May 1, 2023
3 mins read

ጋዜጠኛ ሙሉጌታ አንበርብር የሚከተለውን መልስ ሰጥቷል።

344546779 2034007546941136 4078334548667587036 n

ኦህዴድ መራሹ የዐቢይ አህመድ መንግሥት “የአማራ ሕዝብን እንደ ሕዝብ የምናደርስበትን መከራ ለምን ድምፅ ሆናችሁት” በሚል በርካቶችን እያሳደደ እና እያሰረ ይገኛል።
በዛሬው ዕለትም እኔን እና ወንድሞቼን “ሕገ – መንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለማፍረስ” በሚል በሽብር ወንጀል እፈልጋቸዋለሁ እያለ ነው።
ወንድማችን ግርማ የሺጥላን የገደለው ኃይል ከያዛቸው ከወራት በላይ የሆናቸውን እንዲሁም ፍርድ ቤት የዋስ መብት የሰጣቸውን ግለሰቦች የዋስ መብታቸውን ነፈጎ በአዲስ ክስ ለመመሥረት አመቺ መንገድ መፍጠሩ ነው። የዐቢይ አህመድ ‘መንግሥት’ የጡት አባታቸውን ሕውሓትን ከምኒልክ ቤተ መንግሥት ከመባረር እንዳላዳናቸው ማወቅ ተሥኗቸዋል።
በወንድሜ ሻለቃ ምሬ ወዳጆ እና በፋኖ በለጠ ጋሻው የተቀነባበረው የድምፅ ልውውጥም በማን እንደተቀነባበረ እንኳን እንደ እኔ አይነቱ ጋዜጠኛ እና የሳይበር ደህንነት ስልጠና ለወሰደ ሰው ለተራ ግለሰብም ሀሰተኛ የድምፅ ቅንብር መሆኑ የሚሰወር አይደለም።
እኔ አንድ አማራ ነኝ፤ በአማራነቴ የመጣብኝን መከራ እቀበለዋለሁ። ነገር ግን ስንቱን ገድሎ እና አፈናቅሎ እንደሚጨርሰው አብረን የምናየው ይሆናል። እኔና ሌሎች ጓዶቼ የአማራ ሕዝብ እንደ ሕዝብ ከፈጣሪ የተሰጠውን የመኖር መብት ቀምተን ከባሪያ ያነሰ አኗኗር እናኑራችሁ ለሚለን አካል እሺ እንደማንል ያደግንበት ሥሪትም ሆነ ሥነ – ልቦናዊ ውቅር እንደሌለ ልታውቁት ይገባል። ስለዚህ እንኳን የእስር ማደኛ አግኝታችሁ ብትሰቅሉኝም ከባሪያ ያነሰ ሕይወት ከምገፋ ለነጻነቴ እየታገልሁ ብሰቀል አይቆጨኝም።
የአማራ ሕዝብ እንደ ሕዝብ ሁሉም ፋኖ መሆኑ እየታወቀ “ኢ – መደበኛ” ማቃለያ ሕዝብን እንደ ሕዝብ ፈርጆ ለማጥፋት እየተንቀሳቀሰ መሆኑ መላው የአማራ ሕዝብም ሆነ ሌላው ኢትዮጵያዊያን ብሎም ለሰብዓዊ መብት መከበር የቆሙ የአገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ ተቋማት ጉዳዩን በልዩ ትኩረት እንዲከታተሉት እና እየተፈፀመ ያለውን የዘር ጭፍጨፋ እና የዘር ማጽዳት እንዲያስቆሙ ጥሪ ማቅረብ እፈልጋለሁ።
በመጨረሻም፦
አማራ ግን የታወጀብትን የዘር ጭፍጨፋ እና የዘር ማጽዳት ግን ቀልብሶ እንደሚወጣ እርግጠኛ ነኝ!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop