November 5, 2022
6 mins read

ትናንት ዱቄት ያሉን ዛሬ አለት ለሚሉን !

abiy and debreጉድ ሳይሰማ መስከረም አይጠባም ሲባል እንዲሁ የአንድ ዘመን ገጠመኝ ይመስለን ነበር ፡፡ ሆኖም ላለፉት አራት አመታት ኢትዮጵያ በዘመኗ ያላየችዉ ወይም ያልገጠማት አንዲያዉም መስከረም ሳይጠባ ሳይሆን መሽቶ እስኪጠባ  ሶስት ጊዜ ጉድ መስማት ተለምዷል፡፡

ይህም ጉድ ሳይሰማ መስከረም አይጠባም የሚለዉን በኢትዮጵያ ሰማይ  ስር ሳይነጋ የተነገረ ሳይረፍድ እንደጤዛ ሲጠፋ ማየት  ዛሬ በኢትዮጵያ ጉድ ሳይሰማ መሽቶ አይነጋም ቢባል ቢያንስ እንጂ አይበዛም ፡፡

ኢህአዴግ ከስሟል ፤ የኢህአዴግ ግንባር ድርጂቶች ወይም ጉልቾች  ከስመዋል  በኢህአዴግ መተዳደሪያ ህግ -ህገ-አህአዴግ መሠረት ያልተካሄደ ምርጫ በሚል በትህነግ እና በብልፅግና መካከል በህግ የበላይነት ማስከበር እና መከበር ስም ፍጥጫ ዉስጥ ተገባ ፡፡ በዚህም በሽብርተኝነት የተመዘገበዉ ትህነግ ወደ ጦር አምጣ ህልም ገባ፡፡

የኢትዮጵያ ህዝብ  የርኩስ መዉጊያ በማድረግ በተለይም በብዙኃኑ የዓማራ ህዝብ ላይ የመጀመሪያ እና የመጨረሻ የትህነግ  ጠላት ሆኖ ለዘመናት የሚፈረጀዉ እና የመከራ ቀንበር ተሸካሚ ሆኖ እንዲቀጥል ሆኗል፡፡

ለግማሽ ክ/ዘመናት ኢትዮጵያን ለማፍረስ እና የዓማራ ህዝብ በኢትዮጵያዊነት የደረሰበትን ዕንግልት ፣ስደት እና ሞት ዕልባት ባልተሰጠበት የሞተዉን ትቶ የገደለዉን አንስቶ ምን አይነት ዘላቂ መፍትሄ ሊያስገኝ አይችልም ፡፡

ለኢትዮጵያ ብሄራዊ አንድነት ፣ሉዓላዊነት እና የኢትዮጵያዉን  በተለይም ኢትዮጵያን እንደ ድሪቶ ለመቀራመት ለረጂም ዓመታት ለሚያሴሩት አፍራሽ ኃይሎች  የማይታኘክ  አጥንት የሆነዉን የዓማራ ህዝብ ተሳትፎ አለመኖር ከዕዉነትነቱ እና ገቢራዊነቱ አጠያያቂ ነዉ ፡፡

በመላ አገሪቱ በኗሪነቱ እና በዜግነቱ ለዘመናት በግፍ  የተገፋዉ የዓማራ ህዝብ ዳግም በነዚህ ሁለት መሰረታዊ የዜግነት መብቶች የአመታት የመከራ ጅረት በሚወርዱበት ሆኖ ሳለ ዛሬም ጥቃቱን እና ሞቱን በማቅለል ዛሬም ለዳግም በደል የሚዳርግ ዳር ዳርታ ነዉ ፡፡

የበነነ ዱቄት አለት ከሆነ  የተታደፈነ ዕሳት እንደነበር ከዓመታት በፊት የተባለዉ የበነነ ዱቄት መባሉ ስህተት እና ዳግም ታሪካዊ ክስተት ነዉ ፡፡

ኢትዮጵያዉያን በተለይም ብዙኃን ዓማራ ቀድሞም በፀረ-ኢትዮጵያ አፍራሽ ኃይሎች ከመቀሌ አስከ ቦሌ በግንባር ቀደም ጠላት በማድረግ ኢትዮጵያን ለማፍረስ ዓማራን በደም እና በአጥነቱ መስርቶ ፣በጥበብ አስማምቶ  ፣ በህይወት መስዋዕትነት አቅንቶ ዕትብቱ በተቀበረባት እናት አገር ኢትዮጵያ ባይተዋር፣ ሟች እና ስደተኛ ሆኖ በሚገኝበት እንዲሁም የህልዉና እና የሉዓላዊነት ትግል እያደረገ ባለበት ዱቄት አለት አድርጎ ዕሳቱን አመድ በማድረግ ዕዉነተኛ እና ዘላቂ ብሄራዊ አንድነት እና ሉዓላዊነት ይጠበቃል ማለት ዘበት ነዉ ፡፡

ትናንት ዱቄት ያሉን ዛሬ አለት ለሚሉን እንዴት መተማመን ሊኖር እንደሚችል ማሳያ ባይኖርም ገዳይ ከሟች ጋር ባልተደረገ ስምምነት እና ዕርቅ ብሄራዊ መግባባት ይሰፍናል ማለት አሽሙር ነዉ  ፡፡

በኢትዮጵያ ታሪክ ከፍተኛ ብሄራዊ ክህደት እና ወንጀል የፈፀሙት ብሄራዊ እና ታሪካዊ ጠላቶች ከመጠየቅ እና ከመከሰስ ይልቅ ባለፍርድ ማድረግ ሟቹን እና ተበዳዩን ብዙኃን ኢትዮጵያዉያንን እና ኢትዮጵያን መርሳት ብሎም ሁሉም ለአገራቸዉ እና ለህዝባዉ ሉዓላዊነት እና ህልዉና የሚተጉት በስደት ፣ በሞት እና በዕስራት በሚማቀቁባት አገር እነኝህን አካላት የሚያሳትፍ ዕርቅ ሳይኖር የሚታለፍ ቢሆን ይህ ልባዊ ዕርቅ ሳይሆን የትዉልድ የሠላም እና አብሮ መኖር ጠንቅ እንዳይሆን ሁሉም ይመለከታኛል ባይ ልብ ሊለዉ ይገባል ፡፡

አንድነት ኃይል ነዉ !

Allen Amber!

https://youtu.be/ddmS6haUh2g

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop