November 12, 2022
13 mins read

ኦነግ ሸኔ ብሎ ነገር የለም … ያለው የፀረ ኢትዮጵያ ኃይሎች ፕላን ቢ  እና ሲ ነው… – ሲና ዘ ሙሴ

ኦነግ ሸኔ

ኦነግ ሸኔ ብሎ ነገር የለም ። ያለው ሥለ ገንዘብ ብሎ ሰው የሚያርድ የአውሬ ስብስብ ነው ። ያለው በግፍ በጭካኔ እና በስርቆት ሥለሚሰበሰብ ሀብት እና ንብረት የሚጨነቅ የአውሬ መንጋ ነው ። ያለው እየተዘረፈ ሥለሚበላ ሥጋ  ብቻ የሚያሥብ ለሆድ ብቻ የሚኖር ከአውሬና ከእንስሳ ጎራ የሚመደብ ፀረ ሰው ፣ ፀረ ህብረተሰብ ፣ ፀረ አገርና ትውልድ ” በለዔ ሰብ  ” ቡድን ነው ።

ኦነግ ሸኔይህንን ፀረ ሰው እና አገር አፍራሽ ” በላዔ ሰብ እና መንጋ ቡድን ” መሐል ከተማ ሆነው ( በመላው አትዮጵያ በተለይም በኦሮሚያ ክልል ውሥጥ ሆነው ) የሚመሩትና የሚደግፉትም ትላንት ምንም የሌላቸው ዛሬ በለባንክና ባለፎቅ የሆኑ ግለሰቦች ናቸው ። እነዚህ ግለሰቦች  ከግብፅ ፕላን ቢ ጋር በመቀናጀትም  ” የአሸባሪ ተግባር በመፈፀም የኢትዮጵያን ህዝብና መንግሥት እንዳይረጋጉ ማድረግ ። ” የሚለውን ዕቅድ በማስፈፀም ላይ ናቸው   ። ትላንት በአረብ በረሐዎች አይሲስ አንገት ይቀላ ነበር ። ዛሬ ደግሞ በኦሮሞ ሥም ተደራጅቶ አንገት የሚቀላ የግብፅ ተላላኪ  አውሬ ቡድን  ፈጥረወልናል ።

ምናልባትም የሰውን  አንገት ማረድ እንዴት ቀላላ እንደሆነ የሚያሰለጥን ሤጣን በከፍተኛ ብር ክፍያ ከዚህ ኦነግ ሸኔ ተብዬ ቅጥረኛ ነፍሰ ገዳይ እና የሽብር ቡድን ጋር እንዳለም ጠርጥሩ ። ትላንት በህውሃት ቤት ነበረ ። ዛሬ ደግሞ በኦነግ ሸኔ ተብየው ቤት ሥለታም ቢላውን ከፍ አድረጎ ይዞ እብድ እብድ እየተጫወተ ነው ። ይህንን የእብድ ተግባሩን አጠናክሮ እንዲቀጥልም  ያላሰለሰ ድጋፍ የሚያደርጉለት የጥቅም ተጋሪዎቹ በመንግሥት ማዋቅር ውሥጥ የተሰገሰጉ ምናልባትም ከፍተኛ አመራራ የሆኑ ሆዳም ግለሰቦች ሊሆኑ እንደሚችሉ ህዝብ ከጠረጠረ ቆየ ። ለዚህ ዋቢ የሚሆነን ደግሞ በኃቅ ህዝብን የሚያገለግሉ የኦሮሚያ ክልል አመራሮች  በእነዚህ አውሬዎች በግፍ ና በጭካኔ  መገደላቸው ብቻ ሳይሆን ፣ አያሌ የኦሮሚያ ፖሊሶች እና ልዩ ኃይሎች ለግዳጅ መሰማራታቸው አሥቀድሞ ለአውሬው እየተነገረ በአሳዛኝ ሁኔታ በጉዞ ላይ ሳሉ በድንገተኛ ጥቃት ማለቃቸው ነው ። ይህ የሚያሥረዳን ” ኦነግ ሸኔ ” የተሰኘ ቡድን ያለመኖሩን ነው ። ያለው ከላ እስከታች በኔት ዎርክ የተደራጀ ፣ አገር አፍራሽ ቅጥረኛ ነፍሰ ገዳይ አውሬ ቡድን ነው ። ይኽ ቡድን ለዘረፋ ፣ በጭካኔ ለማረድ እና ለመግደል በጠላቶቻችን የተፈጠረ ሆኖም ሆዳም እና ህሊና ቢሥ ምሁራን ፣ ትልቅ የሚባሉ ግን ″ የትኋን አሥተሳሰብ ያላቸው  ″ ፖለቲከኞች እና ባለሥልጣናት ፣ በብርቱ የሚደግፉት በመሆኑ መሐል አገር ድረስ ዘልቆ የጭካኔ ተግባር ይፈፅማል ።ይኽንን እኩይና ኩንን ተግባር በግልፅ እና በአደባባይ በፀሐይ ብርሀን ሲፈፅምም   ሃይ የሚለው የጠፈውም በዚህ ምክንያት ነው ።  የግል ሀብታቸውን እያደራጁ፣ ዶላራቸውን በውጪ እያሳበጡ  እና እጅግ የተቀናጣ ኑሮ በሸገር እየኖሩ እንዴት ብለው ከጠላቶቻችን የሚያገኙትን ገንዘብ ከላዩ ላይ እየቆነጠሩ   በመሥጠት  ፣ ለዚህ ያበቁትን እና እነሱን ቱጃር ያደረጋቸውን የአውሬ ቡድን እንዴት ተው ! ይበቃል ! እረፍ ! ሰውን በመግደል እንደ አውሬ  መኖርህ ይብቃ   ሰው ሁን ! ይሉታል ። መጀመሪያ ራሳቸው ሰው ሳይሆኑ ሌላውን አውሬ አምሳያቸውን ወደ ሰው ለመቀየር እንዴትስ ይችላሉ ?

በነገራችን ላይ የፌደራል መንግሥቱ  በፀጥታ ኃይሉ ውሥጥ የተሰገሰጉ በመጥፎ ሱስ የተበከሉ ፣ ለሱሳቸው ሲሉ አገር ከመሸጥ ወደኋላ የማይሉ  በፀጥታ አካላቱ ውስጥ ያሉ  አባላቱን ለማጥረት ፣ ልዩ ኦፕሬሽን ወይም የማጋለጫ ውይይት ″ በጎድ ደረጃ ″ ሳይዘገይ ማካሄድ እንዳለበት አስባለሁ  ። የአገር መከላከያ ሠራዊት፣ ወታደራዊ ዲሲፕሊኑ ከብረት የጠነከረ መሆን ይገባዋልም ። እንደ ብረት የጠነከረ ዳሲፕሊን ላለው የመከላከያ ሠራዊትም ኢትዮጵያ ከማንኛውም የመንግስት ሠራተኛ  የተሻለ ደመወዝ ልትከፍለውና  ልትንከባከበውም እንደሚገባም አምናለሁ ። የአገር ሠላም ዋሥትና የመከላከያ ሠራዊቱ ፣ የፊደራል ፖሊሱ እንዲሁም በየክልሉ ያሉ ኃቀኛ ፖሊሶች እንደሆነም አበክረን መረዳት ይኖርብናል ። በእነዚህ ህግ አሥከባሪ ፣ አገርና ህዝብን ጠባቂ ተቋሞችም  ውሥጥ ያለው ″ ንቅዘት ″ እሥካልተወገደ ድረሥ የኢትዮጵያ ሠላም አሥተማማኝ አይሆንም ።

ትላንት ፣ የህውሃት ጀነራሎች የግል መኖሪያ ቪላ ብቻ  ቢሰሩ ኖሮ አይገርመንም ነበር ። የንግድ ፎቅ ሠርተው ሲያከራዩ ግን አይተናል ። ይህ ምን ማለት ነው ? ይህንን የሚሰማ በዝቅተኛው እና በመካከለኛው አመራርና በተራ ወታደርነት ያለው በደመወዙ ብቻ የሚተዳደረው ፣ ከዓመት እሥከዓመት ኑሮው ባለበት የሚረግጠው ዓባል ምን ይሰማዋል ?  በእውነቱ ወደ ታችኛው እና የበዛ መሰዋትነት ወደ ሚከፍለው ለውይይት ስትሄድ ውድ ኮትህን ወደ ርካሽ \ ጃኬት መቀየሩ ከቶ ምንም ዋጋ እንደማይኖረው መገንዘብ አለብህ ። መጀመሪያ እራስህ በእውነት ከሥግብግብነት እንደተላቀቅህ ራስህን ጠይቅ ። ሥግብግብ ሰው ህሊና ቢሥ ነው ። ማሥተዋልም ከቶም አይችልም እና ይህንን ፍራ ፡፡ …

ዛሬ ፣ ዛሬ ሥግብግቦች አና ከራስ በላይ ነፋስ ባዮች በመንግሥት ማዋቅር በከፍተኛው አመራር ውሥጥ በመብዛታቸው ነው ፣ ተራ ነፍሰ ገዳይ አውሬዎችን እንኳን ማጥፋት ያልተቻለው ። ከተማ ሲገቡ ድምፅን አጥፍቶ በመመሸግ እምሽክ ማረግ ሲቻል ፤ ” እኛ በዚህ ሥፍራ ተሰባሥበን ቁጭ እንላለን እናንተ ገብታችሁ ዝረፉ ። ” በማለት ይመስላል ወደ ወለጋ ከተሞች እየግቡ ያለፍርሃት ዘርፈው ወደ ጨካቸው የሚመለሱት ። አሥቀድሞ ይህ ከፍተኛ ባለሥልጣን ( ወታደራዊም ሆነ ሲቪል )ከአውሬዎቹ ሥንት ሚሊዮን ብር ቢቀበል ነው ፣የፀጥታ መዋቅሩን ″ አርፈህ ቁጭ በል ። ″ ብሎ ቀጭን ትዕዛዝ የሚሰጠው ?  በዚህ ዓለም እኮ  ለፅድቅ ተብሎ ዘረፋ ፣ ግድያ እና ሰው ማረድ ይከናወናል እንዴ ?! …

በዚህ ዓለም ላይ፣  ሁሉም ጦርነት ለጥቅም ሥለ ጥቅም ነው  የሚከናወነው ። ጥቅምህን ሲያሳጡህ ጦርነት ትከፍታለህ ። ያልተገባህን ሆኖም የቋመጥክበትን ጥቅም ለማግኘት ጦርነት ተከፍታለህ ወይም ታሥከፍታለህ ። እንዲህ ዓይነቱ ጠርነት ነው ፣ ዛሬ በዓለማችን እየተከናወነ ያለው  ።  በእኛ አገርም እንዲሁ ።

ኦነግ ሸኔ የሚባል የሌለ የሽፋን  ሥም ይዘው ፣ በባርነት ያልተያዘውን የኦሮሞ ማህበረሰብ ነጻ እናወጣለን በማለት አላማቸውን የማይደገፈውን ሁሉ ፣ ቋንቋ እና ጎሳ ሳያመርጡ   ጦርነት ከፍተውበት ፣ ጭካኔ በተሞላ መንገድ የሚገድሉ ፣ የአውሬ ሥብሥቦች ፣ በአገር ውሥጥ ያሉ ትሆን ፐለቲከኞችን ወደሥልጣን ለማምጣት አንደሆነ ግን መታወቅ አለበት ። እነዚህ ትሆን ፖለቲከኞች ፓርቲ መስርተው በሰላማዊ መንገድ እንቀሳቀሳለን የሚሉ አስመሳዮች ናቸው ፡፡  በውጪ   ፀረ ኢትዮጵያ ጠላቶቻችን በገንዘብ እንደሚደገፉ የታወቀ ነው ። በእርግጥ ፀረ ኢትዮጵያ ኃይሎች የቋመጡለትን ጥቅም ለማግኘት የሚችሉት ኢትዮጵያን  በማፍረሥ  ነው ። ( አንባቢ ሆይ ልብ በል ፤ እንደ ቴዎድሮስ ጸጋዬ አይነቱን ልበ እውር ፣ በገንዘብ ቀጥረው የጥላቻ ጥሩንባ ቢያስነፉ አይገርምህ ) ።

ዛሬ የኢትዮጵያ ጠላቶች ኢትዮጵያን ለማፍረስ በፕላን ቢ እየተንቀሳቀሱ ነው ። ፐላን ሲም አላቸው ፡፡ ያንን በጊዜው እገልፅዋለሁ ። ጅማሬው ግን  ሀ ተብሏል ።  ለጊዜው ዛሬ ፣ ለዕቅዶቻቸው ግብ  ያቋቋሙት ፀረ ሰው የአውሬዎች ሥብሥብ በሙሉ ኃይሉ ፣  ሌት እና ቀን  ለጥፋት ተግባር እየተንቀሳቀሰ ነው ። ይህንንም እውነት ለመገንዘብ  ከፈለክ አፍንጫህ  ሥር  ምሥረቅ እና ምዕራብ ኦሮሚያ ውስጥ የሚታረዱትን ንፁሐን ተመልከት  ።  የዚህ አሸባሪ፣ አፍራሽ እና አውዳሚ አውሬ ቡድን ሞተር  ከአዲስ አበባ እስካልጠፋ ጊዜ ድረስም የዘረኛ አክራሪዎች ፕላን ቢ እና ሲ ይቀጥላል ። …

 

2 Comments

  1. ጎበዝ ጁዋር መሀመድ አሜሪካዊ ነው የሀገሪቱ ህገ አራዊት የሁለት አገር ዜግነትን አይፈቅድም። ይህንን እያወቀ አቶ መራራ ጉዲና ዝም ብሎታል ድክመቷና ነገዷ ታውቆ በብልጽግና የተመረጠችው ሚደቅሳም አላየሁም ብላለች። በዚህ መልኩ ኢሰፓን እውቅና አልሰጥህም ብሎ ሰው ዘቅዝቆ ያሰቀለው ጁዋር መሀመድ ይህንን የፖለቲካ ወንበር መያዙ አግባብነት አለውን? ከላይ መራራ ጉዲና አቶ የተባለበት እሱ ብርሀኑ ነጋ አረጋዊ በርሄ ከአካዳሚክሱ አለም ከተፋቱ ጊዜው በመንጎዱ ነው። የነገር አተያየታቸውም መላቅጡ የጠፋ አመንክዮ የሌለው በመሆኑ ነው።

  2. የሴራና የእኩይ ፖለቲከኞች ድራማ ወንጀለኛን በተገቢ ስሙ ያለመጥራት ወይንም ሌላ ተለጣፊ ስም ማውጣት ነው:: በወቅቱ የሃገራችን ሁኔታ አሰቃቂ የሰላማዊ ህዝባችን ነፍሰጡር ሴቶችና ያልተወለዱ ህጻናትን ሳይቀር ከሆድ አውጥቶ በዘግናኝ ሁኔታ የሚጨፈጭፈው ኦነግን ሸኔ የሚል የዳቦ ስም ማውጣት ነው:: በትክክል ይህን አረመኔያዊ ስራ የሚሰራው ድሮ ከሃገራዊ የትግል ድርጂ ኢጭአት የትግል አጋሩን የገሙውን አሰፋ ጫቦን ክዶ የመሰረተው ባሮ ቱምሳ ያዋቀረው በጥላቻ የዘር ፖለቲካ የኦሮሞ ትግል በኩር ኦነግ ነው:: ኦነግ ባሮ ቱምሳ ባሌና ሃረር ለትግል በሄደ ጊዜ የራሱ የዘር የትግል አጋር የሆኑን ኦሮሞዎች ሲገድሉት ድርጅቱን እድሜ ያስቀጠለለት የባሮ ወንድም መካነኦነግ የተባለው በቅኖቹ በነቄስ ባድማ ደፋ ኦነሲሞስ ነሲብ ደፋ ጀሞ ወዘተ የተዋቀረችውን መካነኢየሱስን ለእኩይ ስራው መጠቀሚያ በጀመረበት ጸያፍ የሃይማኖትና የዘር ፖለቲካ ጋብቻ ነበር:: ዛሬ ግን ሰው የዘራውን ያጭዳል ወንጌል ተሰበከበተ የተባለው ወለጋ ከሁሉም ክልሎች የከፋ ደም የሚፈስበት መሆኑን የዚሁ የዘር ፖለቲካ አራማጅ የባሮ ቱምሳን ልጅ ያገባው ዶ/ገመችስ ደስታ ቡባ መስክሯል:: ስለዚህ ምንም ሳናምታታ አካፋን አካፋ እንበል የንዑሃን ደም አፍሳሽ የኢትዮጲያ ህልውና ተሟጋች የኢትዮጲ ኦርቶዶክስ ተዋህዶና ከዘሩ ይልቅ ኢትዮጲያውቱን የሚያስቀድመውን አማራውን ለማጥፋት መጽሃፍ በማሳተም በነተሰማ ተአ ፊታውራሪነት በሃይማኖት ሽፋን ተተናክሮ ዛሬ ይፋ የሰው ዘር ጭፍጨፋ የቀጠለው ኦነግ የኦሮሞ ነጻ አውጭ የሚሉት በእንግሊዝኛ OLF ነው

Leave a Reply

Your email address will not be published.

127489623 gettyimages 1244430199.jpg
Previous Story

ፍትህ የሌለው እርቅ አሁንም የሞተ ነው! – በላይነህ አባተ

Ephrem Madebo
Next Story

የኤፍሬም ማዴቦ ሸፍጥ፤ ያይጥ ምስክሯ ድንቢጥ (ክፍል 2) – መስፍን አረጋ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop