November 12, 2022
13 mins read

ኦነግ ሸኔ ብሎ ነገር የለም … ያለው የፀረ ኢትዮጵያ ኃይሎች ፕላን ቢ  እና ሲ ነው… – ሲና ዘ ሙሴ

ኦነግ ሸኔ ብሎ ነገር የለም ። ያለው ሥለ ገንዘብ ብሎ ሰው የሚያርድ የአውሬ ስብስብ ነው ። ያለው በግፍ በጭካኔ እና በስርቆት ሥለሚሰበሰብ ሀብት እና ንብረት የሚጨነቅ የአውሬ መንጋ ነው ። ያለው እየተዘረፈ ሥለሚበላ ሥጋ  ብቻ የሚያሥብ ለሆድ ብቻ የሚኖር ከአውሬና ከእንስሳ ጎራ የሚመደብ ፀረ ሰው ፣ ፀረ ህብረተሰብ ፣ ፀረ አገርና ትውልድ ” በለዔ ሰብ  ” ቡድን ነው ።

ኦነግ ሸኔይህንን ፀረ ሰው እና አገር አፍራሽ ” በላዔ ሰብ እና መንጋ ቡድን ” መሐል ከተማ ሆነው ( በመላው አትዮጵያ በተለይም በኦሮሚያ ክልል ውሥጥ ሆነው ) የሚመሩትና የሚደግፉትም ትላንት ምንም የሌላቸው ዛሬ በለባንክና ባለፎቅ የሆኑ ግለሰቦች ናቸው ። እነዚህ ግለሰቦች  ከግብፅ ፕላን ቢ ጋር በመቀናጀትም  ” የአሸባሪ ተግባር በመፈፀም የኢትዮጵያን ህዝብና መንግሥት እንዳይረጋጉ ማድረግ ። ” የሚለውን ዕቅድ በማስፈፀም ላይ ናቸው   ። ትላንት በአረብ በረሐዎች አይሲስ አንገት ይቀላ ነበር ። ዛሬ ደግሞ በኦሮሞ ሥም ተደራጅቶ አንገት የሚቀላ የግብፅ ተላላኪ  አውሬ ቡድን  ፈጥረወልናል ።

ምናልባትም የሰውን  አንገት ማረድ እንዴት ቀላላ እንደሆነ የሚያሰለጥን ሤጣን በከፍተኛ ብር ክፍያ ከዚህ ኦነግ ሸኔ ተብዬ ቅጥረኛ ነፍሰ ገዳይ እና የሽብር ቡድን ጋር እንዳለም ጠርጥሩ ። ትላንት በህውሃት ቤት ነበረ ። ዛሬ ደግሞ በኦነግ ሸኔ ተብየው ቤት ሥለታም ቢላውን ከፍ አድረጎ ይዞ እብድ እብድ እየተጫወተ ነው ። ይህንን የእብድ ተግባሩን አጠናክሮ እንዲቀጥልም  ያላሰለሰ ድጋፍ የሚያደርጉለት የጥቅም ተጋሪዎቹ በመንግሥት ማዋቅር ውሥጥ የተሰገሰጉ ምናልባትም ከፍተኛ አመራራ የሆኑ ሆዳም ግለሰቦች ሊሆኑ እንደሚችሉ ህዝብ ከጠረጠረ ቆየ ። ለዚህ ዋቢ የሚሆነን ደግሞ በኃቅ ህዝብን የሚያገለግሉ የኦሮሚያ ክልል አመራሮች  በእነዚህ አውሬዎች በግፍ ና በጭካኔ  መገደላቸው ብቻ ሳይሆን ፣ አያሌ የኦሮሚያ ፖሊሶች እና ልዩ ኃይሎች ለግዳጅ መሰማራታቸው አሥቀድሞ ለአውሬው እየተነገረ በአሳዛኝ ሁኔታ በጉዞ ላይ ሳሉ በድንገተኛ ጥቃት ማለቃቸው ነው ። ይህ የሚያሥረዳን ” ኦነግ ሸኔ ” የተሰኘ ቡድን ያለመኖሩን ነው ። ያለው ከላ እስከታች በኔት ዎርክ የተደራጀ ፣ አገር አፍራሽ ቅጥረኛ ነፍሰ ገዳይ አውሬ ቡድን ነው ። ይኽ ቡድን ለዘረፋ ፣ በጭካኔ ለማረድ እና ለመግደል በጠላቶቻችን የተፈጠረ ሆኖም ሆዳም እና ህሊና ቢሥ ምሁራን ፣ ትልቅ የሚባሉ ግን ″ የትኋን አሥተሳሰብ ያላቸው  ″ ፖለቲከኞች እና ባለሥልጣናት ፣ በብርቱ የሚደግፉት በመሆኑ መሐል አገር ድረስ ዘልቆ የጭካኔ ተግባር ይፈፅማል ።ይኽንን እኩይና ኩንን ተግባር በግልፅ እና በአደባባይ በፀሐይ ብርሀን ሲፈፅምም   ሃይ የሚለው የጠፈውም በዚህ ምክንያት ነው ።  የግል ሀብታቸውን እያደራጁ፣ ዶላራቸውን በውጪ እያሳበጡ  እና እጅግ የተቀናጣ ኑሮ በሸገር እየኖሩ እንዴት ብለው ከጠላቶቻችን የሚያገኙትን ገንዘብ ከላዩ ላይ እየቆነጠሩ   በመሥጠት  ፣ ለዚህ ያበቁትን እና እነሱን ቱጃር ያደረጋቸውን የአውሬ ቡድን እንዴት ተው ! ይበቃል ! እረፍ ! ሰውን በመግደል እንደ አውሬ  መኖርህ ይብቃ   ሰው ሁን ! ይሉታል ። መጀመሪያ ራሳቸው ሰው ሳይሆኑ ሌላውን አውሬ አምሳያቸውን ወደ ሰው ለመቀየር እንዴትስ ይችላሉ ?

በነገራችን ላይ የፌደራል መንግሥቱ  በፀጥታ ኃይሉ ውሥጥ የተሰገሰጉ በመጥፎ ሱስ የተበከሉ ፣ ለሱሳቸው ሲሉ አገር ከመሸጥ ወደኋላ የማይሉ  በፀጥታ አካላቱ ውስጥ ያሉ  አባላቱን ለማጥረት ፣ ልዩ ኦፕሬሽን ወይም የማጋለጫ ውይይት ″ በጎድ ደረጃ ″ ሳይዘገይ ማካሄድ እንዳለበት አስባለሁ  ። የአገር መከላከያ ሠራዊት፣ ወታደራዊ ዲሲፕሊኑ ከብረት የጠነከረ መሆን ይገባዋልም ። እንደ ብረት የጠነከረ ዳሲፕሊን ላለው የመከላከያ ሠራዊትም ኢትዮጵያ ከማንኛውም የመንግስት ሠራተኛ  የተሻለ ደመወዝ ልትከፍለውና  ልትንከባከበውም እንደሚገባም አምናለሁ ። የአገር ሠላም ዋሥትና የመከላከያ ሠራዊቱ ፣ የፊደራል ፖሊሱ እንዲሁም በየክልሉ ያሉ ኃቀኛ ፖሊሶች እንደሆነም አበክረን መረዳት ይኖርብናል ። በእነዚህ ህግ አሥከባሪ ፣ አገርና ህዝብን ጠባቂ ተቋሞችም  ውሥጥ ያለው ″ ንቅዘት ″ እሥካልተወገደ ድረሥ የኢትዮጵያ ሠላም አሥተማማኝ አይሆንም ።

ትላንት ፣ የህውሃት ጀነራሎች የግል መኖሪያ ቪላ ብቻ  ቢሰሩ ኖሮ አይገርመንም ነበር ። የንግድ ፎቅ ሠርተው ሲያከራዩ ግን አይተናል ። ይህ ምን ማለት ነው ? ይህንን የሚሰማ በዝቅተኛው እና በመካከለኛው አመራርና በተራ ወታደርነት ያለው በደመወዙ ብቻ የሚተዳደረው ፣ ከዓመት እሥከዓመት ኑሮው ባለበት የሚረግጠው ዓባል ምን ይሰማዋል ?  በእውነቱ ወደ ታችኛው እና የበዛ መሰዋትነት ወደ ሚከፍለው ለውይይት ስትሄድ ውድ ኮትህን ወደ ርካሽ \ ጃኬት መቀየሩ ከቶ ምንም ዋጋ እንደማይኖረው መገንዘብ አለብህ ። መጀመሪያ እራስህ በእውነት ከሥግብግብነት እንደተላቀቅህ ራስህን ጠይቅ ። ሥግብግብ ሰው ህሊና ቢሥ ነው ። ማሥተዋልም ከቶም አይችልም እና ይህንን ፍራ ፡፡ …

ዛሬ ፣ ዛሬ ሥግብግቦች አና ከራስ በላይ ነፋስ ባዮች በመንግሥት ማዋቅር በከፍተኛው አመራር ውሥጥ በመብዛታቸው ነው ፣ ተራ ነፍሰ ገዳይ አውሬዎችን እንኳን ማጥፋት ያልተቻለው ። ከተማ ሲገቡ ድምፅን አጥፍቶ በመመሸግ እምሽክ ማረግ ሲቻል ፤ ” እኛ በዚህ ሥፍራ ተሰባሥበን ቁጭ እንላለን እናንተ ገብታችሁ ዝረፉ ። ” በማለት ይመስላል ወደ ወለጋ ከተሞች እየግቡ ያለፍርሃት ዘርፈው ወደ ጨካቸው የሚመለሱት ። አሥቀድሞ ይህ ከፍተኛ ባለሥልጣን ( ወታደራዊም ሆነ ሲቪል )ከአውሬዎቹ ሥንት ሚሊዮን ብር ቢቀበል ነው ፣የፀጥታ መዋቅሩን ″ አርፈህ ቁጭ በል ። ″ ብሎ ቀጭን ትዕዛዝ የሚሰጠው ?  በዚህ ዓለም እኮ  ለፅድቅ ተብሎ ዘረፋ ፣ ግድያ እና ሰው ማረድ ይከናወናል እንዴ ?! …

በዚህ ዓለም ላይ፣  ሁሉም ጦርነት ለጥቅም ሥለ ጥቅም ነው  የሚከናወነው ። ጥቅምህን ሲያሳጡህ ጦርነት ትከፍታለህ ። ያልተገባህን ሆኖም የቋመጥክበትን ጥቅም ለማግኘት ጦርነት ተከፍታለህ ወይም ታሥከፍታለህ ። እንዲህ ዓይነቱ ጠርነት ነው ፣ ዛሬ በዓለማችን እየተከናወነ ያለው  ።  በእኛ አገርም እንዲሁ ።

ኦነግ ሸኔ የሚባል የሌለ የሽፋን  ሥም ይዘው ፣ በባርነት ያልተያዘውን የኦሮሞ ማህበረሰብ ነጻ እናወጣለን በማለት አላማቸውን የማይደገፈውን ሁሉ ፣ ቋንቋ እና ጎሳ ሳያመርጡ   ጦርነት ከፍተውበት ፣ ጭካኔ በተሞላ መንገድ የሚገድሉ ፣ የአውሬ ሥብሥቦች ፣ በአገር ውሥጥ ያሉ ትሆን ፐለቲከኞችን ወደሥልጣን ለማምጣት አንደሆነ ግን መታወቅ አለበት ። እነዚህ ትሆን ፖለቲከኞች ፓርቲ መስርተው በሰላማዊ መንገድ እንቀሳቀሳለን የሚሉ አስመሳዮች ናቸው ፡፡  በውጪ   ፀረ ኢትዮጵያ ጠላቶቻችን በገንዘብ እንደሚደገፉ የታወቀ ነው ። በእርግጥ ፀረ ኢትዮጵያ ኃይሎች የቋመጡለትን ጥቅም ለማግኘት የሚችሉት ኢትዮጵያን  በማፍረሥ  ነው ። ( አንባቢ ሆይ ልብ በል ፤ እንደ ቴዎድሮስ ጸጋዬ አይነቱን ልበ እውር ፣ በገንዘብ ቀጥረው የጥላቻ ጥሩንባ ቢያስነፉ አይገርምህ ) ።

ዛሬ የኢትዮጵያ ጠላቶች ኢትዮጵያን ለማፍረስ በፕላን ቢ እየተንቀሳቀሱ ነው ። ፐላን ሲም አላቸው ፡፡ ያንን በጊዜው እገልፅዋለሁ ። ጅማሬው ግን  ሀ ተብሏል ።  ለጊዜው ዛሬ ፣ ለዕቅዶቻቸው ግብ  ያቋቋሙት ፀረ ሰው የአውሬዎች ሥብሥብ በሙሉ ኃይሉ ፣  ሌት እና ቀን  ለጥፋት ተግባር እየተንቀሳቀሰ ነው ። ይህንንም እውነት ለመገንዘብ  ከፈለክ አፍንጫህ  ሥር  ምሥረቅ እና ምዕራብ ኦሮሚያ ውስጥ የሚታረዱትን ንፁሐን ተመልከት  ።  የዚህ አሸባሪ፣ አፍራሽ እና አውዳሚ አውሬ ቡድን ሞተር  ከአዲስ አበባ እስካልጠፋ ጊዜ ድረስም የዘረኛ አክራሪዎች ፕላን ቢ እና ሲ ይቀጥላል ። …

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

የኦህዴድ መራሹ ብልፅግና  መንግስት  በአማራ እና በኦሮሚያ ክልል በንጹሀን  ዜጎች ላይ እየወሰዳቸው ያሉ የነፃ እርምጃ  ግድያዎች  መንግስት ያሰበውን የፖለቲካ ግብ ያሳካለታል  ወይ ? በኔ አመለካከት እነዚህ የንፁሃን ዜጎች  የጅምላ ግድያዎች  በሁለት በኩል እንደተሳለ ቢላዎ (double edge sword) ናቸው:: ፩- መንግስት እያሰላው

 የኦህዴድ መራሹ ጅምላ ግድያዎች ስሌት (ሸንቁጥ- ከምዕራብ ካናዳ)

January 24, 2025
እነዶ/ር ደብረፅዮን እና በጠ/ሚ ዐብይ አህመድ በተሾሙት የትግራይ ጊዜያዊ መንግሥት መሪዎች እነጌታቸው ረዳ መካከል የነበረው አለመግባባት ተካርሮ ሰራዊቱን ወደውግንና አስገብቷል። የትግራይ ሐይል አዛዦች ትላንት ባወጡት መግለጫ ውግንናቸው ከእነዶ/ር ደብረፅዮን ጋር መኾኑን አስታውቀዋል።

በትግራይ የተፈጠረው ምንድነው?

January 23, 2025
የድሮ መሪዎች ያላደረጉትን ምሁር ጳጳሳቱ ያላስተዋሉትን ከፈረሰች ጎጆ ከባልቴት ቤት ገብቶ ክብሩን ዝቅ አድርጎ ውሀዋን ጠጥቶ ምግቧንም ተጋርቶ ያላለቀሰ ሰው ያንን ትይንት አይቶ ማን ይኖራል ከቶ? በዉሸት ፈገግታ ፊቱን አስመስሎ ፀሀይ የበራበት

ሰው በሰውነቱ – ከ ይቆየኝ ስሜ

Go toTop