February 11, 2023
4 mins read

አንዳንድ ሰዎች ስለትላንትናው የፍ/ቤት ትእዛዝ የሚያወሩትን አወዛጋቢ ጉዳይ በተመለከተ – ከአንዱአለም በእውቀቱ

ከአንዱአለም በእውቀቱ ፌስቡክ ገፅ የተወሰደ።

አንዳንድ ሰዎች ስለትላንትናው የፍ/ቤት ትእዛዝ የሚያወሩትን አወዛጋቢ ጉዳይ በተመለከተ ለብጹአን አባቶች ዛሬ ጠዋት ገለጻ አቀረብን።

አንተ ከያዝከው የጦር መሳሪያ እኔ የያዝኩት መስቀል ይበልጣል
አንተ ከያዝከው የጦር መሳሪያ እኔ የያዝኩት መስቀል ይበልጣል

‘ህገወጡ ቡድን የያዛቸውን ቦታዎች ለምን ይዞ እንዲቀጥል ተባለ?!’ የሚለውን ጠየቁን።

እስከ አሁን የእግድ ፋይል እንጂ(ያውም ክስ ሳይጀመር በእግድ ጉዳይ ብቻ በቀጥታ የተከፈተ የመጀመሪያው የፍ/ቤት ፋይልም ነው) ዋናው ክስ እንዳልተከፈተ :ከጉዳዩ ውስብስብነት አንጻር ክስ ለመክፈት ጊዜ ለማግኘት ሰው እንዳይሞት ሲባል ለፍርድ ቤት እግድ ጠይቀን በዚህ ጉዳይ ያሉ አከራካሪ ነገሮች እስኪጠናቀቁ ብቻ የተሰጠ ጊዜያዊ የእግድ ትእዛዝ መሆኑን :የቤተክርስትያን ንብረቶችን የማስመለስ ክስ በቀጣይ የምንከፍት መሆኑን ነገርናቸው ።

…ለአንዳንዶች ‘ኒውክለር ሳይንስ’ የሆነባቸው የእግድ እና የውሳኔ ልዩነት ብጹአን አባቶች ለመረዳት 30 ሰከንድ ነው የፈጀባቸው!!

ያስገኘነውን ውጤት በተመለከተ በመላው ብጹአን አባቶች አጥንት ድረስ የሚደርስ ምርቃት እና መባረክ ተችሮናል!!

ከዛ በተረፈ ቅድም እንደሰማችሁት አንዳንዶች እኔን እና አንዳንድ የህግ ኮሚቴ አባላትን በተመለከተ እላፊ ሄደው የሚናገሩት ለቤተክርስትያን ካላቸው ቀናኢነት እና መንፈሳዊ ቅናት የመነጨ መሆኑን በብጹአን አባቶች ደስስ በሚል ሁኔታ ምክር ስለተለገሰኝ ማንም እኔን በተመለከተ በሰጠው ትንታኔ ቂም ላልይዝ ነገሩን ሁሉ እርግፍ አድርጌ ትቻለሁ!!

( ትንሽ የከበደኝ ለሰማይ ለምድር የከበዱ ብጹአን አባቶች በካሜራ ፊት ቆመው እባካችሁ ከእንደዚህ አይነት ነገር ተቆጠቡ ሲሉ እና ሲማጸኑ ሳይ ነው!!)

በነገራችን ላይ ይሄን ስራ የምሰራው ከበርካታ የህግ ባለሙያዎች ጋር ነው! በእውቀት በልምድና ቤተክርስትያንን በምንወክልበት ሁሉ የፈጣሪ እርዳታ እንዳይለየን ተባርከንም ጭምር ነው!!

ስራውን ስንሰራ አሁንም ወደፊትም ከበረከት በቀር የምንቀበለው አምስት ሳንቲም የለም!!

ለኔ እስከዛሬ ከያዝኳቸው ጉዳዮች ሁሉ የምንግዜም ከባዱ እና ወሳኙ ጉዳዬ ነው!

ያው በፌስቡክ እና በዩቲዩብ ጥቆማ አልተመረጥኩምና በፌስቡክ እና በዩቲዩብ የነቀፌታ ጋጋታ የተጣለብኝን ሃላፊነት አልለቅም!!

ገና ብዙ ስራ እንሰራለን!!

አብረውኝ ባሉት ባልደረቦቼ :እና በሁሉም ጉዳይ በሚመሩን የቅዱስ ሲኖዶስ አባቶች እተማመናለሁ:እጸናለሁም!!

አንድ ነገር ግን ልለምናችሁ…

እኔን ተፋቱኝ እና ዋናው ጉዳይ ላይ (እንደዚህ ሰሞኑ ሁሉ) አተኩሩ!!

መልካም ቀን!!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

ጥር 2 ቀን 2017 ዓ/ም   January 10, 2025  በኢትዮጵያዊነታችሁ፡ በኦርቶዶክሳዊ እምነታችሁ፡ በአማራነታችሁ፡ በአማረኛተናጋሪነታችሁ፡ በተሰነዘረባችሁ ብትር፡ ቤተ ሰብ፡ ወዳጅ ዘመዶቻችሁን ያጣችሁ: ልጆቻችሁን የቀበራችሁ፡ አካልችሁን ያጣችሁ፡ የተሰነዘረውን ብትር በመከላከል ላይ ያላችሁ፡ያለፈቃዳችሁ በመንግሥት ተጽእኖ ወደመግደልና

በኢትዮጵያዊነታችሁ፡ በኦርቶዶክሳዊ እምነታችሁ፡ በአማራነታችሁ፡ በአማረኛ ተናጋሪነታችሁ፡ በተሰነዘረባችሁ ብትር፡

January 10, 2025
Go toTop