አንዳንድ ሰዎች ስለትላንትናው የፍ/ቤት ትእዛዝ የሚያወሩትን አወዛጋቢ ጉዳይ በተመለከተ – ከአንዱአለም በእውቀቱ

ከአንዱአለም በእውቀቱ ፌስቡክ ገፅ የተወሰደ።

አንዳንድ ሰዎች ስለትላንትናው የፍ/ቤት ትእዛዝ የሚያወሩትን አወዛጋቢ ጉዳይ በተመለከተ ለብጹአን አባቶች ዛሬ ጠዋት ገለጻ አቀረብን።

አንተ ከያዝከው የጦር መሳሪያ እኔ የያዝኩት መስቀል ይበልጣል
አንተ ከያዝከው የጦር መሳሪያ እኔ የያዝኩት መስቀል ይበልጣል

‘ህገወጡ ቡድን የያዛቸውን ቦታዎች ለምን ይዞ እንዲቀጥል ተባለ?!’ የሚለውን ጠየቁን።

እስከ አሁን የእግድ ፋይል እንጂ(ያውም ክስ ሳይጀመር በእግድ ጉዳይ ብቻ በቀጥታ የተከፈተ የመጀመሪያው የፍ/ቤት ፋይልም ነው) ዋናው ክስ እንዳልተከፈተ :ከጉዳዩ ውስብስብነት አንጻር ክስ ለመክፈት ጊዜ ለማግኘት ሰው እንዳይሞት ሲባል ለፍርድ ቤት እግድ ጠይቀን በዚህ ጉዳይ ያሉ አከራካሪ ነገሮች እስኪጠናቀቁ ብቻ የተሰጠ ጊዜያዊ የእግድ ትእዛዝ መሆኑን :የቤተክርስትያን ንብረቶችን የማስመለስ ክስ በቀጣይ የምንከፍት መሆኑን ነገርናቸው ።

…ለአንዳንዶች ‘ኒውክለር ሳይንስ’ የሆነባቸው የእግድ እና የውሳኔ ልዩነት ብጹአን አባቶች ለመረዳት 30 ሰከንድ ነው የፈጀባቸው!!

ያስገኘነውን ውጤት በተመለከተ በመላው ብጹአን አባቶች አጥንት ድረስ የሚደርስ ምርቃት እና መባረክ ተችሮናል!!

ከዛ በተረፈ ቅድም እንደሰማችሁት አንዳንዶች እኔን እና አንዳንድ የህግ ኮሚቴ አባላትን በተመለከተ እላፊ ሄደው የሚናገሩት ለቤተክርስትያን ካላቸው ቀናኢነት እና መንፈሳዊ ቅናት የመነጨ መሆኑን በብጹአን አባቶች ደስስ በሚል ሁኔታ ምክር ስለተለገሰኝ ማንም እኔን በተመለከተ በሰጠው ትንታኔ ቂም ላልይዝ ነገሩን ሁሉ እርግፍ አድርጌ ትቻለሁ!!

( ትንሽ የከበደኝ ለሰማይ ለምድር የከበዱ ብጹአን አባቶች በካሜራ ፊት ቆመው እባካችሁ ከእንደዚህ አይነት ነገር ተቆጠቡ ሲሉ እና ሲማጸኑ ሳይ ነው!!)

በነገራችን ላይ ይሄን ስራ የምሰራው ከበርካታ የህግ ባለሙያዎች ጋር ነው! በእውቀት በልምድና ቤተክርስትያንን በምንወክልበት ሁሉ የፈጣሪ እርዳታ እንዳይለየን ተባርከንም ጭምር ነው!!

ስራውን ስንሰራ አሁንም ወደፊትም ከበረከት በቀር የምንቀበለው አምስት ሳንቲም የለም!!

ተጨማሪ ያንብቡ:  ከዳባት አጅሬ ጠገዴ ሊሰራ ታቅዶ የነበረው መንገድ በአገዛዙ ከፍተኛ ባለስልጣናት ውሳኔ መታጠፉ ተገለፀ

ለኔ እስከዛሬ ከያዝኳቸው ጉዳዮች ሁሉ የምንግዜም ከባዱ እና ወሳኙ ጉዳዬ ነው!

ያው በፌስቡክ እና በዩቲዩብ ጥቆማ አልተመረጥኩምና በፌስቡክ እና በዩቲዩብ የነቀፌታ ጋጋታ የተጣለብኝን ሃላፊነት አልለቅም!!

ገና ብዙ ስራ እንሰራለን!!

አብረውኝ ባሉት ባልደረቦቼ :እና በሁሉም ጉዳይ በሚመሩን የቅዱስ ሲኖዶስ አባቶች እተማመናለሁ:እጸናለሁም!!

አንድ ነገር ግን ልለምናችሁ…

እኔን ተፋቱኝ እና ዋናው ጉዳይ ላይ (እንደዚህ ሰሞኑ ሁሉ) አተኩሩ!!

መልካም ቀን!!

1 Comment

  1. ወዳጄ ብዙ ደክመህ ሳንረዳህ ቀርተን ይሆናል ያም አበሳጭቶህ ይሆናል ይህንን መንግስት አንተ ባመንከው ልክ እኛ ለማመን እንቸገራለን ሲናገር ይዋሻል፣ቃል ሲገባ ያፈርሳል፣ሲታመን ይከዳል። ወዳጄ ጠሚኒስተሩና ካቢኔያቸው የህወአት ስራዎች ናቸው። እናንተ ይሄንን ተስፋ ይዛችሁ ስትመለሱ በተቃራኒው ሽመልስ አብዲሳና ጁዋር መሀመድ በተጻራሪው ሌላ አዋጅ አውጥተዋል። እስከዛሬ ሲፈጸም ያየነው የነሱን እንጅ የጠቅላዩን አይደለም በተመሳሳይ ሁኔታ በምርጫ 97 እንደ ዛሬው ሁሉ ምድር አንቀጥቅጥ ሰልፍ ተዘጋጅቶ ብርሀኑ ነጋን ጠርተው ጭንቅላቱን እያሻሹ ጀርባውን ቸብ ቸብ ሲያደርጉት ሰልፉን አስቀርቶት እዚህ ሁሉ ማጥ ውስጥ ገብተናል። ለሀገርህም ለሀይማኖትህም ስለሆነ የምትሰራው ብስጭት አግባብ አይደለም ትግሬዎች በዚህ የተካኑ ስለሆኑ እኛን መስለው የሚያስቀይሙህም ሊኖሩ ይችላሉ። ለማንኛውም ቢያንስ ተበሳጭተህ መልስ ባትሰጥ መልካም ነበር። እኛም ስለጨነቀን ነው ሊሰለቅጠን ያሰፈሰፈው ሀይል ቀላል አይደለም በተረፈ በርታ ጽና ካሁኑ እንዲህ መሆን መልካም አይሆንም።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share