“አማራን በጥበብ የተደራጀ ኃይሉን እንዲበተን አድርገንበታል!” ጌታቸው ረዳ

June 2, 2023

FxmySIoWcAMUuOk 1

ትንጊርቱ ገብረፃዲቅ ተክሌ

የኔ ምልከታ፦

የፋሺሽቱ አገዛዝ የአማራ ህዝብ ላይ ይፋዊ ጦርነት እንዲያውጅ ክፉ ምክር የሆነ አካል መክሮት ሊሆን እንደሚችል እንገምት ነበር። በርግጥ የፋሺሽቱ ቡድን በራሱ ህዝብ ላይ ጦርነት ማወጅን ስራው ስላደረገው በዚህ ረገድ መካሪ አያሻውም።

የሆነ ሆኖ ይህ የእብደት ውሳኔው አገዛዙን ከወደማይጣው ጣጣ ውስጥ ከቶታል። እንሆ አስር ነጥቦች፦

አንድ፦ ፋኖንና አማራን ትጥቅ እናስፈታለን ብለው በህዝብ ላይ ጦርነት ያወጁት እብሪተኛ ጀነራሎች ባልጠበቁት ሁኔታ ፋኖንና የአማራን ህዝብ ድጋሚ ደጁ ድረስ ሄደው ከባድ መሳሪያ ሳይቀር አስታጥቀውታል፤

ሁለት፦ መከላከያውን እንደ ተቋም ብቻ ሳይሆን ዩኒፎርሙንም ጭምር የሚያከብረውን የአማራን ህዝብ በእብሪት ጦርነት አውጀውበት ለመጀመሪያ ግዜ በታሪኩ በተቋሙ ላይ ተስፋ እንዲቆርጥና የተቋሙን ዘረኝነትና አድሏዊነት በተግባር እንዲረዳ በማድረግ ውለታ ውለውለታል፤

ሶስት፦ ከጦርነቱ በተጨማሪ የፋሺሽቱ አገዛዝ ገበሬው የማዳበሪያና የዘር አቅርቦት እንዳያገኝ በማድረጉ ወጣቱንና አርሷደሩ ወደ ህልውና ተጋድሎው በፍቃዱ እንዲቀላቀል በማድረግ ተጨማሪ ውለታ ውለዋል፤

አራት፦ አስበውም ይሁን ሳያስቡት የነብስ ወከፍ ትጥቅ ያልነበረውን ወጣት እና አርሶአደር ሁሉ ሚሊሻ ሆነህ ፋኖን ተዋጋ በሚል ቅዠት ተጨማሪ ትጥቅ በማስታጠቅ የዳበረ አቅም እንዲፈጠር አድርገዋል፤

አምስት፦ የአገዛዙ የጥፋት ጦርነቱ ህዝባዊ ሀይሉ የአገዛዙን አቅም በሚገባ እንዲረዳና በዛውን መጠን እንዲዘጋጅ እድል ተፈጥሮለታል፤

ስድስት፦ይህ የእብሪት ውሳኔ ከአማራው ውጪ ያለው የኢትዮጵያ ህዝብም በአገዛዙ ላይ ፈጽሞ ተስፋ እንዲቆርጥና የአገዛዙንም አቅም በሚገባ እንዲረዳ አድርጎታል፤

ሰባት፦ ጦርነቱ የአማራውን አንድነት ከምንጊዜውም በላይ አጠናክሯል፤

ስምንት፦ አማራ እያደረገ ያለው ተጋድሎ ከአገዛዙ በተጨማሪ ሌሎች በቀጠናው ላይ የተለየ ፍላጎት ያላቸውን ሀገራትም ጭምር አማራ በኢትዮጵያ ውስጥ ተገዳዳሪ የፖለቲካ ሀይል ሆኖ እየመጣ መሆኑን ሳይወዱ በግዳቸው እንዲረዱና መነጋገር እንዲጀምሩ አድርጓቸዋል፤

ዘጠኝ፥ ጠንካራ የአማራ የፖለቲካ ሀይል እንዲወለድና ህዝባዊ ተቀባይነት እንዲያገኝ ጦርነቱ ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማድረግ ላይ ይገኛል፤

አስር፥ በመጨረሻም አቶ ጌታቸው ረዳ እንደተናገሩት ሳይሆን በተቃራኒው ጦርነቱ የአማራ ሰራዊት በተጠናከረ ቁመና ላይ እንዲገኝና የጸና አንድነት በመካከሉ እንዲፈጠር ያስቻለ መሆኑን በዚህ አጋጣሚ መግለጽ ያስፈልጋል።

ነጻነታችን በፋሺሽቶች ችሮታ ሳይሆን በምናደርገው ተጋድሎ ብቻ ይረጋገጣል!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop