንጂ እንደ አግድም አደግ ክፍት አፍ መሆን ተገቢም፣ ልክም አይደለም። በብፁዕ አቡነ ኤርሚያስ ላይ ያለን የአባትና የልጅ ጥያቄ፣ ሙግት ይቀጥላል። መብታችንም ነው።

    ብፁዕነታቸውን የምንሞግተው ብአዴን ብልጽግና ቆራርጦ በለጠፈው ቪድዮም አይደለም። ሀገረ ስብከቱ የለጠፈውንም አይተናል። ለምን ማለት መብታችን ነው። ክፍት አፍ የኦሮሙማ ካድሬ ግን አይመለከትህም። አንት መናፍቅ አዛኝ ቅቤ አንጓች።”

  3. ሳልወድ በግድ ምክንያቱም ጥፋት ሲፈፀም ዝም ማለት ከአጥፊው ጋር መሰለፍ ስለሚሆን ዛሬም የሚከተለውን ለማለት ብቅ ብያለሁ::
    እኔም ሆንኩ ሌሎቹ የእምነት አባቶች በተደጋጋሚ የሚፈፅሙትን ስህተት ከመቃወምና ከመጠቆም አልቦዘኑም:: ባለፈው ጊዜ በዚሁ ድረገፅላይ በውጭአገር ቤተክርስቲያንና ገዳም በመገንባት ዙሪያ የሚታዬውን አላስፈላጊ እሩጫና ውድድር ቲጂ (ለእምነታቸው ያለፍርሃት መቆማቸውን ለማሳዬት ሲሉ ሙሉ ስማቸውን ቢገልፁት ይመረጥ ነበር) የሰጡትን አስተያዬት ተከትዬ እኔም ሰጥቼ እንደነበር መለስ ብሎ ማዬት ይቻላል ::በዛሬውም በዚያው በእምነት አባቶች ዙሪያ በሚታዬው ድክመት ላይ አስተያዬት ለመስጠት ተመልሰን መጥተናል::በእኔ በኩል ሃሳብ ልሰነዝርበት የምሻው ነጥብ የሲኖዶስ ጉባኤ በአገራዊ ጉዳይ ላይ ተወያይቶ ያሳለፈውን ውሳኔና መግለጫ የሚመለከት ይሆናል ::በብፁእ ፓትርያርኩ በተነበበው ዝርዝር መልእክት ቤተክህነት በአገራችን የሚታዬውን የፖለቲካ የኤኮኖሚና የማህበረሰብአዊ ውድቀትና ድቀት በዝርዝር በማስቀመጥ የጥፋቱ ባለቤት ማን እንደሆነ በመሸፋፈን ብሎም ፍትህን ቦታና ድርሻ በመንፈግ በሚመስል መልኩ አጥቂና ተጠቂ ተሳስመው ሁሉም ነገር በይቅርታ እንዲቋጭ በሚል መልእክት መዝጋታቸውን ስመለከት አላስችሎኝ ብሎ ብእሬን አነሳሁ:: በጣም የሚገርመው ደግሞ ከመፅሃፍ ቅዱስም ምዕራፍና ቁጥር እዬጠቃቀሱ ምክንያታዊ ማድረጋቸው ነው::የክርስቶስም ትምህርት ዋናው ይቅርታና ይቅርባይነት ነው የሚለውን ትምህርት ካለቦታው ሰንቅረው ለማሳመን ሞክረዋል::እርግጥ ነው ይቅርታን የሚጠላ የለም ግን የጥፋቱ ልክና መጠን መታዬት አለበት::የቃላት እላፊና ህይወትን ማጥፋት እኩል አይታይም::ህዝብንና አገርን ለማጥፋት የተነሳ ጨካኝ ሰላምን የማያውቅ በስልጣን ላይ የተቀመጠ ቡድን ምንም ወንጀል ሳይሰራና ሳይበድል የተጨፈጨፈን ንብረቱ የወደመን የተፈናቀለን ህዝብ ከተበዳዩ ጋር እኩል በእርቅ ወንበር ላይ ይቀመጥ ብሎ ማስተማር ለህዝቡ ሳይሆን ለወንጀለኛው ለድጋሚ ጥፋት ዕድሜና ዕድል መስጠት ይሆናል:: እባብን አሸዋ አልብሰን ለጊዜው ያግኝ እንደማለትም ይሆናል::ምንም ያህል ክርስቶስ ይቅርታን ቢያስተምርም ከሰይጣን ጋር ይቅር ተባብሎ አልታረቀም::በተመሳሳይም በአገራችንና በህዝባችን ላይ መጠነ ሰፊ ወንጀል የሰራ ስርዓትና ተከታዮቹ ምድራዊ ፍርድ ይሰጣቸው ይባላል እንጂ አይድገማችሁ ተብለው በስልጣናቸው ላይ እንዲቆዩ ወይም በነፃነት እንዲንቀሳቀሱ አይደረግም:: ሰላም ከደፈረሰ አገርና ህዝብ መከራ ውስጥ አስርታት ዓመታት አልፏል ::ታዲያ አሁን ላይ የሰላም ካርታ ለምን ተመዘዘ? ምክንያቱ ግልፅ
    ነው ::ያም ህዝቡ መሮት ስርዓቱን ከጫንቃው ላይ ለማውረድ ቆርጦ በመነሳቱ ነው::ያንን ህዝባዊ የለውጥ ማእበል ተረባርቦ ለማክሰም አንዱ መንገድ በእምነት አባቶች በኩል ዘመቻ ማድረግ ነው::ይህ በእግዚአብሄርም ዘንድ ፍርደገምድልነት ነው::
    የሲኖዶሱ ጉባኤ መግለጫ ለዘላቂ ሰላም የሚያበቃ ሳይሆን ፍትህና ርትህ ተጥሰው ወንጀለኞች በያዙት የስልጣን ቦታና በሰሩት ስራ ኮርተው እንዲኖሩ የሚያበረታታ ወገንተኛ የሆነ ውሳኔና የህዝብን የፍትሃዊ ትግልን ትጥቅ የሚያስፈታ ጥሪ ነው::ሌላው ቀርቶ ቤተክህነቷ ለደረሰባት በደል ወንጀለኛውን አካል ተጠያቂ ለማድረግ አልደፈረችም::በአጠቃላይ ሲታይ በሰላም ስም ስርአቱን የማዳን የሚደረግ በተደጋግሞ እንድተገለፀው የማደንዘዥያ ተልእኮ ነው::ዳዊት ጎልያድን በእርቅና ድርድር ሳይሆን በጥበበኛ የትግል ዘዴ ነው ያሸነፈው ::የኢትዮዽያም ህዝብ በጀመረው ትግል እራሱንና አገሩን ያድናል::እምነቱንም ከአስመሳይ የእምነት አባቶች ነፃ ያደርጋል ::
    ጎሰኝነት የሰይጣን ስራና እምነት ነው::ጎሰኝነትን መቃወም መታገልና ማሶገድም የመልካም ተጋድሎና የፀረ ሰይጣናውያን ተግባርና ግዴታ ነው::እንደሲኖዶሱ አቋም ከሆነማ አቡነዼጥሮስም ከጣልያኖች ጋር መደራደርና በሰላም አገራቸውንና እምነታቸውን አሳልፈው መስጠት ነበረባቸው ማለት ነው::ያንንም ባለማድረጋቸው ፀረ ሰላም ፀረ ክርስቶስ ነበሩ ማለት ነው::

    ከተደጋጋሚ ስህተት ለመዳን ብሎም አገራቸውንና እምነታቸውን ለማዳን ምእመናን የሚገባቸውን የቤት ስራ መስራት ይጠበቅባቸዋል::መብታቸውን ለሲኖዶስ ብቻ አሳልፎ መስጠት የለባቸውም::ግዝተትና ፍርሃት እውነትን ማሸነፍ አይኖርበትም::ቤተ እምነቶችም ፋኖ ሊኖራቸው ይገባል::

  4. Regarding Abiy Ahmed’s ploy to use the Ethiopian Church clergy to ensnare and destroy Fanno, Zemedkun Bekele writes thus:

    “…ስለዚህ መላው ዐማራ በሃይማኖት አባቶች በኩል የሚመጡበትን የመጨረሻ ኒዩክለር ቦንብ ከወዲሁ ሊያመክን ይገባል። ቀላል ነው። እምቢኝ፣ እምቢዮ፣ ጥፋ ከዚህ፣ አውግዝ፣ ደኅና ሰንብት ሊባል ይገባል። ራሱ ቤተ ክህነቱ ፋኖን የሚፈራበት ምክንያት አለው። ቤተ ክህነቱ የፋኖ መምጣት እርግጥ ከሆነ እንዲያውም ከአረመኔው አቢይ አሕመድ በከፋ ሁኔታ ፋኖን የሚታገለው ራሱ ቤተ ክህነቱና መጅሊሱ ነው። ጴንጤ አሁንም ከፋኖ ጋር እየተታኮሰ ነው።

    ቤተ ክህነቱ የወንበዴ፣ የሌባ፣ የሸርሙጦች መነሃሪያ ከሆነ ሰንብቷል። አስገድደው የደፈሩ ጳጳስ አሁንም በሥልጣናቸው እንዳሉ ነው። አስገድደው ያውም መነኩሲት አስገድደው በመንበረ ፓትርያርክ መኖሪያ ውስጥ የደፈሩ፣ የተደፈረችውም መነኩሲት ወልዳ ተቀምጣ ጳጳሱ እስከአሁን በሥልጣን ተቀምጦ እያየን፣ እየተመለከትን ከዚህ ወገን የሚመጣ ውግዘት ማንን ይጎዳ ብዬ ነው የምሳቀቅ? ዘራፊ፣ ነጋዴ፣ የፓርቲ ካድሬ ዘጭ ብሎ ቆብ አጥልቆ ቢያወግዘኝ እንዴት እሰማዋለሁ። ነፍሰ ገዳይ፣ በሻሸመኔ ምእመናንን በመትረየስ የስጨፈጨፈ ጳጳስ ላውግዝህ ቢለኝስ እሰማዋለሁ እንዴ? አዎ ፋኖ ሲመጣ እነዚህን በቤተ እምነት የተሸሸጉትን ወንበዴዎች በዥራፍ እየዠለጠ እንደሚያጠራቸው አሳምረው ያውቃሉ። እናም ከወዲሁ የመንግሥት መጠቀሚያ ኮንዶ* ወይም ሸንኮራ ሆነው ቢቀርቡ አያስደነግጠኝም።

    ስለዚህ ፋኖ ከዚያ አካባቢ የሚመጣን ገተት የራስ ምቾት ማስጠበቂያ፣ በቆብ ስር የተሸሸጉ ምቾት ያንገላታቸውን ባለ ቪ8 የደሀ ልጆችን ሰበካ እንዳይሰማ እመክራለሁ።”

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share