ባዶ ሆነዉ በባዶ የሚነግዱትን መስማት ከሰለቸን ባጀን

 ባዶነት ሰለቸን !

288358186 5211569042256804 2092752397205846827 nሁሉም የመጣዉ ሁሉ በአገር እና ህዝብ ስም ሲምል ሲገዘት ባዶ ካዝና ፣ ባዶ ዲሞክራሲ ፣ ባዶ ሰባዊ መብት አየያዝ ……. ይላል፡፡

ይቀጥል እና ራሱን አልፋ እና ኦሜጋ በማድረግ ብቸኛዉ የአገር እና ህዝብ አለኝታ ራሱ ብቻዉን የሠላም ፣ ዕድገት እና አንድነት ምሰሶ ማድረግ ይዳደዋል ፡፡

ይህም የአምልኩኝ ዳር ዳርታ መሆኑ ነዉ ፡፡ ራሱ እና ግብረ አበሮች የሚያደርጉት ሁሉ ትክክል እና የተቀደሰ ነዉ ብሎ ከማመኑ የተነሳ ጥዋት ያለዉን በረፋድ ለመካድ የለዉጥ አካል አድርጎ የለዉጥ ሀዋርያ መሆኑን እዩልኝ ስሙልኝ ይላል ፡፡

በህዘብ ስም በህዝብ ትከሻ እንደመዥገር ተጣብቀዉ  አገር እና ህዝብ ሲያደሙ ፣ ሲያወድሙ እና ሲያቆስሉ የሚዉሉትን የዕድገት እና ብልጽግና ደቀመዝሙር ማድረግ  ከባዶነት  ይሻላል ብሎ ጆሮ ዳባ ልበስ በባዶ ለባዶ እንድንኖር እና ሳንኖር እየሞትን  መኖርን በባዶ ተለማመድነዉ ፡፡

ይባስ ተብሎ ከሰሞኑ ዞትር ለአለፉት ዓመታት እንደሚሆነዉ በህዝብ ላይ  በማንነት እና በአመለካከት ልዩነት እየተደረገ ባለዉ የዘር ፍጂት ስለሞቱ  የህዝብ ወገኖች እና ዜጎች የህሊና ፀሎት ለማድረግ ፣ ቁጥራቸዉን ለማወቅ እና በአገር ባህል ፣ወግ እና ዕምነት ቀብር ለማድረግ ፈቃደኛ እና ኃላፊነት የሚወስድ አካል ለማግኘት አለመቻሉ በባዶ መኖር እና በባዶ መጀመር አባዜ እንደህዝብ ልማድ ሆኗል ፡፡

ለመሆኑ  በማንነት ላይ ጥቃት ፣ ሞት ፣ ስደት እና የመሳሰሉት የጅምላ የወንጀል ድርጊቶች የአገር አንድነት እና ሉዓላዊነት ለማናጋት ሆኖ ተብሎ የሚከናወኑ እና በተደጋጋሚ ለረጂም ዓመታት የታዩ መሆኑ እየታወቀ  እንደ ተዘረፈ የአገር ሀብት ፤ንብረት እና የይስሙላ ዲሞክራሲ(ህዝባዊ መንግስት)፣ ኢፍትኃዊነት……ከባዶ እንጀምር ማለት እንዴት ኢትዮጵያ ዓምላክን እና ዕዉነትን የሚፈራ ሠዉ ብታጣ ነዉ ፡፡

ዜጎች በማንነታቸዉ ሲሞቱ ፤ሲገለሉ፤ ሲገደሉ …..ለዓመታት እያየን ይህ የአገር ጉዳይ ፣ የህዝብ ጥያቄ…..አይደለም እየተባለ መኖር ከዚህ በላይ ባዶነት ምን ይምጣ ፡፡ ዕዉነት ኢትዮጵያ ዉስጥ በማንነት የደረሰዉ ግፍ እና መከራ ላለፉት ሠላሳ ዓመታት  ቢቆጠር ከዚህ በላይ በዓለም ላይ በሰዉ ልጆች በራሳቸዉ አገር ፣ምድር እና ግዛት እንደ ኢትዮጵያ ህዝብ በተለይም ኢትዮጵያዉያን እና ዐማራ ላይ የደረሰዉ ሰቆቃ ከዕዉነት በላይ ምን ሊሆን እና ማን ሊናገር ይችላል፡፡

ከባዶ መነሳትን ክህደት እና በአገር እና ህዝብ ላይ የማላገጥ ሴራ መሆኑን አዉቀን ሁላችን ለራሳችን እና ለአገራችን የባዶ  ጅምር ነጋዴዎችን በቃ ልንል ይገባል ፡፡

ኢትዮጵያ እና ህዝቧ ባዶ ሆነዉ አያወቁም ባዶነትን  ለከንቱ ዉዳሴ ትረፍ የሚገለገሉበት የህዝብን እና የአገርን አንጡራ ሀብት እና ንብረት ለግል እና ለቡድን ለሚመዘብሩት መንደርደሪያ መንገድ መሆኑን ይህም የባዶነት ጭምብል እጂ እጂ ማለቱን እና እንደሰለቸን ሊያዉቁት ይገባል፡፡

ነፃነት ወይም ሞት !

ሞት ለፀረ ኢትዮጵያ!

Neilos Amber

1 Comment

  1. ጎሰኞችና ፅንፈኞች እንደአሸን በፈሉበት አገር ውስጥ ሕዝብን በሰላም ለማስተዳደር ከባድ መሆኑን ኢትዮጵያ እያስመሰከረች ነው:: ከየአቅጣጫው የሚሰነዘረው ስድብና ውርጅብኝ አንዱ ጎሳ ተቀናቃኜ ነው የሚለውን የሚኮንና የሚወነጅል እንጅ እስከፊና ልብ የሚሰብር የስው ልጆች የእርስ በርስ እልቅት መሆኑን አይደለም:: ሟቹም ገዳይም ሰው ነው:: በአማራ ስም የሚሞተውና ገዳዩ ፅንፈኛውና ወደ እውሬነት የተለወጠው የኦኔግ ሸኔም ወንጀለኞች የሰው ልጆች ናቸው:: ታዛቢዎችም የሰው ልጆች ነን:: ይህ የሰው ልጅ ግድያ የተፈለገው ስም ቢሰጠውም የሰው ልጆች እልቂት መሆኑን ማጉላት ትተን የሟቾቹን መንደርና የመጡበትን ጎሳ ላይ በማተኮር የሰው ልጅነታቸውን እያሳጣን ነው:: ይህም መንደርኝነትና ጎሳነት የሰውልጅነት ላይ እንዳናተኩር አድርጎናል::ኢትዮጵያ ላይ የወደቀባት መከራ በመንደርነትና በጎሳ ጠባብነት የመጣ ነው:: ይህ መንደርነትና ጎሳነት አስተሳሰብ እስካልጠፋ ድረስ ይህ አስከፊና አሳዛኝ የሰውልጆች እልቂት ይጠፋል ይወገዳል ዩሚል እምነት የለኝም:: ምክንያቱም ይህ አስተያየት የምሰጥበት ፅሁፍ ከዚህ ውጭ እንዳስብ አላደረገኝም:: ችግሩን አላስቀመጠም:: ምክንያትም ብሎ የሚያቀርበው ተደጋግሞ የሚለፈፈውን የጎሳ ሹኩቻ አንዱ ጎሳ ሌላውን ጎሳ ሊያጠፋ አድርጎ ነው:: በወለጋ ውስጥ የሞቱት የቆሰሉት የተፈናቀሉት በሰፊው የሰው ልጆች ወይም በጠባቡ ከሆነ ኢትዮጵያውያን እህቶቻችን ወንድሞቻችን ናቸው:: በአገራቸው ውስጥ እንደኢትዮጵያ ዜጋዎች በፈለጉበት ቦታ የመኖር መብት እንዳላቸው ከመከራከርና ከመጮህ በጎሳ ማንነታቸው ብሎ የችግር መንስኤ የሆነውን ጎሰኝነት ከሰው ልጅነት በላይ አድርጎ ማቅረብ የገዳዮችን ጉዳይ ማስፈፀም ነው::
    የሚያሳዝነው ለዘመናት በኢትዮጵያ ውስጥ በትልቁም ሆነ በትንሹ ሕዝብን ለማከፋፈልና ለማጋጨት የተያዘውን የጎሳ ፖለቲካ የአቢይ አህመድ ስራ ነው:: አቢይ እህመድ አማራን ሊያጠፋ ቆርጦ የተነሳ ነው ማለት የጎሳን ጦርነት የሚፈልግ አካል ደጋፊ ካልሆነ ለኢትዮጵያ ሕዝብ አንድነትና ህብረት የሚማስብና የሚቆጭ አይደለም:: የዚህ ፅሁፍ ደራሲ የትጫረው የጎሳ ጠብ እሳይ ላይ ቤንዚን አርከፍካፊና ፅሁፉም የዚህ የጎሳ ጥላቻን አራማጅ ነው:: እንዲህ አይነት ፅሁፍ ለኢትዮጲያና ለሕዝቦቿ የሚሰጡት ጥቅም የለም:: ጎሳነት ለማንም አይጠቅምም::ሟቾችም ገዳዮችም የሰው ልጆች ሙሆናቸውን ተገንዝበን በምንም ምክንያት ሆነ እንዲህአይነት የሰው ልጆች ጭፍጨፋ በማንኛውም የሰው ልጅ መወገዝ አለበት:: አቢይ አህመድ እንደመሪ ይህንን አይነት የሰው ልጆች እልቂት በአገሩ ውስጥ እንዲፈፀም ይፈልጋል የሚል እምነት ፍፁም የለኝም:: ሰውዬውንና አመራሩን መቀበል አለመቀበል የግለሰብ ምርጫ ነው:: ግን እንዲህ አይነት በጎሳው ጥላቻ ላይ የተመሰረተ የተሳሳተ ክስ የፀሃፊውን ሚዛናዊነት ያስገምታል:: በጥላቻ የተገደሉብንን ኢትዮጵያውያን እህቶቻችንና ወንድሞቻችንን ነፍሳቸውን ከፃድቃን ጎን ያስቀምጥልን:: ገዳዮቻቸውን ፈጣሪና መንግስት ይፋረድልን:: የፈሰሰው የንፁሃን ደም በከንቱ እንዳይቀር ገዴዮችን ለፍትሕ እንዲያቀርብ መንግስትን በየጊዜው እናስታውስ::

Leave a Reply

Your email address will not be published.

289346752 337752958531763 1103120152180402484 n
Previous Story

የኢዜማ መሪ ብርሃኑ ነጋ በተዘዋዋሪ በአማራ የዘር ጭፍጨፋ ሙሉ በሙሉ ተጠያቂ ነው

288869500 7624097970964785 1425253706093743685 n
Next Story

ሰባተኛው ንጉስ፣ እባክህ ወደ ጠንቋይ ሂድና የቀረህን እድሜ ይንገርህ – ደረጀ አያኖ

Go toTop