May 30, 2023
8 mins read

የታፈነዉ ጠጣር እዉነት …1 ለህዝቦች አብሮነት! – ታዬ ደንድአ

7 anchor media
#image_title
7 anchor media
#image_title

በኢትዮጵያ የአሁናዊ ሁኔታዉ አስቸጋሪነት በሚገባ ይታወቃል:: የፀጥታ.. የኢኮኖሚና የሌብነት ችግሩ አጥንት ድረስ ይሰማል:: ይህን ለመቋቋም ከብረት የጠነከረ አንድነት ይጠይቃል:: ግና እዉነቱ ታፍኖ ዉሸቱ አየር ይዟል:: አንዳንዱ ኦሮሞንና ኦሮሞነትን የችግሩ ባለቤት ሊያደርግ ሲሞክር ይታያል:: እጅግ አደገኛ የኦሮሞ ጥላቻ ተደጋግሞ ሲሰራጭ ይሰማል:: ይህ ውዥንብር ህዝቡን ላልተገባ አሉታዊ አመለካከት አጋልጧል:: ህዝቡ ያለወንጀሉ እንዲፈረጅ ተደርጏል:: በአዲስ አበባ ሆስፒታሎች ምስኪኑ ኦሮሞ ሲታመም እንኳን ለመታከም ተቸግሯል:: የሴራ ፖለቲካዉ መተባበር የሚገባቸዉን አቃቅሯል:: አዝማሚያዉ በጣም አደገኛ መሆኑን ማዬት ይቻላል:: ከአሁኑ በእዉነት ሊጠራ ግድ ይላል! ይህን ማድረግ ከባድ ዋጋ የሚያስከፍል ቢሆንም ከግለሰብ ህዝብ ይበልጣል!

ለነገሩ ሁሉም የጉዳዩን አመጣጥ ያስታዉሳል:: ከዚህ ቀደም ፖለቲካ ቁማር እንደሆነ በግልፅ ተነግሮናል:: ከኦሮሞ አንፃር ቁማሩ ሁለት ጉዳዮችን ያካትታል:: አንደኛዉ ውስጣዊ አንድነቱን መናድ ላይ አተኩሯል:: ታላቁ ህዝብ በአከባቢ.. በሀይማኖትና በጎሳ ተከፋፍሎ እንዲያንስ ታስቦ ይሰራል:: ሰሞኑን በመስኪድ ፈረሳ ምክንያት የቱለማ ኦሮሞን ከሙስሊም ወንድሞቹ ጋር ለማጋጨት የተሰራዉ ተንኮል ይታወሳል:: በመዋቅር ስም በደቡብ ኦሮሚያ የተፈጠረዉ ውዥንብርም ወንድማማቾችን ነጣጥሎ ለማዳካም ከተሸረበዉ ሴራ ይመነጫል:: እንዲህ ዓይነት ተንኮል በዞን… በወረዳ… በቀበሌና በጎጥ ደረጃም ተተግብሯል:: ለማንኛዉም ሴራዉ በተደጋጋሚ ተሞክሮ እንደከሸፈ ቁማርተኛዉም ያዉቃል! ህዝቡ ከሴረኛዉ ቀድሟል!

ኦሮሞን በወንድሞቹ ዘንድ ለማስጠላት የተወጠነዉ ሁለተኛዉ ቁማር ግን አደገኛነቱ ያሳስባል:: በአንድ በኩል ከማንም በላይ በመከራ እሳት እየተቃጠለ ያለዉን ንፁህ ህዝብ የተለየ ተጠቃሚ ለማስመሰል የሀሰት ሪፖርት ይቀርባል:: የፎቶና የቪድዮ ድራማ ይሰራል:: በሌላ በኩል ደግሞ አሳፋሪ ተግባራት ተፈፅሞ በኦሮሞነት ካባ ይፎከራል:: ሀይማኖትና ብሔር በአደባባይ ይዘለፋል:: ያለሀፍረት “ፖለቲካ በማታለል የታጀበ ቁማር ነዉ” ይባላል:: ቁማሩን የሚጫወቱትም ለኦሮሞ ተብሎ እንደሆነ ይመሰላል:: ጫወታዉን ለማሳመር በቁማርተኛዉ ስብዕና ፈፅሞ የሌለዉ ኦሮሙማ በየመድረኩ ይደጋገማል:: በዘመድ አዝማድ ተደራጅቶ ሀገር ይጋጥና በተጎጂዉ ህዝብ ስም ለመሸፈን ይሞከራል:: በህዝቡ ዘላቂ ኪሳራ ሴረኛና ዘራፊ ጊዜያዊ ርካሽ ጥቅሙን ያካብታል:: ህዝቡ ግን በ21ኛዉ ክፍለ ዘመን በረሃብ ሲሞት ሁሉም አይቷል:: የሌሎችን እርዳታ እንኳን እንዳያገኝ ለገፅታ ጥራት ተብሎ መከራዉ ይደበቃል:: በአጋጣሚ የህዝቡ መከራ ከተሰማ መልሶ ለመሸፈን ዶክመንተሪ ይሰራል:: አሁን በኦሮሚያ ስለህዝቡ ሞትና መፈናቀል መረጃ ማግኘት ከሰማይ ይርቃል! የክልሉ ህዝብ በኢህእዴግ ዘመን የነበረዉን የህብት ነፃነትን እንኳን አጥቷል:: በሌቦች ዉሳኔ ምርቱን ከገበያ ዋጋ በታች ለቁመርተኛዉ ደላሎች ለመሸጥ ይገደዳል:: ማህበራዊ ግልጋሎት ከናካቴዉ ተረስቷል:: በሀገር ደረጃ 3 % የነበረዉ የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት እንኳን በኦሮሚያ 2% ብቻ እንደነበር ልብ ይሏል! በተለያዬ ቦታ ሰዉ በዘፈቀደ ይገደላል:: የከረዩ አባገዳ ከ14 ባለሟሎቹ ጋር ተረሽኖ ፍትህ ተነፍጏል:: ከኢትዮጵያ በውሳኔ የቆመዉ የስቃይ ምርመራ በኦሮሚያ ብቻ ቀርቷል:: ዛሬም እንደትላንቱ ዜጎችን በምርመራ ስም ማኮላሸት ቀጥሏል!

ነገር ግን የህዝብ ፍላጎትና የቁማርተኛ ጥቅም ለየቅል:: ሌብነት እንደሀገርም ከባድ ጉዳት ማስከተሉ በፓርላማ ሳይቀር ተደጋግሞ ተነስቷል:: ህገ-መንግስቱን በመቃረን መሬት የሌባና የደላላ መሆኑን ሰምተናል:: ኦሮሞ ደግሞ ከማንም በላይ የሌብነት ሰለባ ሆኗል:: አብዘኛዉ የተዘረፈዉ መሬት የኦሮሞ አርሶ አደር መሆኑ ይታወቃል:: ኦሮሞ ሀብት-ንብረቱ ብቻ ሳይሆን ማንነቱ ጭምር ተሰርቋል:: ዉሃ ሲጠይቁት ወተት የሚሰጥ የዋው ህዝብ ገፊና አፈናቃይ እንዲመስል ተደርጏል:: ከነባራዊዉ ትርክት አንፃር ይህ እዉነት ለማመን ሊቸግርም ይችላል:: ግና መራራ ሀቁን መግለፅ አሁን ግድ ይላል:: የቁማርተኛ ሌባ ወንጀል ፈፅሞ ኦሮሞን አይመለከትም:: በመሰረቱ ሌባ ሆድ እንጂ ብሔር .. ሀይማኖት ወይም ሰፈር የለዉም:: ትውልዱ የትም ቢሆን ሌባ ከሌባ አይለይም:: ኦሮሞነት… አማራነት ወይም ትግራዋይነት ክፋቱን አይለውጥም:: እዉነቱን ለምናገር ግን አቃፊዉ የኦሮሞ ህዝብ የወንድሞቹ ደስታና ሀዘን ተጋሪ እንጂ ለቁማርተኛ ሌቦች ወንጀል አባሪ አይደለም!

ለህዝቦች አንድነት ሲባል የታፈነዉ ጠጣር እዉነት ሊገለጥ ይገባል:: ቁማርተኛ ሌቦች በህዝብ ኪሳራ ለመጠቀም ኦሮሞን ልዩ ተጠቃሚ ለማስመሰል ብዙ ደክሟል:: በተጨባጭ ግን ምስኪኑ የኦሮሞ ህዝብ የቁማሩ ልዩ ሰለባ ሆኖ ይገኛል:: ከሁሉም ለከፋ መካራ መጋለጡ አንሶት በወንድሞቹ ዘንድ ባልተገባ መንገድ ይታያል:: ለህዝቦች ሰላም… ነፃነት.. እኩልነት.. ወንድማማችነትና የጋራ ዘላቂ ተጠቃሚነት ሲባል እዉነቱ ሊነገር ይገባል!

እዉነትና አንድነት ለሰላም! ሠላም ለኢትዮጵያ! ሰላም ለሰዉ ልጆች! መልካም ቀን!

ታዬ ደንድአ

1 Comment

  1. If Amhara and other region PP leaders have a gut they can use this information to confront Abiy and Co in the on going meeting. Thanks Taye Dendea!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

183002
Previous Story

ከ ፬ ኪሎ የተሰማው ጉድ/ከአማራ ህዝባዊ ግንባር መግለጫ ተሰጠ/የባለስልጣኑ አጃቢ ያደረገው የሴት ጠለፋ/(አሻራ ዜና

Abiy Ahmed 3 1 1
Next Story

በሁሉም አከባቢዎች ያሉ ፀረ-ዴሞክራሲያዊ ብሄርተኞች ሃገር የቆመበትን ምሰሶ የሚቦረቡሩ ቅንቅኖች ናቸው!!!

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop