ያማራን ሕዝባዊ ትግል ማጧጧፊያ ሰባት ነጥቦች፤ አማራነት ወይም ሞት 

ጭራቅ አሕመድ ለማጥፋት የተነሳው አለቅጥ የሚፈራውን አማራነትህን ነውና፣ ባማራዊ እንድነት በነቂስ ተነሳስተህ፣ አማራነት ወይም ሞት ብለህ ጭራቁን ጨርቅ አድርገው፡፡

አንደኛ ነጥብ

መሪር ጠላትህን አምርረህ የምትታገለው አምርረህ ስትጠላው ብቻና ብቻ ነው፡፡  በማክበር የምትጠራውን ደግሞ አምርረህ አትጠላውም፡፡  ለምሳሌ ያህል ኦነጋውያን ሳት ብሏቸው እንኳን አጤ ምኒሊክን አንድም ቀን አጤ ብለው አያውቁም፡፡  ወያኔወችም መንግስቱ ኃይለማርያምን ኮልኔል መንግስቱ እንጅ ሊቀመንበር መንግስቱ ብለዋቸው አያውቁም፡፡

ጭራቅ አሕመድ ደግሞ አንቱ፣ እርስወ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር እየተባለ በከበሬታ ሊጠራ /የማይገባው/ ክብረቢስ፣ ቢባልም \የማይገባው\ እውቀትቢስ ነው፡፡  አሳዳጊው ወያኔ አለቅጥ የበደለው የስዶች ስድ፣ የባለጌወች ባለጌ፣ የወራዳወች ወራዳ፣ የነውረኞች ነውረኛ ነው፡፡

ጭራቅ አሕመድ ዶክተር አይደለም፣ የቀጣፊነት ወይም ያጭበርባሪነት ዱክትርና እስከሌለ ድረስ፡፡  እሱ ራሱ ዱርየ ስለሆነ፣ ዱርየውን ጭራቅ አሕመድን በደንብ የሚያውቀው ጌታቸው ረዳ በትክክል እንደተናገረው፣ ጭራቅ አሕመድ ፈረንጆቹ አራዳ (street smart) ወይም ጮሌ የሚሉት፣ ሲዋሽ ዓይኑን የማያሽ ቀጣፊ፣ አፉ ጥሬ የሚቆላ ምላሳም፣ አንደበቱ ያልተገራ ስድ ከመሆኑ በስተቀር፣ ለማገናዝበ የሚያስችለው ምንም እውቀት ስለሌለው የነገሩት ሁሉ ውነት የሚመስለው ተራ ማይም ነው፡፡

ያማራን ሕዝብ በተመለከተ ደግሞ ጭራቅ አሕመድ የኦነግንና የወያኔን ፀራማራ ጥምር ጦር በጠቅላይነት የሚመራ ጠቅላይ ወንጀለኛ (prime criminal) እንጅ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር (prime minister) አይደለም፣ የተቀመጠበት መንበር የጠቅላይ ሚኒስትርነት ቢሆንም፡፡  ስለዚህም ያማራ ሕዝብ ይህን እኩይ ግለሰብ ጭራቅ፣ አረመኔ፣ አጭበርባሪ፣ ቀጣፊ እያለ በምግባሩ እንጅ በመንበሩ ሊጠራው አይገባም፡፡

ይህን ወራዳ ግለሰብ ዶክተር፣ ጥቅላይ ሚኒስተር፣ እሳቸው እያሉ በማይገባው ክብር የሚጠሩትን ደግሞ፣ ያማራ ሕዝብ በሁለት ዓይነት መንገድ ሊመለከታቸው ይገባል፡፡  የመጀመርያወቹ ዓይነቶች አጉል ጨዋ ለመምሰል ወይም ለመባል የሚፈልጉ አጉል ተምጻዳቂወች ናቸው፡፡  ሁለተኛወቹ ዓይነቶች ደግሞ ጭራቁን ላልማስቀየም የሚሞክሩ፣ እንደ ሲሳይ አጌና ስማቸውን ጠርቶ ካሞገሳቸው ደግሞ እግሩ ሥር ለመውደቅ የተዘጋጁ አድርባዮች ናቸው፡፡   ሁለቱም ዓይነቶች ደግሞ ላማራ ሕዝብ የሕልውና ትግል ስለማይበጁ፣ ያማራ ሕዝብ አንቀሮ ሊተፋቸው ይገባል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  መልእክተ-አንቃእድዎ ! ጤና ይስጥልኝ፤ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አቢይ አህመድ

ሁለተኛ ነጥብ

ባሁኑ ዓይነት ወሳኝ ሰዓት ላይ መሪ ይሆንህ ዘንድ የፈጠርከውን ድርጀት (ያማራ ብሔራዊ ንቅናቄ፣ አብን) ከቀንደኛው ፀራማራ ከጭራቅ አሕመድ ጋር ተምሳጥረው ያፈራረሱብህን የአብን አመራሮች (በተለይም ደግሞ በለጥ ሞላና ጣሂር ማንትሴ የሚባሉትን) ማየት ያለበህ ጭራቅ አሕመድን በምታይበት ዓይን ነው፡፡  በነሱ ላይ መውሰድ ያለብህ ደግሞ በጭራቅ አሕመድ ላይ ልትወስደበት የሚገባህን ዓይነት ርምጃ ነው፡፡

ሶስተኛ ነጥብ

አማራዊ ስም ያለው ሁሉ አማራ እንዳልሆነ አትርሳ፡፡  ቆንጆ ያማራ ስም ይዘው አማራን ከወያኔና ከኦነግ በላይ የሚጠሉ ፀራማሮቸ እንዳሉ አትዘንጋ፡፡  አብዛኞቹ የብአዴን አመራሮች ደግሞ ማንነታቸውን በቆንጆ ያማራ ስም የሸሸጉ፣ ያማራ ለምድ የለበሱ ፀራማራ ተኩላወች መሆናቸውን እወቅ፡፡  ከወያኔና ከኦነግ በላይ አማራን አምረሮ የሚጠላ ፀራማራ ካልሆነ በስተቀር፣ የሰናፍጭ ቅንጣት የምታህል አማራዊነት ያለው ወይም የሚሰማው ሰው፣ ምንም ያህል ለሆዱ ያደረ ሆዳደር ቢሆንም፣ ደመቀ መኮንን፣ ተመስገን ጡሩነህ፣ ሰማ ጡሩነህ፣ አበባው ታደሰ፣ ብናልፍ አንዷለም፣ መላኩ አለበል፣ ግርማ የሺጥላ፣ ይልቃል ከፋለ እና መሰሎቻችው የፈጸሟቸውንና የሚፈጽሟቸውን ፀራማራ ተግባሮች አይፈጽምም፡፡

ስለዚህም እነዚህን ከወያኔና ከኦነግ በላይ አማራን የሚጠሉ፣ ያማራ ለምድ የለበሱ፣ የብአዴን ፀራማራ ተኩላወች፣ ከሕዝባችሁ ጋር ቁሙ እያልክ በመለመን ጊዜህን አታጥፋ፣ አማራ ሕዝባቸው አይደለምና፡፡  ይልቁንስ በማናቸውም መንገድ እነሱን ለማስወገድ የምትችለውን ሁሉ አድርግ፡፡

ዐራተኛ ነጥብ

አቶ ልደቱ አያሌውን የመሰሉ የጦቢያዊነት አቀንቃኞች ነን የሚሉ የፖለቲካ ተንታኞችን ባይነ ቁራኛ ተመልከት፡፡  እነዚህ ግለሰቦች ያማራ ሕዝብ ትግል የተዳፈነ ወይም የጠፋ ሲመስላቸው እነሱም ድምፃቸውን ያጠፋሉ፡፡  ያማራ ሕዝብ ትግል እንደ ሰደድ እሳት ተቀጣጥሎ ወያኔንና ኦነግን ሊያንጨረጭራቸው ሲል ግን፣ ከተደበቁበት ወጥተው በየሚዲያወቹ እየተሯሯጡ አማራጭ የሚሏቸውን ሐሳቦች ያቀርባሉ፡፡  አማራጭ የሚሏቸው ሐሳቦች ግን ለሰሚ ጆሮ የሚያስደሰቱ ቢሆኑም፣ ነባራዊ ሁኔታወችን ያላገናዘቡ በመሆናቸው ሊተገበሩ የማይችሉ ተምኔታዊ አማራጮች ናቸው፡፡  ስለዚህም ያቶ ልደቱና የመሰሎቹ ዋና ዓላማ አማራጭ ሐሳብ ለማቅረብ ሳይሆን የአማራን ሕዝብ ውጤታማ ትግል አቅጣጫ በማስቀየር፣ ምንም ውጤት ወደሌለው ወደ ወሬ ትግል ለመለወጥ ነው ብለህ ጠርጥር፣ ያልጠረጠረ ተመነጠረ ነውና፡፡  

ተጨማሪ ያንብቡ:  የተቆለፈበት ቁልፍ ! ከዶ/ር ምህረት ደበበ፣ የአዕምሮ ህክምና ስፔሺያሊስት፣ 438 ገጽ ትችት! -  በዶ/ር ፈቃዱ በቀለ

ስለዚህም አቶ ልደቱና መሰሎቹ ለሚሰብኳቸውና ለሚከትቧቸው ሊተገበሩ የማይቸሉ ፍሬከርስኪወች ጆሮህን አትስጥ፡፡  አውቆ የተኛውን ጭራቅ አሕመድን ለመቀስቀስ  “ግልጽ ደብዳቤ ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር” እያሉ የሚጽፏቸውን አሳፋሪ የልምምጥ ደብዳቤወች ደግሞ ማንበብ ቀርቶ አትክፈታቸው፡፡

የነ አቶ ልደቱን ምንም የማይፈይድ እንቶ ፈንቶ ቋንቋ ለነ አቶ ልደቱ ትተህ፣ ወያኔንና ኦነግን በሚገባቸው ቋንቋ አናግራቸው፣ የሚገባቸው ቋንቋ ደግሞ ኃይልና ኃይል ብቻ መሆኑን አትርሳ፡፡  ኦነግና ወያኔ የሕልውና ጠላቶችህ ስለሆኑ፣ እነሱን በተመለከት ያለህ አማራጭ እነ አቶ ልደቱ የሚያቀርቡት ከትግልህ የማዘናጊያ እንቶ ፈንቶ አማራጭ ሳይሆን፣ የሞት የሽረት አማራጭ መሆኑን ላፍታም ቢሆን አትዘንጋ፡፡  ኦነግና ወያኔን ካላጠፋሃቸው እንደሚያጠፉህ አውቀህ፣ ባልሞት ባይ ተጋዳይ ስሜት የሞት ሽረትህን ታገላቸው፡፡

አምስተኛ ነጥብ

ከጭራቅ አሕመድ ጋር ወይም የሱ ሎሌወች ከሆኑት ያማራ ለምድ ከለበሱት ፀራማራ ብአዴናዊ ተኩላወች ጋር ላሸማግልህ ብሎ የሚመጣን አሸማጋይ ነኝ ባይ ሁሉ (አርጋዊ፣ ባህላዊ፣ ጳጳስ፣ መጅሊስ ሳትል) የጭራቅ አሕመድ ተላላኪ ነውና፣ ባንዳነቱ ነግርህ አሳፍረህ መለሰው፡፡  ድጋሚ ከመጣ ደግሞ አመጥጡ ያለህበትን ቦታ ለጭራቅ አሕመድ ሊጠቁም ነውና ግንባሩ ብለህ እዛው አስቀረው፡፡

የዘመነ ካሴን ስሕተት እንዳትደግም ተጠንቀቅ፡፡  ጭራቅ አሕመድ ማለት ሲያቃጡበት የሚጥመለመል፣ ሲዞሩለት የሚናደፍ አሲል እባብ መሆኑን መችም ቢሆን አትርሳ፡፡  ጭራቅ አሕመድ እግርህ ላይ የሚወደቀው ማጣፊያው ሲያጥረው ብቻ እንደሆነ አትዘንጋ፡፡  እግርህ ላይ ሲወደቅ ተነስ በለህ እጆችህን ከሰጠኸው ደግሞ ስቦ ስለሚጥልህ፣ በወደቅበት አናቱን በርቅስህ ተገላገለው እንጅ ዳግም እንዲነሳ ዕድል አትስጠው፡፡  እባብ ግደል ከነብትሩ ገደል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:   ያማራ ሕዝብ ሆይ ቋንቋህን አርም፣ አረመኔን አረመኔ አለማለት ፈሪነት እንጅ ጨዋነት አይደለም

ስድስተኛ ነጥብ

የጭራቅ አሕመድ አራጅ ሠራዊት አለህበት ደርስ መጥቶ እስኪያርድህ አትጠበቅ፡፡  እሱ ወዳንተ ሲመጣ አንት ወደሱ ሂድና ባላሰበው መቸት (መቸና የት) ግጠመው፡፡  በተለይም ደግሞ በኮንቮይ (ሰልፍ) የሚመጣ ከሆነ፣ ተራራማ ቦታ ላይ መሽገህ ጠብቀውና፣ የሰልፉን የመጀመርያና የመጨረሻ መኪኖች በፈንጅና በመሳሰሉት አውድመህ፣ ወደፊትም ወደኋላም መንቀሳቅስ የማይችለውን አራጅ ሠራዊት በጥይት ቁላው፡፡  በመድፍ ሊጨፈጭፍህ የመጣውን ኦነጋዊ አውሬ በመትረየስ ረፍርፈው፡፡

ሰባተኛ ነጥብ

አንድ አማራ ለሁሉም አማራ፣ ሁሉም አማራ ላንድ አማራ ነውና ባንተ ትብስ አንተ ትብስ መንፈስ ተባበር፣ ተከባበር፡፡  የአካል ብልቶች ብዙ ቢሆኑም፣ የአንድ በአንድ ለአንድ ናቸው፡፡  ዓይን ጆሮን ንቆ አያስፈልገኝም ቢል፣ የደንቆሮ ዓይን ይሆናል፡፡  ጆሮ ዓይንን ንቆ አያስፈልገኝም ቢል፣ የእውር ጆሮ ይሆናል፡፡  እጅ እግርን ንቆ አያስፈልገኝም ቢል፣ የስንኩል እጅ ይሆናል፡፡  እግር እጅን ንቆ አያስፈልገኝም ቢል፣ የዱሽ እግር ይሆናል፡፡

ጭራቅ አሕመድ ለማጥፋት የተነሳው አለቅጥ የሚፈራውን አማራነትህን ነውና፣ ባማራዊ እንድነት በነቂስ ተነሳስተህ፣ አማራነት ወይም ሞት ብለህ ጭራቁን ጨርቅ አድርገው፡፡

 

መስፍን አረጋ

mesfin.arega@gmail.com

 

1 Comment

  1. እናመሰግናለን በዚህ ህዝባዊ ማእበል አለአግባብ የታሰሩትን አማሮች እስር ቤቱን ሰብሮ መልቀቅ ማንን ቸገረ? ወንጀለኛ ያላግባብ የታሰረው ፋኖና ህዝባዊ ሰራዊት ሳይሆን ብአዴንና ህወአት ነው፡፡ ከስብሃት ነጋና ከትግሬ ወንጀለኞች በላይ አለም ላይ ወንጀለኛ ይኖራል?

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share