ኤርትራና ሲንጋፖር – አብራሃም ለቤዛ

ኤርትራ ከሲንጋፖር ጋር ለመተረክ የፈለግኩት ከሰሞኑን የኤርትራ የተባበሩት መንግስታት ተቀማጭ አማባሳደር ከሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስተር  Mr. Yap Ong Heng ጋር ተገናኙና ተወያዩ የሚል ዜና ነው፡፡  ነገር ነገር ያነሳዎል እንዲሉ ለመተረክ የፈለግኩት ስለሁቱ አገሮች ግንኙነት ሳይሆን የምስራቅ አፍሪካ ሲንጋፖር እንሆናለን ይል ስለነበረው የኤርትራዊያን ቅዠት ነው፡፡

የኤርትራ መንግስት ከኢትዮጵ ለመገንጠል በሚያደርገው ጥድፈት ዋዜማ ኤርትራን የምስራቅ አፍሪካ ሲንጋፖር እናደርጋታል ይል ነበር፡፡  የየደቡብ ምስራቅ ኤሺያ አገሮች በአጭር ጊዜ ከድህነት ስለወጡ ለብዙ የአፍሪካ አገሮች መቅኛ ነበሩ፡፡  ፈጣን እድገትና ልማት ግን ትክክለኛ  የፖሊሲ አቅጣጫ በመያዝ የሚመጣ እንጂ በማለም ብቻ የሚሆን አይደለም፡፡  የኤርትራዊን የምስራቅ አፍሪካ ሲንጋፖር የመሆን ምኞት የመጣው ራሳቸውን ከሌላው ሀባሻ የኢትዮጵ ህዝብ እንዲሁም ከትግሬ ወንድሞቻቸው ለይተው ማየታቸው ነው፡፡ የ60 ዓመት የጣሊያን ቅኝ ገዢ ፖሊሲ በኤርትራዊያን ላይ ይኸ አስተሳሰብ እንዲጫን አድረጎል፡፡ ፕሮፌሰር ተከስተ ነጋሽ “Ethiopia and Eritrea- The Federal Experience”  በሚለው ጥናታዊ ፅሁፋቸው ኤርትራዊያን ከኢትዮጵያ ለመነጠል ዳግም የሄዱበት መንገድ እኛ የተለየን ነን ፤ ከሃበሻ እኛ የሰለጠንን ነን፤ እኛ ከተገነጠልን በፍጥነት እንበለፅጋለን የሚለው አስተሳሰብ ስለሰረፀባቸው ነው ይላል፡፡

የሆነው ግን ኤርትራ የአፍሪካ ሲንጋፖር ሳይሆን የአፍሪካ ሰሜን ኮርያ ሆነ፡፡ የሃበሻ ምቀኝነት እንዲሉ ለዚህ ደግሞ የወያኔ ኢተዮጵያ ኤርትራን በማሳጣት ትልቅ አስተዋፅኦ አድርጋለች፡፡

የደቡብ ምስራቅ ኤሽ አገሮች ሲንጋፖር ፤ ማሌዥያ፤ ቬትናም፡ታይላድ ፤ኢንዶኔዢያና ፊሊፒንስ ሲሆኑ ፤ በአጭር ጊዜ ከድህነት በመውጣታቸው ምክንያትም የኤሽያ ታይገር የሚል የዳቦ ስም ወጥቶላቸዋል፡፡  የወያኔዎ ኢትዮጵያ ልማታዊ መንግስትን በመከተል የደቡብ ምስራቅ ኤሽ አገሮች መንገድ እከተላለሁ ብትልም፤  ነገር ግን የኢትዮጵያ ፖሊሲ በጎሳ ፖለቲካ ፤ የጋራ መግባባት የሌለው ፖለቲካ ሃይል እና በሙስና የተጨማለቀ ፖለቲካ ሃይል የተተበተ ስለሆነ የደቡብ ምስራቅ ኤሽያ አገሮችን ፈለግ መከተል አልቻለችም፡፡ ነገር ግን ኢትዮጵያ ለራሷ የአፍሪካ ላይዮን የሚል የዳቦ ስም አውጥታለች፡፡ ለከታታይ 14 ዓመት (2005-2019)  በሁለት ዲጂት ያደገ ኢኮኖሚ ባለቤት የሚል የተለመደ የወያኔዎች የአፍ ማሞሻ ጥቅስ ነበር፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  "… አላውቅም ! የወንድሜ ጠባቂው እኔ ነኝን … ? " ባዮቹ ፤ ቃየንአዊያን እና ባቢሎናዊያን አኛ  አይደለንምን? - መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ

ፅንፈኛው ጃ-War  መሃመድ   የኦሮሞ ፖለቲከኛም በሲንጋፖር ኢኮኖሚ እምርታ እንደሚማክና ሲጋፖር እየተማረ እናዳጠናዉም በተደጋጋሚ ይገልፃል፡፡ ችግሩ የሲንጋፖርና የደቡብ ምስራቅ ኤሽያ አገሮች ሲንጋፖር አገሮች መመንደግ ሳይሆን እነሱ የሄዱበትን  እኛ እንዳንሄድበት  ራሳችንን አድርገናል፡፡ የእኛ መንገድ ማለት በህገመንግስታችንም ሆነ በኢኮኖሚ ፖሊሲያችን ኢትዮጵያዊነት በዜጋነት እንዲደራጁ አንፈቅድም፡፡  የብሄር ፖለቲካ ይዘን እንደ ዝንጀሮ መንጋ ባለች ሃብት (ክምር) ላይ ሰፍረን መበዝበዝ እንጂ ምርታማነትና ዕድገትን አናመጣም፡፡

 

2 Comments

  1. የቅናት ወሬ ነው በታላቁ ትግሬ መሪ በኢሳይያስ አፈወርቅ ኤርትራ ትልቅ እመርታ አሳይታለች ኢኮኖሚያቸው ከብራዚልና ከታይዋን እኩል ነው፡፡ ዜጎቿ ከ70 አመት በላይ ብቻ በኤርትራ ምድር ይኖራሉ፡፡ 300 ኤርትራውያን ላምፓዱስ የሞቱት ወደ አገራቸው ተመልሰው እንዳይቀበሩ በርህሩሁ መሪያቸው ኢሳይያስ አፈወርቅ ተከልክለዋል፡፡ በዚሁ ሁሉ ነገር ዜጎቿ ለሌላው አይድላው በሚል መንፈስ ጭጭ ምጭጭ አድርገው ሰቆቃቸውን ውጠውታል እነሱ አጋሜ የሚሏቸው ትግሬዎች በምንም መንገድ ስለ ችግራቸው እንዲያዉቁ አይፈልጉም፡፡ ፍላጎታቸው ሰምሮ በትግሬ ወንድሞቻቸውም ላይ የመከራ ዶፍ እየዘነበ ነው ሁለቱም ከአንድ ውሃ እንደሚቀዳ አስተሳሰባቸውም ተንኮላቸውም ቅጥፈታቸውም አንድ ነው፡፡ ኢትዮጵያን አጥብቀው ይጠላሉ ሁለቱም ትግሬዎች መኖሪያቸውም ህልማቸውም ኢትዮጵያ ነው፡፡ የኢትዮጵያውያንን ስስና ቅን ልብ አይተው ከዘመን ዘመን ይቀልዱብናል ይህን ያየ የኢትዮጵያ አምላክ ግፉን ቆጥሮ ለላይኞቹ ከትግሬ የወጣ ሂትለር ሲሰጣቸው ለታችኞቹ ደግሞ ያበዱ መሪዎች ሰጥቷቸው ህዝቡን ያሳብዱታል ያስጨርሱታል፡፡ ህዝቡም እውሸትን ከሃሰት መለየት ቸገረው መሰል የሚግቱትን በአንድ ትንፋሽ ይጨልጣል፡፡ እስቲ የትግሬ መንበረ ፓትሪያርክ ሲመሰርቱ ትግሬ ዝም ብሎ ያያል? አዲስ አበባ ያሉት ፓትሪያርክ ትግሬ ሁነው ሳለ እንዲህ ያለ እብደት ምን ይባላል፡፡ ካህኖቻቸው ሲቀጥፉ ጌታቸው ረዳን፤ስታሊን ገ/ስላሴን ያስንቃሉ፡፡ እስቲ ልብ ይስጣቸው አሁንማ አብይን መክረው አማራ ክልል እንዳይታረስ አድርገዋል አሜሪካም በዩክሬን ተወጥሯል ምን እንደሚሆኑ ማየት ነው፡፡

  2. እኝህ ሴትዮ ጸጉራቸው እንዲህ መላ ቅጡን ሲያጣ ኢሳይያስ ዝም አላቸው? ሲንጋፖር ወደ ኤርትራ ትምጣ እንጅ እሳቸው እዚያ ምን ይሰራሉ፡፡ ኤርትራ ተስፋ ያለው ኢኮኖሚ አላት ሰው ጥጋብ በጥጋብ ላይ ነው ወደ ኤርትራ የሚመለስ እንጅ ጥሎ የሚሄድ የለም፡፡ ራሽያ የሰጠውን ስንዴም አንፈልግም ብለዋል ፈጣን እድገት ካሳዩት ከሩቅ ምስራቅ አገሮች በላይ ኤርትራ አድጋለች፡፡ ምድረ ሻቢያ እውነት መስሎህ ይህን ለጥፍ እንግዲህ፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share