May 17, 2023
5 mins read

ከቶ ማን ነው ህገ ወጡ? – ገለታው ዘለቀ

FwUPaltXsAEZXy

የኦሮምያ ክልል መንግስት አዲስ አበባ ላይ ቤተ መንግሥት እሰራለሁ ብሎ ቢሊዮን ብሮች መድቧል። በአንድ በኩል የኦሮሞ ህዝብ ስንት ፈጥኖ ደራሸ እርዳታ በሚፈልግበት በዚህ ሰአት የክልሉ መሪ ቅንጡ ቤተመንግስት ለመገንባት መነሳቱ አንድ አሳዛኝ ታሪክ ነው።

በጣም የሚገርመው ነገር ግን ይህ የቤተመንግስት ግንባታ ህገ ወጥ መሆኑ ነው።  የኦሮምያ መንግስት አዲስ አበባ ላይ ቤተ መንግሰት ለመስራትም ሆነ መቀመጫውን ለማድረግ የሚያስችለው አንድም ድንጋጌ የለም። በፌደራሉ ህገ መንግስትም ይሁን በኦሮምያ ህገመንግስት ውስጥ አዲስ አበባ የኦሮምያ ክልል መቀመጫ ናት የሚል ድንጋጌ የለም። የተሻሻለው የኦሮምያ ህገ መንግስትም አዲስ አበባ ዋና ከተማዬ ናት አይልም። ለነገሩ የኦሮምያ ክልል ህገ መንግስት ይህንን ለማለት ቢነሳም ከዋናው ህገ መንግስት የሚቀዳ ስለማይሆን ውድቅ ይሆናል። የሆነ ሆኖ ግን አንድም ሰነድ አዲስ አበባ የኦሮምያ ዋና ከተማ ናት የሚል የለም።
 በዚህ ሰአት ፌደራል መንግስት አዲስ አበባን መቀመጫው ሲያደርግ ድንጋጌዎች አሉት። በፌደራል መንግሥት እና በአዲስ አበባ አስተዳደር መካከል ህጋዊ መተሳሰር አለ። ትስስሩ መሻሻል እንዳለበት የሚታወቅ ቢሆንም።
FwUPcDLWIAEGbFw
#image_title
 ነገር ግን በኦሮምያና በአዲስ አበባ አስተዳደር መካከል ድንጋጌዎችን መሰረት ያደረገ አንድም ትሰሰር የለም። በዚህ መሰረት የኦሮምያ መንግስት አዲስ አበባ ላይ የተቀመጠው ህገ ወጥ ሆኖ ነው። ግንባታዎቹ ህገ ወጦች ናቸው። ይልቅ እነዚህ ህገ ወጥ ቤት ሰርታችኋል የሚባሉት እና ቤታቸው የሚፈርስባቸው ወገኖች ይልቅ እነሱ ከገበሬው መሬት ያዛወሩበት ሰነድ አላቸው። ደግሞም መንግስት የቤት ፍላጎቶችን ማሟላት ስላልቻለ ጎጆ ቀልሰው የሚኖሩ ዜጎች ናቸውና ልንታገሳቸው የሚገባቸው ነበሩ።
አዲስ አበባ ላይ የኦሮምያ መንግስት ያለ ምንም ድንጋጌ ዋና ከተማዩ እያለ ሲኖር፣ ግንባታ ሲያካሂድ፣ ወይዘሮ አዳነች አበቤ ሽፋን ይሰጣሉ። ለነገሩ እኚህ ሴት ከንቲባ የሆኑትም ለዚህም ነው። ወይዘሮ አዳነች በአንድ ወቅት ህገ መንግስታችን አዲስ አበባ የኦሮምያ መቀመጫ ናት ይላል ብለው የሃሰት መረጃ ሰጥተው አልተጠየቁም። አዲስ አበባ የኦሮምያ ዋና ከተማ ናት የሚል በሀገራችን ሰማይ ስር አንድም ህግ የለም ጎበዝ።
ከሁሉም ከሁሉም የልየሚያሳዝነው ግን ፓርላማውም ይሁን የአዲስ አበባ ምክር ቤት የኦሮምያን ክልል መንግሰት ለመሆኑ በየትኛው ድንጋጌ ነው አዲስ አበባ መቀመጫዬ ናት የምትለው? ድንጋጌ አምጣ፣ ስነድ አምጣ፣ ብሎ አለመጠየቁ ነው። የጉድ ሀገር……ከማለት ሌላ ምን ይሏል?
አዲስ አበባ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ ቤት መሆኗ ተከብሮ ደግሞ የኦሮምያ ክልል መቀመጫ አዲስ አበባ ይሁን ከተባለ ስምምነትና ድንጋጌ ያስፈልጋል እኮ። የአዲስ አበባ አስተዳደር እና የኦሮምያ ክልል የሚተሳሰሩበት ግልጽ ዶክመንት ያስፈልጋል እኮ። አገርን የሚያስተዳድር ሰው እንዴት ህገ ወጥ ስራ በዚህ ደረጃ ይሰራል?
ወገኖቼ ሆይ በዚህ ሰአት የኦሮምያ መንግስት እንቅስቃሴ አዲስ የአበባ ላይ ህገ ወጥ ነው። ሁላችንም ተባብረን ህግ ይከበር እንበል። አሰራርና ህግ ይኑር። እባካችሁ ህግ ይከበር!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop