April 14, 2023
3 mins read

አትሰቀል ይቅር! (አሥራደው ከፈረንሳይ)

ab67616d00001e02632b311051d3a98b957ef156
#image_title

ab67616d00001e02632b311051d3a98b957ef156

በገባለት ቃሉ – አባትህ ለ’ኛ አባት፤
አንተ ለኛ ሞተህ – ልንድን ከሃጢያት፤
እኛን አድናለሁ – ብለህ ከመከራ፤
መስቀል ተሸክመህ አትውጣ ተራራ::

በጨካኞች ጅራፍ – አይገረፍ ጀርባህ፤
ምስማር አይቸንከር – በጅና በግሮችህ፤
በጦር አይወጋ – አይበሳ ጎንህ፤
አትጠጣ ፍጹም – የሃሞት መራራ፤
አድናለሁ ብለህ – እኛን ከመከራ፤
መከራህ አይብዛ መከራችን ላይቀር፤
ተንገላተህ አትሙት አትሰቀል! ይቅር::

ተከባብሮ መኖር – አብሮ መብላት ቀርቶ፤
ጥላቻ፤ ጭካኔ – መከራ በርክቶ፤
ወንድማማችነት – ፍቅር መተባበር፤
አንድነት፤ ነፃነት – ፍጹም ጠፍተው ካገር፤
መቻቻል፤ ደግነት – ከሃገር ተሰደው፤
ግፍ በደል በርክቶ – ሞልቶ ፈሶ ጽዋው፤
ሰው ሆነን ሰው ካልሆን – ተፈጥረን ባምሳልህ፤
ከሰማየ ሰማይ – ወርደህ ከዙፋንህ ፤
አፈር ለባሽ ገላ : ከንቱ ሥጋ ለብሰህ፤
አትሰቀል በቃ! እኛን ላድን ብለህ ::

ይልቅስ ከሰሙህ እንዲህ ምከራቸው………!
እንደዚህ በላቸው – ስልጣን ላዋስካቸው……!

ስልጣን ተገን አርጎ – ቀምቶ የበላ፤
ለሥጋው አድልቶ – ወገኑን ያጉላላ፤
ዘረኝነት አርሶ – ቂም በቀል የዘራ፤
የሚያበዛ ት’ቢት – ሰው የሚያስፈራራ፤
ውሸት ያመረተ – በደል የከመረ፤
በግፍ የገደለ – ወህኒ ቤት ያጎረ፤
ጥላቻን አንግሶ – ፍቅርን ያኮሰሰ፤
ወንድሙን የገፋ – በደል ያነገሰ፤
ቁጣዬን አብዝቶ: መከራውን ያጭዳል፤
ሕዝቤን አታጉላሉ: ከንግዲህ ይበቃል !
ብለህ ንገራቸው………!
ልቦና ቢገዙ…. ድንገት ቢመለሱ.… ወደ ሕሊናቸው ::

ግን፤
የሕዝብህን ጩኸት – እየሰማ ጆሮህ፤
ስቃይ መከራውን – እያየኸው ባ’ይንህ
ሲካድ ሰብዕናው – ፈጥረኸው ባምሳልህ፤
ዝምታህ ከበዛ – ከዘገየ ፍርድህ፤
ኤሎሄ ! ኤሎሄ ! ላማ ሰበቅታኒ: ላ’ባትህ ልናገር፤
ቁም ስቅልህ ይብቃ! እኛ አልዳንምና: አትሰቀል ይቅር!!

አንድ ቀን

በፍትህ እጦት በወህኒ ቤት፤ በኑሮ ውድነት፤ በሥራ አጥነት፤ በስደት ለሚጉላው፤ ኢትዮጵያዊ ወገኖቼ ማስታወሻ ትሁንልኝ::

 

 

 

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Amhara Genocide
Previous Story

ዐምሐራ ይግደለኝ!!! – ያሬድ መኩሪያ

6765666 1 3 1
Next Story

ኢትዮጵያን ማዳን የፈለገ ሁሉ፤ አማራን ለማዳን መነሳት አለበት – አንዱ ዓለም ተፈራ 

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop