ሰባተኛው ንጉስ፣ እባክህ ወደ ጠንቋይ ሂድና የቀረህን እድሜ ይንገርህ – ደረጀ አያኖ

“አትነሳም ወይ! አትነሳም ወይ! የፈሰሰው ደም ያንተ አይደለም ወይ?”

አዎን፣ በትክክል። ያንተው ነው።

ሰባተኛው ንጉስ፣ እባክህ ወደ ጠንቋይ ሂድና የቀረህን እድሜ ይንገርህ። ጭንቀቱ እንዳይግርድልህ ብዬ ነው።

አማራን ከኦሮምያ የማፅዳት ዘመቻ

አማራ በላው፣ ከአራዊት የባሰው ዘግናኙ በአብይ አህመድ የሚመራው ብልፅግና፣ እስካሁን ታይቶና ተሰምቶ በማይታወቅ ደርጃ፣ በከፍተኛ በተደራጀና በተቀናጀ ህኔታ፣ ከዛሬ ሶስት ቀናት በፊት (ቅዳሜ ጁን 18) እስከ አሁን ድረስ ከአንድ ሺህ አምስት መቶ የሚበልጡ አማራዎች፣ ከአውሬ በባሰ ጭካኔ ህፃን፣ ልጅ፣ ሴትና ሽማግሌ ሳይለይ በገፍ ጨፍጭፏል። ኗሪዎችና የአይን እማኞች እንደሚሉት ከሆነ ለብዙ ጊዜ አገራቸውን ለቀው እንዲሄዱ በአካባቢው አባገዳዎች፣ ሚሊሽያዎች፣ የቅበሌና የወረዳ አመራሮች በተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው ነበር። መንግሥት ይጠብቀናል ብለው አርፈው የተቀመቱት እነዚህ አማሮች፣ የትፀጥታ ሃይሉ በእቅዳቸው መሰረት ቦታውን በመልቀቅ፣ የኦነግ ሸኔ ሰራዊትና የአካባቢው ሚሊሽያ፣ መውጭያና መግቢያውን ዘግቶ ጭፍጨፋውን እንዲያካሂድ ተደረገ። በጣም የሚደንቀውና ግድያው ለቀናት የተቀናጀ ለመሆኑ የሚያሳየው ግን፣ ይህንንው ጨፍጫፊ አረመኔ “አራዊቱን ኦነግ ሸኔ” ከኋላ ኋላ እየተከተለ፣ የሚጨፈጭፋቸው አማሮች ንብረት ላይ መረባረቡ ነው። በእውነት ይህ ሕዝብ፣ አብሮ የበላውንና የተዋለደውን ጎረቤት በዚክ መንገድ ያስፈጀ፣ የወለጋ ኦሮሞ ነው? ወይንስ ከሌላ ሐገር የመጣ “የሰው ምስል የለበሰ” ሰው በላ አራዊት? ይስደነግጣል።

ወገኔ ሆይ! አማራ በላው የኦህዴድ ብልፅግና መች ይህ በቃውና? ጆሮ ያለህ ስማ። ከ50 ሚልዮን ሕዝብ በላይ ያለው አማራ፣ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሀዘኑን እንኳን እንዳይገልፅ ታፍኗል። አማራን እንወክላለን የሚሉት የኦህዴድ ብልፅግና የሾማቸው የብአዴን ተላላኪዎች አሳፍረውናል። አንገታችንንም አስደፍተውናል። ከጣት ያማይበልጡት የአማራ የቁርጥ ልጆች፣ አብኖች ግን አኩርተውናል።

አስተባባዮቹ የኦህዴድ ብልፅግና የሶሻል ሚድያ ቅጥረኞችና ህልውና ቢስ ወዶ ገባዎች።

ይህ ሁሉ የአማራ ሕዝብ በአስከፊ ህኔታ ሲጨፈጨፍ፣ ሕዝብ እውነቱን እንዳያውቅ ለማወናበድ  የኦህዴድ ብልፅግና የሶሻል ሚድያ ቅጥረኞችና ህልውና ቢሶቹ ወዶ ገባዎች፣ ከምቅፅፈት ሀቁን መሸርሸርና መመንዘሩን ተያይዘውታል። ቅጥረኞቹ እንኳን እሺ፣ የሚገርመው ግን በሕዝብ እስፖንሰርሽፕ የሶሻል ሚድያ ከፍተው “ሕዝብን የሚደልሉ” ነገር ግን ከበስተኋላ ደግሞ የኦህዴድ ብልፅግና “ወዶ ገባዎች” የሆኑት ናቸው። እነዚህ ሆዳሞች የሕዝብ አመለካከት ለመቀየርና ሌል አጀንዳ ለማስያዝ “ይህ አይነት ግድያም አሚሪካ ወስጥ ይታያል፣ አዲስ ነገር አይደለም”፣ “ዶክተር አብይ እንደዚህ ማለታቸው አይደለም!”፣ “እሳቸው ምን ያድርጉ ከኋላ ያሉት ናቸው” ይሉናል። በሺህ አማራዎች ሲጨፈጨፉ፣ በሕዝብ ሃብት ተቋቁሞ የህዝብ ደሞዝተኛ የሆነው የመንግሥት የዜና ተቋም ደግሞ፣ በኦህዴድ ብልፅግና ተለጉሞ “ፀጥ፣ እረጭ” የበል እንጂ፣ ልጓሙ ለቀቅ ሲልለት ደግሞ “መንግሥት ሸኔን ላንዴም ለመጨረሻም ጊዜ ደመሰሰ” ይለናል። መነገር የነበረበት ዜና ግን “ሸኔ  ለሚቀጥለው ጭፍጨፋ በይበልጥ በኦህዴድ ብልፅግናና በዳውድ ኢብሳ እየተደራጀ ነው” የሚል ነበር። ከ15 ሺህ የበለጠ ፋኖ ታፍኖና ብዙዎችም ተገድለው እያሉ፣ እነዚሁ ለሆዳቸው ያደሩ (አንዳንዶቹም አማራ ነን የሚሉ ልበ ቢሶችና አሳፋሪዎች) “መንግሥት ያሰረው በፋኖ ሥም የሚዘርፉት ነው” እያሉ አፋኙን የኦህዴድ ብልፅግናን ፕሮፓጋንዳ ከፊት ሆነው ያስተጋባሉ። ሁላችሁንም፣ በየአውሮፓም ይሁን በሰሜን አሜሪካ የተሰገሰጋችሁ ወዶ ገባዎች ሕዝቡ ያውቃችሁዋል። ሌሎቹ እንደሚያደርጉት በቶሎ መደባችሁን ለዩ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ኦሮማይ ትግሉ በሚቻለውና በማንኛውም መንገድ!

አስመሳይ በሀይማኖት ሥም ሕዝብ የምታጋጩ የኦህዴድ ብልፅግና ካድሬውች

የታሉ እነዚያ ጎንደር ላይ 20 አስላሞች ሞቱብን በማለት፣ በመብረቃዊ ፍጥነት ወጥተው ቤተክርስትያን ያቃጠሉ? ንፁሃንን የገደሉ? የት ሄዱ? ለአንዲት የሙስሊም ህይወትም እንኳን ጠበቃ ነኝ የሚለው ጀዋር መሐመድ? የት ሄደ? በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ እስላም አማራዎች በየቤታቸው፣ በየጓሯቸውና በየመስጊዱ እንደ ጫጩት ዶሮ ሲጨፈጨፉ፣ ያልተወለዱትን ህፃናት ከእናታቸው ማህፀን እያወጡ ሲዘለዘሉ፣ ትናንሽ ህፃናትን ደግሞ በተርታ አሰልፈው እንደዶሮ ሲያረዱ፣ አሮጊትና ሽማግሌው ሲሰይፉ፣ የት ጠፋችሁ? እውነትስ ለእስላም ህይወት ታዝናላችሁን? ወይንስ የአማራ እስላም ህይወት “ዋጋ ቢስ” ነው? ይህ በግልፅ የሚያሳየው እናንተ “የኦህዴድ ብልፅግና ድብቅ የሸኔ ሰራዊት” ለመሆናችሁ ነው። የተሰጣችሁን የመከፋፈልና የማበጣበጥ አጀንዳ ለማስፈፀም እንጂ “ለሙስሊሙ” ህይወት ቅንጣት ያህልም ደንታ የላችሁም። አሁን ህዝቡም ይህንን አውቆታል። ወለጋ የተጨፈጨፈው እስላም “በአማራነቱ” ብቻ ነው። እናንተ እንደዚህ እየተጨፈጨፈ ባለበት ጊዜ የረሳችሁትም “በአማራነቱ” ብቻ ነው። ችግሩ “የዘር በሽታ” ነው። በጠና ታማችኋል። በቶሎ ካልታከማችሁት፣ ይህ በሽታ “ይዟችሁ ይሄዳል”። አትጠራጠሩ። ትክክለኛው፣ በዘር በሽታ ያልተለከፈው ሙስሊም ግን አሁንም ከወገኖቹ ጎን ቆሟል።

ከወለጋ በመቀጠል። ዝግጀቱ እያለቀ ነው። ለአማራው ብቻ አይደለም፣ ሁልህም ተደግሶልሃል።

የኦህዴድ ብልፅግና፣ ለዓመታት ያስብበት እንጂ በተግባር የዘር ማፅዳት ዝግጅቱን ከጀመረ ዛሬ አራት ዓመቱ ነው። ተራ በተራ፣ ደረጃ በደረጃ እየተከናወነ ነው። አሁን ግን በጣም አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል። የተግባር ጅማሬው ከተረሳችሁ (ሌሎቹን የአቢቹንና የሸመልስ አብዲሳን የኦቢኤን ቪድዮ ኢንተርቪዎችን ሳልጠቅስ) ፍንጭ ልስጣችሁ። ወደ አራት ዓመታት ወደ ኋላ መለስ ብዬ (ኦክቶበር 2018)። ታስታወሳላችሁ ቀይ ለባሽ ወታደሮች አቤቱታ ለማቅረብ ቤተመንግሥት የሄዱ ጊዜ (አቢቹ ሊገለብጡኝ ነበር ብሎ በማግስቱ ዋሸ እንጂ)? ሁኔታው ከበረደ ባኋላ፣ በቲለቪዝን አብይ አህመድ፣ “ወታደሮቹ እኔን ለማጥቃት የመጡ መስሏቸው፣ የቡራዩ ወጣቶች ግልብጥ ብሎ ለመምጣት ተዘጋጅተው” ነበር ብሏል። እኔን ለማጥቃት የሚከጅል ቢኖር “በኦህዴዱ የብልፅግና ሚሊሽያ ዙርያውን ተከቧል” ማለቱ ነው። ይህ አብይ አህመድ የጠራው የቡራዩ ስብስብ ከጥቂት ቀናት በፊት በቡራዩ የዘር ማፅዳት ዘመቻ (በተለይም በጎሙ ሕብረተሰብ ላይ) ሲያኬሂድ የነበረ ጨፍጫፊ ቡድን ነው። ከአራት ዓመታት በኋላ፣ ዛሬ ይህ ገዳይ ቡድን በምን አቋም ላይ እንዳለ መገመት አያዳግትም። ከአንዴም አልፎ ወደ አዲስ አበባ እንብርት ድረስ ገብቶ ጥቃት ለማድረስ ሞካክልሯል። የመከተውም የአዲስ አበባ ወጣት ነበር። አሁን ግን ይህ ወጣት በየመንደሩ በታጠቀ ሃይል ተከቧል። የየመደሩ የታጠቀ ሃይል ማን እደሆነ ጠጋ ብለህ አነጋግር። ወገኔ ሆይ ተከበሃል።

ዛሬ አማራዎች እንደዶሮ ሲታረዱ “እኔን ምን አገባኝ” ብለህ አንገትህን ድፍተህ በየቤትህ የተቀመጥክ፣ በየክልሉ ሀገሬ ነው ብለህ በዜኝትህ ኮርተህ የምትኖር የጉራጌ፣ የሃድያ፣ የሲዳማ፣ የሱማሌ፣ የአፋር፣ የወላይታ፣ የትግሬ፣ ወዘተ ብሔርተኛ ሁሉ፣ ነገ ያንተ ተራ መሆኑን አዘንጋ። በተለይም “የኔነትና የባለቤትነት” ከበሮ እየተደለቀባትና በተረኞች እየተቀረማመተች ባለችው “አዲስ አባባ” የምትኖር የማንኛውም ብሄር ተወላጅ፣ የተረኛውን የኦህዴድ ብሔር ሳይጨምር፣ ወዮልህ። አሁን ወለጋ ላይ የደረሰው አረመኔያዊ ጭፍጨፋ በሺህ ደረጃ ከፍ ብሎ የከሰትብሃል። ተዘጋጅ። ከሌሎች ይብሄር ተወላጅች አንድነት ፍጠር። አለበለዚይ ለየብቻ አድርገው ይርዱሃል። አያ ጅቦ ሶስት ትላልቅ በሬዎች ላይ “ሁለት ለአንድ” እያሳደመች አንዱን፣ “አንዱን አንዱላይ” ደግሞ እያሳደመች የቀሩትን ሁለቱን በሬዎች የበላችው ምሳሌ ይደርስብሃል። የኦህዴድ ብልፅግና ግልፅ ነው። ዞር ዞር ብለህ አካባቢህን ተመልከት። ሕዝብ ሆይ ነብሰ በላ የኦህዴድ ብልፅግና ሰራዊት ዙርያህን ከቦሃል። ዛሬው ኑ ነፍስህን አድን። “ነግ ለኔ” ብለህ ተዘጋጅ። ጭፍጨፋውን አውግዝ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የሻምበል ፍቅረሥላሴ ወግደረስ አሳሳች መረጃዎችና የተምታታ አስተያየት

ጆሮ ያለው ይስማ፣ የመጨረሻው ሰዓት ላይ ተዳርሰናል።  

ሕዝቤ ሆይ! አላወከውም እንጂ ተከበሃል። ሰው በላው ዳውድ ኢብሳ በኤርትራ ያቋቋመውና አሁን አዲስ አበባ ተቀምጦ የሚመራው፣ የአቢይ አህመድ የኦህዴድ ብልፅግና ደግሞ ከነትጥቁ ከኤርትራ ተቀብሎ በተሟላ የሚሊቴሪ አቋም  ያደራጀው አረመኔ፣ በማህፀን የተቀመጠን ሽልና ጡት ጠብተው ያልጠገቡ ህጻናትን ከረሜላ እንድሚሰጥ አሰልፎ በአሰቃቂ ሁኔታ አርዷል። አንበሳና ነብርን የሚያክል የዱር እንሰሳ እንኳን፣ የሚዳቆ ግልገል ሲያጋጥመው እንኳን ሊበላ ቀርቶ ከሌላ አራዊት ለማዳን ይከላከላል። ይህ የኦህዴድ ብልፅግናና የዳውድ ኢብሳ “ኦንግ ሸኔ” ግን፣ ልብ የሌለው የሰው ሥጋ የለበሰ እንጂ የአራዊት ስብእና የተላበሰና የተረገመ ፍጡር ነው። ይህ አካል ከሰው መፈጠሩም ያጠራጥራል።

ሕዝቤ ሆይ! አላወከውም እንጂ ተከበሃል። ትላንትና ይህ የኦህዴድ ብልፅግናና የዳውድ ኢብሳ “ኦንግ ሸኔ” በአጣዬ፣ በከሚሴ፣ በቤንሻንጉልና አሁንም በሚያርድበት ወለጋ የአማራን ህዝብ በተደጋጋሚ ፈጅቷል። ለሦስት ቀናት አጣዬና ከሚሴን ሲያወድም አብይ አህመድና የኦህዴድ ብልፅግና የሎጂስቲክና የመሳርያ አቅርቦት ከመርዳት በስተቀር ሕዝቡ “የመግሥት ያለህ! ድረሱልኝ!” ሲል፣ ጆሮ ዳባ ሆነዋል። አሁን ወለጋን ከአማራ ካፀዳ በኋላ፣ ሕዝቤ ሆይ! አላወከውም እንጂ ወዳንተ ይመጣል። ሰላማዊውውን ፋኖ ከጉያህ ፈልቅቆ ለማጥፋት የፈለገውም፣ እንደዛሬው (እንደወለጋ) በቀላሉ ሊያርድህና ሊያጠፋህ አስቦ ነው። አንተ የዋህ በመሆንህ፣ ግልፅ የሆነውን የኦህዴድ ብልፅግና አጀንዳ በግብዝህነትና በቸልተኝነት ነቀህ አሳለፍከው። ነገር ግን ነገ ያንተ ተራ ነው። ዙሪያህን ተከበሃል። ተነስ። ተነስ። ተነስ። እንደተኛህ አትታረድ።

ወደ ሰሜን አሜሪካ በኦህዴድ ብልፅግና በአማላጅነት የተላከው፣ የእንግዴ ልጁ ብአዴን።  

ይህን “አማራን ከኦሮምያ የማፅዳት” ዘመቻ ከግቡ ለማድረስ በቅንጅት የሚመሩት “ሿሚው” የኦህዴድ ብልጽግናና፣ “ተሿሚው” ብአዴን፣ ከወለጋው ጭፍጨፉ ጥቁት ቀናት ቀደም ብሎ፣ ወደ ሰሜን አሜሪካ ፊታቸውን አዙረው፣ ዳያስፖራውን “እባካችሁ ከፋኖ ጋር ጡት አጣቡን፣ ካመፁት ፋኖዎች ጋር ቁጭ ብለን እንደራደር” በማለት ተማፅኖ አቅርበው ነበር። ወይ ጉድ፣ በሹመትና በጥቅም መግዛት ያቃታቸውን ፍኖ፣ በአማላጅ ለማፈን ማሰባቸው “የማን ልጆች ቢሆኑ ነው” ይስብላል። መልሱ ቀላል ነው። በሰላም ሥም ወንድሞቹን በተኙበት ያረደው “የወያኔ ልጆች”።

ታድያ፣ በዚህ በበይነመረብ በተካሄደው ስብሰባ ላይ (ዝም ብለን ጥሪ እንበለው አጀንዳው ቀድም ብሎ ያልታወቀ ስለሆነ)፣ በተላላኪው ብአዴን በተደርገ ተማፅኖ፣ አይነደርቁ የአብይ አህመድ የኦህዴድ ብልፅግና “የለመደች ጦጣ ሁልጊዜ ሸምጣጣ” እንደሚባለው፣ ልመናውን ያቀረበው ለነዚሁ “ኢትዮጵያን ለማዳን” በሚል እሳቤ ቀንና ማታ በዓለም መድረክ ላይ ሲሟገቱ ከነበሩትና በጣት የሚቆጠሩ የሲቪክ ዳያስፖራ ድርጅት መሪዎችና የ#NoMore አዝማቾች ነበር። የበይነመረቡንም ቅጂ ይዘንዋል።

ይህ “ኢትዮጵያን ለማዳን” የሚለው የዳያስፖራው እሳቤ፣ ህልውናውን ለማስቀጠልና በምን ያህል የሀገርና የውጭ ሀገር ፕሮፓጋንዳውን ለማጠናከር እንደጠቀመው ጠንቅቆ የተረዳው “አማራ ጠሉ” የኦህዴድ ብልፅግናና “ተላላኪው” ብአዴን፣ አሁን ደግሞ ከምድር ገፅ ለማጥፋት የሚፈልገውን ፍኖ ለማጥመድና ለመብላት እንዲያመቸው፣ አንቴናውን ወደ ሰሜን አሜሪካ ድረስ ዘርግቶ ዳያስፖራውን “አማልዱኝ ከፋኖ ጋር አደራድሩኝ” እያለ ብቅ ብሏል። “የሌባ አይነደረቅ መልሶ ልብ ያደርቅ”

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሃበሻው ዶክተርና ልጁ - በአሜሪካ (ከኢየሩሳሌም አረአያ)

ከንግዲህ በኋላ “ኢትዮጵያን ለማዳን” በሚል እሳቤ፣ ዳያስፖራው የኦህዴድ ብልፅግና የፋሽስትና የአምባገነን መንግሥት እንደማይደግፍ አስረግጦ አስረድቷል። ለምን ቢሉ እንደዚህ ነው።

አብይ አህመድ የተባልክ የኦህዴድ ብልፅግና መሪ፣ እራስህን “ሰባተኛው ንጉስ” ብለህ የሰየምክ ፍጡር፣ ማወቅ የሚገባህ፣ በታሪክ ዳያስፖራው አንተ መድርኩ ላይ ስትወጣ በነቂስ ወጥቶ ካዳር እዳር የደገፈህና በአሁኑ ሰዓት ደግሞ እንደ አንተ ያፈረበት፣ ያዘነበትና የተዋረደበት የኢትዮጵያ መሪና መንግሥት የለም። ጭካኔህ፣ ሽንገላህ፣ ውሸትህና ክህደትህ እንኳን በኢትዮጵያ በዓለም እንኳን ተወዳዳሪ የለውም።

ጭካኔህ። በአማራ ላይ ያለው ያንተ ጭካኔ ጠርዝ ያጣ ነው። ለዓራት አመታት አማራ በማንነቱ በመቶዎች ስታረድና ሲጨፈጨፍ፣ እንደ ሰው እንኳን ባታዝን፣ እንደ ሐገር መሪ ህዝብህን ለማስተዛዘን ሞራሉም ሰብአዊነቱም የጎደለህ ነህ። እናትህና ባለቤትህ አማራዎች ናቸው ይባላል። ባንተ ደም ውስጥ ግን አንድ ሚሊግራም የአማራ ደም አለ ብዬ አላስብም። የተሰየፈው ሽል ከባለቤትህ ሆድ ተቅዶ ቢሆን ኖሮ፣ ተሰልፈው የተቆራረጡት የራስህ ልጆች ቢሆኑ ኖሮ፣ ሰምተህ እዳልሰማ፣ ነጭ ልብስ ለብሰህ፣ ችግኝ ተከላ ትሄድ ነበር? ካንዴም ብዙ ጊዜ። እንደዚህ አይነት ጨካኝ ንጉስ ሐገራችን በታሪኳ አይታም ሰምታም አታውቅም።

ሽንገላህ። የኢትዮጵያን ሥም ደጋግመህ ትጠራለህ፣ በተግባር ግን አይታይም። ሸንጋይ በመሆንህ እውነተኛው የኢትዮጵያዊ ባህሪና ታሪክ ያሳምምሃል። ከስልሳ ሚልዮን በላይ የሚጠጋው ዮኦርቶዶክ እምነት ተከታይ ለአመታት የሚጠቀመውን የአርጓዴ ቢጫ ቀይ ሰንደቅ ስታየው ያምሃል። ወደ መንበር ከመጣህ ይህን ባንዲራ የያዘ፣ የለበሰ፣ የሰቀለ፣ እያሳደድክ ታስራለህ ወይም ትገድላለህ። በሌላ በኩል ደግሞ እውነተኛው የኢትዮጵያ ታሪክ ያምሃል። የቅኝ ገዥዎችን ክንድ አድቅቆ የአፍሪካ ኩራት የሆነውን ሚኒልክ፣ ዛሬ ያንተ እግር በአጋጣሚ ሆኖ ቤተ መንግሥቱን በመርገጡ፣ የአድዋ አያቶቹን ድል ለማክበር የወጣውን ወጣት በሙሉ “የንጉሱንና የቴጌዋን” ምስል የየዘ ካናቴራና አልባሳት በመልበሳቸው፣ የአዲስ አበባ ወጣቶችን በከንቲባህ በኩል ታስደበድባለህም ታሳስራልህም። አዎን ተልዕኮህ ኢትዮጵያን በኦህዴድ መልክ ጠፍጥፎ ለመሥራት እንጂ ሰፊው የኢትዮጵያ ሕዝብ እንደሚፈልገው እንዳልሆነ እናውቃለን። አትሸንግለን።

ክህደትህ። ከመጥፋት ያዳነህን ፋኖንና በየበረሃውና በየዱር በገደሉ የተዋደቀልህን የአማራ ልዩ ሃይል በአደባባይ ክደህ ብሺህ የሚቆጠሩትን ከርቸሌ አውርደሃል። ያልያዝካቸውን ለመጨፍጨፍ ደግሞ ዳያስፖራውን በሆዳም ተላላኪዎችህ በኩል ሙከራህን ቀጥለሃል። አይሳካም። ከአሁን በኋላ ዳያስፖራው አይሸወድም። አጀንዳህን የሚያመጡትንም፣ የሚይዙትንም ዳያስፖራዎች በደንብ እናውቃቸዋለን። እንደ አንተ የዘረኝነትና የተረኝነት በሽታ። ይህ ጭካኔህ፣ ሽንገላህ፣ ውሸትህና ክህደትህ እስኪያበቃና ከህዝባችን ላይ የተከሰተው የዘረኝነትና የተረኛነት በሽታ እርስኪያበቃ ድረስ እንታገልሃለን።

የተሸከመህ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንደምታስበው ሞኝ አይደለም። ሆዱ እየሟሸሸ መጥቷል። እርካብህም አልጠበቀም፣ ኮርቻውም እየላላ ነውወይ ከወጣህበት ኮርቻ ትወድቃለህ፣ ካልሆነም የሕዝብ አመፅ ያስደነበረው ፈረስ ወደ ገደል ይከትሃል። አትጠራጠር። የሰፊው ሕዝብ አመፅ ከነበልባልም ይፋጃል። ማንኛውንም ፍሽስታዊና አምባገነናዊ መሪ ከርብቷል። ሰባተኛው ንጉስ፣ እባክህ ወደ ጠንቋይ ሂድና የቀረህን እድሜ ይንገርህ። ጭንቀቱ እንዳይግልህ ብዬ ነው።

 

ደረጀ አያኖ

1 Comment

  1. Abiy Ahmed’s term “the 7tth king” is the most insidious propaganda that should have warned people what his core value and mission regarding the Ethiopian nation is. Ethiopia had at least 240 documented kings and queens before Abiy Ahmed was even born. When he started the propaganda of “the 7th Kng”, it should have alerted people that he subscribes to the OLFite belief that Menilik and Taitu were Adam and Eve, respectively – that human history started at that point. Today’s genocide in Oromia is anchored in this misrepresentation of the history of mankind and the history of Ethiopia. He is neither the 7th king nor the first Oromo prime minster of Ethiopia. When his handlers propagated this falsity during his coronation, they did it intentionally. Abiy Ahmed Ali is not the first Oromo head of state, he is not the first Oromo prime minster and he is not the 7th king.

    These lies do a disservice to the history of the Oromo people in particular and the people of Ethiopia in general.

    We should stick to the truth. If Abiy Ahmed Ali wants distinction, there is enough to distinguish him (not counting the scale of his genocide and destruction). For example, he is Ethiopia’s first Muslim Head of State (if we do not count Ahmed Gragn). Or using his own admission, he is Ethiopia’s first fake protestant head of state.

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share